uk
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Відкрити в Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Показати більше
669
Підписники
-124 години
+37 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
ዲያቆን ነው ሰማእት ነው ሀዋርያ ነው ቅዱስ ነው ሰማያት ተከፍቶለት ስላሴን በአንድነት በሶስትነት ያየ ነው ካህን ነው በድንጋይ እየተወገረ ለወጋሪዎቹ የሚፀልይ ሊቀ ዲያቆን ነው የስጢፋኖስ ውለታ የሌ
ዲያቆን ነው ሰማእት ነው ሀዋርያ ነው ቅዱስ ነው  ሰማያት ተከፍቶለት ስላሴን በአንድነት በሶስትነት ያየ ነው ካህን ነው በድንጋይ እየተወገረ ለወጋሪዎቹ የሚፀልይ ሊቀ ዲያቆን ነው የስጢፋኖስ ውለታ የሌለበት የለም፡፡ በረከቱ ይደርብን ፀሎቱ ይጠብቀን ለቀዳሜ ሰማእት ለቅዱስ እስጢፋኖስ አመታዊ ንግስ እንካን አደረሳችሁ ።

ጥቅምት 17 የፊታችን እሁድ ጥቅምት 17 2017ዓ.ም የቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ አመታዊ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ይከበራል። አይቀርም!

🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴 በእንተ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሐዋርያት 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዚህም ወራት ደቀ መዛሙርት እየበዙ ሲሄዱ ከግሪክ አገር መጥተው የነበሩት አይሁድ በይሁዳ ኖረው በነበሩት አይሁድ አንጐራጐሩባቸው፥ በየቀኑ በተሠራው አገልግሎት መበለቶቻቸውን ችላ ይሉባቸው ነበርና። ² አሥራ ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሁሉን ጠርተው እንዲህ አሉአቸው፦ የእግዚአብሔር ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም። ³ ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፥ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፤ ⁴ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን። ⁵ ይህም ቃል ሕዝብን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፤ እምነትና መንፈስ ቅዱስም የሞላበትን ሰው እስጢፋኖስን ፊልጶስንም ጵሮኮሮስንም ኒቃሮናንም ጢሞናንም ጳርሜናንም ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም መረጡ። ⁶ በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው፥ ከጸለዩም በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው። ⁷ የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ። ⁸ እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር። ⁹ የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ¹⁰ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም። ¹¹ በዚያን ጊዜ፦ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ። ¹² ሕዝቡንና ሽማግሌዎችንም ጻፎችንም አናደዱ፥ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና፦ ¹³ ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ¹⁴ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ። ¹⁵ በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት። 🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️

🌸🌸🌸🌸🌸🌸 🌸  ካነበብነው 🌸 🌸🌸🌸🌸🌸🌸 " ሐር አንተ ስትለብስ ድኻ ጨርቅ እያጣ ዕወቅ ሐሩ ልብስህ በእሳት እንዲያስቀጣ " ጣፋጭ ጥበብ ገጽ ፻፸፬ ቁጥር  ፩ሽ ፪፻፹፭ 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 🌹 ዑል ራስ ካሣ ኃይሉ  🌹 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹

ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡ በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡  በመጨረሻም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡ እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ! እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን:: አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ፤

በጥቅምት 2017 ዓም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! •ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጐጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ •ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ •ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤ ዓመቱን ጠብቆ ስለ አጠቃላይ ተልእኮአችን ለመወያየት በዚህ ጉባኤ የሰበሰበን አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤ “ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊሃ ወዓቃቢሃ ለነፍስክሙ፤ አሁንም ወደ እረኛችሁና ወደ ነፍሳችሁ ጠባቂ ተመለሱ” (1 ጴጥ 2÷!5) ሁሉን የሚችል አምላካችን እግዚአብሔር በፍቅሩና በፍቅሩ መነሻነት ብቻ ፍጥረታትን በሙሉ እንደፈጠረ ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፤ ከፈጠረም በኋላ የክብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ወዶ ክብሩን አድሎአቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ካደላቸው ነገሮች አንዱ በየዓይነታቸው ጠባቂና መሪ እያደረገ በፍጡራን ላይ ፍጡራንን መሾሙ ነው፤ ይህ ስጦታ በሰማይም ሆነ በምድር ላሉ ፍጥረታት የተሰጠ የሱታፌ መለኮት ስጦታ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ ሁሉም ፍጡራን አራዊትም ሆኑ እንስሳት ይብዛም ይነስ ጠባቂና መሪ እንዳላቸው እናስተውላለን፤ በተለይም የፍጥረታት ቁንጮ የሆኑ መላእክትና ሰዎች መሪና ሹም እንዳሏቸው የማንክደው ሓቅ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሓፍም ይህንን ደጋግሞ ያስረዳል፤ የእነዚህ ሁሉ ላዕላዊ ጠባቂና መሪ ደግሞ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በፍጡራን ላይ ፍጡራንን ጠባቂዎች አድርጎ ሲሾም ፍጡራንን የክብሩ ተሳታፊ ለማድረግ እንጂ የእሱ ጥበቃ አንሶ ወይም ድጋፍ ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ፍጹምና ላዕላዊ የሆነ ጥበቃው ሁሉንም ያካለለ ነውና ከእሱ ቊጥጥርና ጥበቃ ውጭ አንድም ነገር እንደሌለ የምንስተው አይደለም ፡፡ •ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት •የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! በአምሳለ እግዚአብሔር በተፈጠረውና በክብር መልዕልተ ፍጡራን በሆነው ሰው ላይ በዚህ ዓለም የተሾሙ ሁለት አካላት አሉ፤ እነሱም የመንፈስና የዓለም መሪዎች ናቸው፡፡  በተለይም የመንፈስ መሪዎችና ጠባቂዎች የተባሉት በመንፈስ ቅዱስ ተሹመን በዚህ ክርስቶሳዊ ጉባኤ የተሰበሰብነው እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ነን፡፡ ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የተሰጠን ኃላፊነት እጅግ በጣም ታላቅ እንደመሆኑ የሚጠበቅብን ውጤትም በዚያው ልክ ትልቅ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለግበታል ያለው የጌታችን አስተምህሮም ይህንን ያስታውሰናል፡፡ ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ደቅኖብናል፡፡ ክፉው መንፈስ የሰውን አእምሮ በማዛባት ምእመናንን በቅዱስ መጽሐፍና በሕገ ተፈጥሮ ከተመደበላቸው የጋብቻ ሕግ በማስወጣት እንስሳት እንኳ የማይፈጽሙት ነውረ ኃጢአት እንዲፈጽሙ በመገፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ በአማንያን ልጆቻችን ላይም በረቀቀ ስልት ግድያ፣ እገታ፣ አፈና፣ የመብት ተጽዕኖ እና አድልዎ በማድረግ እንደዚሁም በአስመሳይ ስብከትና አምልኮ ጣዖትን በማለማመድ ሕዝቡ ሳይገባውና ሳይጠነቀቅ ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዲወጣ እያደረገ ነው፡፡ •ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት •የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! ክፉው መንፈስ በተራቀቀና በተራዘመ ስልት ሊውጠን በተነሣ ልክ እኛም ከእሱ እጥፍ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ልንመክተው ካልቻልን በፈጣሪም ሆነ በትውልድ እንደዚሁም በታሪክ ፊት በኃላፊነት መጠየቃችን አይቀርም፡፡ መከላከል የምንችለውም ችግሩን በውል ከመረዳት አንሥቶ ሕዝቡን በደምብ በማስተማርና በመጠበቅ እንደዚሁም ለመሪነታችን ዕንቅፋት ከሚሆኑን ዓለማዊ ነገሮች ራሳችንን በማራቅ ነው፡፡ ሕዝቡም በዚህ ዙሪያ ሊያደምጠንና ሊከተለን የሚችለው መስለን ሳይሆን ሆነን ስንገኝለት ነው፡፡ ሕዝቡ ሊከተለን የሚችለው እሱን በብቃት ለመጠበቅ ዓቅሙም ተነሣሽነቱም ቁርጠኝነቱም እንዳለን ሲመለከት፣ እንደዚሁም ከዕለት ተዕለት ተግባራችንና አኗኗራችን የሚያየው ተጨባጭ እውነታ ኅሊናውን ሲረታ እንደሆነ አንርሳ፡፡ የምናስተምረው ሌላ የምንሰራው ሌላ ከሆነ ግን ከሕዝቡ አእምሮ መውጣታችን እንደማይቀር መገንዘብ አለብን፤ በመሆኑም በሰብእናችን፣ በአስተዳደራችን፣ በአመራራችንና በጥበቃችን ሁሉ እንደቃሉና እንደቃሉ ብቻ ለመፈጸም መትጋትና በቁርጥ መነሣት ጊዜው አሁን ነው እንላለን፡፡ ይህ ሲሆን በምእመናንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት አስተማማኝና እንከን የለሽ ይሆናል፤ ይህ ከሆነ እውነትም የመሪነት፣ የእረኝነትና የመልካም ተምሳሌነት ኃላፊነታችንን በትክክል ተወጥተናል ማለት እንችላለን፡፡ •ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት •የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!   የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክልል መምራት ይጠበቅበታል፡፡ ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡ እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን  የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡ ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡ ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ

የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ተካሄደ። በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ቀጣይ በሰበካ ጉባኤ አባልነት የሚቀጥሉ አባላት ምርጫ ተካሄደ። ከካህናት ከቀረቡ እጩዎች 1:- ቀሲስ ብርሃነ መስቀል ግርማ 2:- ዲ/ን ሰሎሞን ወ/አማኑኤል 3:- ቀሲስ ጌታሁን (ተጠባባቂ) ከሰንበት ት/ቤት ከቀረቡ እጩዎች 1:- መዘ/ር አሰግድ አስፋው ከምዕመናን ከቀረቡ እጩዎች 1:- መ/አለቃ ገበየው 2:- ወ/ሮ ቆንጂት በቀለ 3:- አቶ ተሾመ ገላልቻ

የአቋም መግለጫ፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ “ትውልደ ትውልድ ይንእዱ ምግባሪከ ወይዜንዉ ኃይለከ - የልጅ ልጅ ሥራህን ይናገራሉ፤ ያመሰግናሉ፣ ከሃሊነትህን ይናገራሉ ያስተምራሉ” መዝ 144 ቁ 4 ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ዓለምአቀፋዊት የሆነቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያዊ ተልዕኮዋ ረጅም ዘመናትን ሰማያዊውን ጥበብንና ምድራዊውን ዕውቀትን በማስተማር፣ የሀገርና የወገንን እምነትና ፍቅር ምንነት ከተግባር ጋር፣ ሰላምና አንድነትና በማስፈን፣ ለሰው ልጅ ዘለዓለማዊ ድኅነት ሌሌት ከቀን ያለማቋረጥ ሰዓት ሳይገድባት፣ መልክዓ ምድር ሳይገድት፣ የሰው ባህልና ቋንቋ ሳይወስኗት፣ ትውልድን፣ ከትውልድ፣ ዘመንን ከዘመን፣ ሰማያውያን ከምድራውያን፣ ፍጡራንን ከፈጣሪ ስታገናኝ ኖራለች፡፡ ለሰው ዘር ጥበብን፣ ለትወልድ ታሪክና ትውፊትን፣ ስትቀምር፣ ነፃነትና ሰብዓዊ ክብርን በዐውደ ምኅረቷ ስታውጅ፣ በአባቶችና በሊቃውንት በሕየወት ሰሌዳ፣ በደመቀ ቀለም በቃልም በመጽሐፍም ስታስተጋባ እስከ አሁን አለች ወደፊትም ትኖራለች፡፡ ከዚህ መሠረታዊ የታሪክ ዕሴት በመነሣት ለዛሬው 43ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ደርሰናል፡፡ በዚሁ ጉባኤው በቆየባቸው ቀናት ውስጥ የቅዱስነታቸውንና የብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ አባታዊ መልእክቶች፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሪፖርት፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር አህጉረ ሰብከት ዘገባዎች፣ ከውይይት ሐሳቦች፣ ከአበው ሊቃነ ጳጳሳት መልእክቶች፣ ከቡድን ውይይትና ዘገባ በመነሣት ከቃለ ጉባኤ ሐሳብ በተጨማሪ በቅዱስ ሲኖዶስ ትኩረት ተሰጥቶባቸው በአጀንዳ ተቀርጸው ውይይትና ምክክር ተደርጎባቸው ውሳኔና መመሪያ ይደረግባቸው ዘንድ እኛም ለተፈጻሚነቱ የራሳችንን ድርሻ መወጣት እንድንችል ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን የአቋም መግለጫ አቅርበናል፤ 1. በጉባኤው መክፈቻ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉፉልንን ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተቀብሎታል፣ ለተግባራዊነቱ ቃል ይገባል  2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፉልንን አባታዊ መልእክት ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ ተግባራዊ ለማድረግ ቃል እንገባለን፤ 3. በብዙ የሀገራችን ክፍል ባለው የሰላም እጦት የተፈጠሩት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምክንያት የካህናት፣ የመነኰሳትና የምእመናን ሞትና ስደት በጥብቅ እያወገዝን በዚህ ታሪክ የማይረሳው በምድር ወንጀል፣ በመንፈሳዊው ዓለምና በሰማይ ኃጢአት የሆነ እኩይ ተግባር የተሰማራችሁ ሁሉ ወደ ርኃራኄ ልብ እንድተመለሱ ጉባኤው በአጽንዖት ጥሪውን ያስተላልፋል፤  4. የሰላም ዕጦት ጉዳይ ምንም እንኳ ዓለም አቀፍ ቢሆንም ሀገራችንም በተከሰተው ግጭትና ጦርነት ምክንያት ሰላም ካጣች ሰንብታለች፣ ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ በዓለም የሚደነቅ፣ ለሀገር ተገን የሚሆን አስደነቂ ውሳኔ እንደሚወስን ተስፋች ጽኑ ነው፣ ጸሎታችንም ነው፤ የአገልጋዮች እንባ የሚታበስበት፣ ለነገ ታሪክ የትውልድ ተወቃሽ ከመሆን ይልቅ፤ የሰላምና እርቅ ምሳሌ የምንሆንበት ከፍተኛ የሰላም ሥራ ልዩ የሆነ የሰላም ኮሚቴ ተቋቁሞ ዘላቂ ሰላምን ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን የሚያመጣ ሥራ እንዲሠራ ጉባኤው ያሳስባል፤ 5. የዚህን ዓለም ተድላ ንቀው፣ ደዋ ለብሰው ጤዛ ልሰው በገዳም ተወስነው ድምጸ አራዊቱን ግርማ ሌሊቱን ታግሰው ለመላው የሰው ዘር የሚጸልዩ ይህን ይደግፋሉ ያንን ይቃወማሉ የማይባሉ ገዳማውያን መነኮሳት ከየበአታቸው ተጎትተው ወጥተው የተገደሉበት ሁኔታ በሀገራችን መከሰቱ ጉባኤውን እጅግ አሳዝኖታል ይኽ ጉዳይ ቀጣይነቱ እየታየ ስለሆነ የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን የሕግ ሥራ በመሥራት የሰው ልጅ ከአምላክ የተሰጠውን የመኖር መብት፣ የእምነት ነፃነት፣ የመዘዋር ተፈጥሯዊና ሰብዓዊ መብት በሀገራች እንዲከበር ያሳስባል፤  6. በታሪካችን ያላየነው ከአባቶቻችን ያልሰማነው በመጻሕፍት ያላነበብነው ከኢትዮጵያ ባህልና ሥነ ልቡና ውጪ በሆነ መንገድ ሰዎችን ለገንዘብ ሲባል ማገት በተለይም ፊትና ኋላ ግራና ቀኝ እሳትና ውኃ ያለዩ ሕፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው፣ ወጣቶችና አረጋውያን ሳይቀር እያተገቱ የሚሰቃዩበትና የሚደፈሩበት ሁኔታ የገጠመንን ፈተና ክብደቱን የሚያሳይ መሆኑ ይኽ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት መፍትሔ እንዲበጅለት ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፤ 7. ጥላቻና የጥፋት ቅስቀሳዎች፣ በዜጎች መካከል አለመተማመንና መለያየት፣ ለሀገር አንድነትና የሕዝብ አብሮነት ጠንቅ፣ ለወደፊቱ አስጊ የሆኑ እንቅስቃሴዎች የበዙበት፣ የትውልዱ የወደፊት በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ የመኖር ዋስትና እየጠፋ፣ በርካታ ወጣቶች በስደትና በመፈናቀል ላይ ያሉበት ሁኔታ በመኖሩ የጥላች ንግግር፣ ዘለፋና ያልተገባ ትችትና መናናቅ ማንንም የማያንጽ ክፉ ትምህርት፣ ለሀገርም፣ ለሕዝብም የማይጠቅም ሁሉንም የሚያጠፋ ስለሆነ በእንዲህ ያለ ተግባር መገናኛ ብዙኀን በመጠቀም የተሰማራችሁ፣ ሁሉ በሚያፋቅርና በሚያዋድድ ተግባር እንድትሰማሩ ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፣ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚሁ ትኩረት ሰጥቶ መመሪያና ውሳኔ ያወጣ ዘንድ አጽንዖት እንጠይቃለን፤     8. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 20 በእንተ ሰማዕታት የጌታችንን ትምህርት መሠረት በማድረግ በተሠራው ቀኖና ካህናትና ምእመናን ሰማእትነትን የተቀበሉበትን ቀን መዘከርና ማክበር፣ የከበረ አጽማቸውን በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን በክብር ማስቀመጥ፣ ቤተሰቦቻቸውንና በእነሱ ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ የሰማእታት ቤተሰብ በሚል መርዳት የተደነገገ ቀኖና ነው፤ ይኽን በማድረግ የሰማእትነት ዋጋን እናገኛለን፣ ቤተ ክርስቲያነን እናጸናለን፤ በዚህ ቀኖና መሠረትና ከሰብዓዊ ርኅራሄ በመነሣት በሰማዕትነት የተለዩን ወገኖች መታሰቢያቸው እንዲደረግ፣ ቤተሰቦቻቸውና ጉዳተኞችን ወላጆቻውን ያጡ የካህነትና የምእመንና ጨቅላ ሕፃናትና ያልደረሱ ልጆች፣ ያለጧሪ የቀሩ አረጋውያን የቤተ ክርስቲያንን እንክብካቤ በጥብቅ ይፈልጋሉ፤ ለዚህ መፍትሔ እንዲሆን በውጭና በሀገር ውስጥ ያሉ አህጉረ ሰብከት ያካተተ አስቸኳይ ዓለም አቀፍ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲሰጥበት እያሳሰብን ለተግባራዊነቱም ሁላችንም ቃል እንገባለን፣ 9. በአንዳንድ አካባቢዎች ሕግንና የአምልኮ ነፃነት ሰብዓዊ መብትን በመጣስ የመስቀል ደመራና የባሕረ ጥምቀት ቦታ መወሰድ ሃይማኖታዊ አለባበስና መስቀል መያዝን በመከልከል የአንገት ማዕተብን መበጠስ፣ በኦርቶዶክሳውያን ላይ እንግልትና ወከባ መፍጠር አሳዛኝ በመሆኑ ድገርጊቱን አጥብቀን እየተቃወመን በቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ውይይት እንዲደረግበት ጉባኤው ያሳስባል፤  10. ቤተ ክርስቲያን እንኳንስ ተናግራ ሰማች ሲባል የሚያስደነግጥ ግርማና መታፈር፣ መከበርና መወደድ የነበራት በመሠረተችው ሀገር የምትሳደድበት፣ የመሪዎቿ አባቶች ጥሪ የማይከበርበት፣ የሰላም ጥሪ ድምጽዋ የማይሰመባት፣ ምክንያቱ ምን እንደሆነ በመፈተሸ ክብርና ልዕልናዋ እንዲመለስ በቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ውይይትና ጥልቅ ምክክር እንዲደረግ መፍትሔም እንዲፈለግለት ጉባኤ ያሳስባል፤

ስለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ብሎ ሀገራችን ኢትዮጵያን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ይማርልን። መልካም ቀን!
ስለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ብሎ ሀገራችን ኢትዮጵያን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ይማርልን። መልካም ቀን!

ውጤት 👆👆👆
ውጤት 👆👆👆

🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ መንፈሳዊ የጥያቄ እና መልስ ውድድር"start the quiz" የሚለውን ይጫኑ"i am ready "ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል።መልካም ዕድል🛎' 🖊 6 questions · ⏱ 30 sec

የፈረሱ ጫማ (ዲ/ን ሕሊና በለጠ) በጉልበት ደካማ የሆነ ሉክ ፋርነም የተባለ ሰው ነበር፡፡ ሀገሩ አሜሪካ ለነፃነቷ በምትዋጋበት ወቅት እንደ ሌሎቹ ጎበዞች ወደ ጦርነት በመዝመት ለመዋጋት ባለመቻሉ ጸጸቱ ሊወጣለት አልቻለም፡፡ በኀዘን ‹‹አልረባም፤ ጓደኞቼና ባልደረቦቼ ኹሉ ሀገራቸውን ይከላከሉ ዘንድ ደማቸውን ሊያፈሱ ወደ ጦርነት ሔደዋል፡፡ እኔ ግን ምንም ላልጠቅም እዚህ ቁጭ ብያለሁ፡፡ የአንድ ብረት ቀጥቃጭ ረዳት ከመሆን ውጪ ምን ጥቅም አለኝ?›› እያለ ራሱን ይወቅስ ጀመር፡፡ ድንገት ጥቂት ወታደሮች መጥተው ከትካዜው መለሱትና ‹‹ወንድም፣ ለአንዱ ፈረሳችን የፈረስ ጫማ ልትሠራልን ትችላለህ?›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹በሚገባ፡፡ ብረት ቀጥቃጩ አለቃዬን በተደጋጋሚ በዚህ ሥራ አግዤዋለሁ፤ የፈረስ ጫማን ስሠራም ጎበዝ ነኝ›› ሲል መለሰ፡፡ ወዲያውም በፍጥነት ምርጥ የፈረስ ጫማን ሠራ፡፡ እንደ ጨረሰም፣ ከወታደሮቹ አንዱና በጦርነቱም ጉልህ ድርሻ የነበረው የፈረሱ ባለቤት ኮሎኔል ዋርነር ‹‹ልጄ፣ ዛሬ ለሀገርህ የሠራኸው ሥራ ከዐሥር ወታደሮች ተጋድሎ ጋር እኩል ነው›› አለው፡፡ በዚያች ቀን ይኸው ኮሎኔል ተዋግቶ አሸነፈ፡፡ ምናልባትም ከመጋረጃው በስተጀርባ ያለው ወታደር - ሉክ ፋርነም ያንን የፈረስ ጫማ ባይሠራለት ኖሮ ኮሎኔሉ ሊሸነፍ ይችል ነበር፡፡ (ከአጫጭር የታሪክ ስብስብ ላይ እንዲመች አድርጌ እንደተረጎምኹት) ወዳጄ ሆይ፣ ያለህን ነገር አሳንሰህ አትመልከተው፡፡ የምታውቃቸው ኹሉ አንተ የማትችለውን መዋጋት ይችሉ ይሆናል፤ ነገር ግን ለፈረሶቻቸው አንተ ጫማ ካልሠራህ ኹሉም ይሞታሉ፤ ወይም ይማረካሉ፡፡ ያንተ ብረት ቀጥቃጭነት የወዳጆችህን ወታደርነት የሚደግፍ ነው፡፡ ካላንተ የሚሞቱ ወታደሮች ናቸው፡፡ ምናልባትም አምላክ አንተን ወታደር ያላደረገህ እኮ ለዚህ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ብረት ቀጥቃጭነትህን አታማርር፡፡ የናሳዋ (NASA) የጽዳት ሠራተኛ ያለችውን አስታውስ፡፡ ፕሬዝዳንቱ መጥቶ ‹‹ምን እያደረግሽ ነው?›› ሲላት ‹‹እያጸዳሁ ነው›› አይደለም ያለችው፤ ‹‹ወደ ጠፈር መንኮራኩር የማምጠቁን ሒደት እያገዝኩ›› እንጂ፡፡ ልክ ናት፡፡ እርሷ ባታጸዳና የሕዋ ምርምር ጣቢያው በቆሻሻ ቢሞላ መንኮራኩር የማምጠቁ ሥራ እንደታሰበው አይሆንም፤ ሳይንቲስቶችም በጽዳት ችግር ባልታሰበ ቦታና ጊዜ ድንገተኛ ሕመም ሊይዛቸው ይችላል፡፡ ስለዚህ እነርሱ የማምጠቁን አሳብ ሲሸከሙ እርሷ የጽዳታቸውን ጉዳይ ትሸከማለች፡፡ አንተ በናቅከው ጸጋህ ካልተሸከምክላቸው የሚጎዱ ብዙዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ ፈጣሪህን ለምን እንዲህ አላደረገኝም ብለህ አትውቀስ፤ ባደረገህ ነገር አመስግነው እንጂ፡፡ ሉክ ፋርነም ያልተሰጠውን ይመኝ ነበር፤ በተሰጠው ጸጋ ግን የዐሥር ሰው ዋጋ እንዳለው ኮሎኔሉ ነገረው፡፡ ወዳጄ፣ ባልተሰጠህ ነገር ለማገልገል ከተነሣህ በጣም የሚሳካልህ ከሆነም እንደ አንድ ሰው ታገለግላለህ፡፡ በተሰጠህ ጸጋ ግን የዐሥር ሰው ሒሳብ ነህ፡፡ ስለዚህ አንተም የራስህን ሥራ፤ ወዳጆችህም የሚችሉትን ይሥሩ፤ ያኔ ምርጥ ዓለም ይፈጠራል፡፡ የክርስቶስን ደቀመዛሙርት እስኪ ተመልከት፤ 36ቱ ቅዱሳት አንስት ናቸው፤ 72ቱ አርድዕት ናቸው፡፡ የቀሩት 12ቱ ብቻ ሐዋርያት ናቸው፡፡ ኹሉም ድርሻ አላቸው፡፡ ሌሎቹ ድርሻቸውን ባይወጡ 12ቱ የሐዋርያነት ሥራቸው እክል ይገጥመው ነበር፡፡ እነ ቅዱስ እስጢፋኖስ የጓዳውን ነገር ትተው እንደነ ቅዱስ ጴጥሮስ ካላስተማርን ቢሉ ኖሮ የክርስትናው ታሪክ ሌላ ይሆን ነበር፡፡ ኹሉም በተሰጠው ተጋ፤ በተሰጠው ጸጋን አገኘ፡፡ ስለዚህ በተሰጠህ ትጋ፡፡ በተሰጠ ማትረፍ ክብር ነው፤ ባልተሰጠ ማትረፍ ግን ሌብነት ነው፡፡ ሚስት ባል ልኹን ካለች፣ ባልም ሚስት ልኹን ካለ ቤተሰቡ ኹሉ ይመሰቃቀላል፡፡ አንድ ቤተሰብ አንድ ባል አንድ ሚስት ነውና ያለው፡፡ ዛሬ ዓለም የተመሰቃቀለችው እንዲህ በሚሉት እኮ ነው፡፡ ስለዚህ ኹን ያለህን በመሆን ጸጋህን አሳድግ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እውነትን በፍቅር ይዞ ወደ ክርስቶስ ማደግ›› ያለው ይህንን ነው፡፡ (ኤፌ.4፡15)፡፡ ማንነትህ እውነት ነው፤ በፍቅር ተንከባክበኸው ዕደግበት፡፡ የምትችለው አለ፣ የማትችለውም አለ፤ የምትሆነው አለ፣ የማትሆነውም አለ፡፡ ይህ እውነቱ ነው፡፡ እውነቱን ሳትጠላው በፍቅር ይዘኸው (ወደኸው) እደግበት፡፡ የማትችለውን ልቻል፣ የማትሆነውን ልሁን ካልክ ግን ሐሰት ስለሚሆን አታድግበትም፡፡ ግብረሰዶማውያን የተፈጥሮአቸውን እውነትነት ቢቀበሉና በፍቅር ቢይዙት በምድር ላይ መአትን አያመጡም ነበር፡፡ በሆንከውና ባለህ ነገር ብቻ አንተ ለዓለም ውድ ሀብት ነህ፤ ለሀገርህ ውድ ሰው ነህ፤ ለሃይማኖትህ ዕንቁ ነህ፡፡ ለሀገርም ለሃይማኖትም ኪሳራ የምትሆነው ባልሆንከውና በሌለህ ለመተወን ስትነሣ ነው፡፡ ስለዚህ ለኹላችንም ጥቅም ስትል በሆንከውና ባለህ ነገር ብቻ ኑርልን፡፡ ዲ/ን ህሊና በለጠ

✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨
ድንግል ማርያም እግዚአብሔር ስለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው ወይስ ንጽሕት ስለሆነች ነው እግዚአብሔር የመረጣት?
አንዳንዶች ስለ ድንግል መመረጥ ሲነገር ሲሰሙ ሲመርጣት ላትመረጥ ነውን? እርሱ ጠበቃት እንጂ እርስዋ ምን አደረገች ሲሉ ይሰማሉ። እግዚአብሔር ሰለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው የሚለው አደገኛ ክህደት ነው። ለምን ቢሉ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠውን ነፃ ፈቃድ የሚንድ ነውና። ዳግመኛ እርሷ እግዚአብሔር ስለመረጣት ብቻ ከሆነ ንጽሕት የሆነችው እያንዳንዱ ሰው ንጹሕ የማይሆነው እግዚአብሔር ስላልመረጠው ነው ወደሚል የቅድመ ውሳኔ ክህደት የሚያመራ ጠማማ መንገድ ነው። ✨✨🌹 እንዲህ ከሆነ ደግሞ በዓለም ላይ ለሚሠሩ የርኩሰትና የአመፅ የበደል ውድቀቶች ሁሉ ተጠያቂው እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም ብሎ እግዚአብሔርን መሳደብ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር የመረጠው ብቻ ንጹሕ ከሆነ ሁሉም የመንጻት ሥልጣን ካልተሰጠው በበደለኛነት ዘመናቸውን የፈፀሙ ሰዎች ተጠያቂ መሆን የለባቸውም፤ ከኃጢአት ለመንጻት ቢፈልጉ እንኳን አልተመረጡምና አይችሉም ማለት ነዋ! እንዲህ ከሆነ ሰዎች ሁሉ ሊድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የሚወድ እግዚአብሔር (ጢሞ. ፪፥፫) ፈቃዱ ወዴት አለ? እርሱ የመረጣቸው ብቻ የሚነጹ ከሆነ ባልመረጣቸው ላይ ለምን ይፈርድባቸዋል? ፈታሒ በጽድቅነቱስ ወዴት አለ? ነገር ግን ርቱዕ የሆነው የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የቀና የጸና አስተምህሮዋ እንዲህ አይደለም። እግዚአብሔር ሰዎችን ፍጻሜያቸውን አስቀድሞ አይቶ ይመርጣል እንጂ ወስኖ መርጦ የፈጠረው ሰው የለም። በወንጌል የእግዚአብሔር መንግስት በመካከላችሁ ናት ማለቱም ሰው ለመዳን የሚያስችለው ለመምረጥ የሚያበቃው ኃይል በእጁ እንዳለ ሲያጠይቅ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው የተባለውም ለዚህ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የተሰጣቸው ስልጣን  የተባለው ለመዳንም ላለመዳንም የሰው ነፃ ፈቃድና ልጅነት እንደተሰጠ ሲያስረዳ ነው። እግዚአብሔር ወደ አቤልና ወደ መስዕዋቱ ተመለከተ የተባለውም አቤል የልቡን ቅንነት የመስዕዋቱን መበጀት ስሙርነት አይቶ ተመልክቶ አቤልን ተቀበለው እንጂ አቤል እንዲያ እንዲሆን አድርጎ ወሰኖ መርጦ አልፈጠረውም። በአንፃሩ ወደ ቃየልና መስዕዋቱ አልተመለከተም ማለት የቃየልን የልቡን ጥመት አየና የመስዕዋቱን አለመበጀት አይቶ አልተቀበለውም  ነገር ግን እግዚአብሔር ለክፋት ወስኖ አልፈጠረውም። እግዚአብሔር ሲኦል የሚገቡ ሰዎች እንዳሉ አውቆ ሲኦልን አዘጋጀ እንጂ ሲኦል በሚገቡ ሰዎች ላይ አስቀድሞ እንዲገቡ አድርጎ ወስኖ አልፈጠረም። ✨✨🌹 እናቱ ድንግል ማርያምን ከእናቷ ማሕፀን መርገም እንዳይኖርባት የጠበቃት እርሱ ነው ቅድመ ዓለም የአምላክ እናት እንድትሆን የመረጣትም እርሱ ነው። ነገር ግን ፍፃሜዋን በነፍስ በስጋ በአፍኣ ንጽሕት እንድትሆን አውቆ መረጣት እንጂ እርሱ ሰለወሰነ የጠበቃት የመረጣት አይደለችም። በዘመኗ ሁሉ በቅድስናዋ ተሸልማ እንደምትኖር አውቆ ከመርገም አነጻት፥ ኖሮባት አይደለም እንዳይኖርባት ጠበቃት እንጂ! መንፈስ ቅዱስ ጠበቃት አነፃት መባሉም ፍፃሜዋን አይቶ መርገም እንዳይኖርባት ጠበቃት ማለት ነው እንጂ በዓለም ኃጢአት እንዳትሰራ ከለከላት ማለት አይደለም። ንጹህ ሆኖ መፈጠርማ አዳምም ተፈጥሮ ነበር በተፈጥሮ የተሰጠውን ንጹህ ጠባይ በቅድስና መጠቀም አልተቻለውም እንጂ እርሷ ግን ንጽሕናን ቅድስናን ደራርባ ይዛ ተገኝታለችና በዛው ድንግልናዋ ለአምላክ እናትነት በቃች። የሕይወት ፍሬን አፈራችበት እንዲመርጣት እግዚአብሔርን የሳበ በአምላክ ዘንድ ሞገስን የያዘ ንጽሕና ይዛ ተገኝታለችና እንድትመረጥ ሆና ተገኝታለች። ንጹሃንን ለክብር መምረጥማ ለፈጣሪ ድንቅ አይደለም ከእርስዋ ይልቅ ጠላቶቹን እኛን በደሙ ፈሳሽነት ይቅር ማለቱ አይደንቅምን? 📝ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ 📚 አሐቲ ድንግል ✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨

"አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ኾይ የጌትነታችኹ ምስጋና በፍጡር ኹሉ አንደበት የሚነገር ሲኾን ከፍጡራን ኹሉ ዓይን የተሠወረ ለኾነ ሥነ ገጻችኹ ሰላምታ ይገባል🙏 ሥሉስ ቅዱስ ኾይ 🤲 በፍጡራን ኹሉ የበ
"አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ኾይ የጌትነታችኹ ምስጋና በፍጡር ኹሉ አንደበት የሚነገር ሲኾን ከፍጡራን ኹሉ ዓይን የተሠወረ ለኾነ ሥነ ገጻችኹ ሰላምታ ይገባል🙏 ሥሉስ ቅዱስ ኾይ 🤲 በፍጡራን ኹሉ የበላይ ገዥ ለመኾን ተነሣሥቶ ጸላዒ ዲያቢሎስ ከባለሟልነታችኹ ወጥቶ ከማኅበረ መላእክት በተለየ ጊዜ በአርአያችኹና በአምሳላችኹ ሰውን ፈጠራችኹ በሱ ቦታ ተካችኹ ክብር ምስጋና ይግባችኹ።"                         መልክአ ሥላሴ

በ2016 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 271 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገለጸ ! ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በየዓመቱ በሚካሄደው በ፵፫ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተ
በ2016 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 271 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ተገለጸ ! ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በየዓመቱ በሚካሄደው በ፵፫ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ዓመታዊ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ ከተሞችና ወረዳዎች የሚገኙ መንፈሳዊ የአብነት ትምህርት ቤቶች የመምህራንና የተማሪዎች መሠረታዊ ፍላጎት ማሟላት መቻሉ ተገልጿል፡፡ በአሰላ ማኅደረ ስብሐት በዓታ ለማርያም ቅ/ፋኑኤል ወቅ/ዮሐንስ ወ/ነጎድጓድ ገዳም በማኅበረ ቅዱሳን ከተገነባው ሕንጻ በተጨማሪ በመንፈሳዊ ትምህርት ቤቱ የመማርያ ክፍሎች አንዲሁም የመምህራንና የደቀ መዛሙርት ማረፊያ ቤቶች መሥራት ተችሏል ተብሏል፡፡ በሀገረ ስብከቱ በሽርካ ወረዳ ከ10 ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ 91 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነ ምእመናን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ሲል ሀገረ ስብከቱ በሪፖርቱ ጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም በደጁ ወረዳ ቡርቃ ጉራቻ ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ የሚኖሩ 150 ምእመናን በጉሬ ደቢኖ ቅ/እግዚአብሔር አብና አርጆ ቅ/ጊዮርጊስ ከ30 በላይ ምእመናን መገደላቸው የተገለጸ ሲሆን 499 አባወራና እማወራ ለስደት መዳረጋቸው ተነግሯል፡፡

#ጥቅምት_፭ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥቅምት አምስት ቀን የታላቁ አባት #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው ⚜⚜⚜💫💫💫⚜⚜⚜ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ። አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አነደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን? አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል። ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊየን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል። ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለየት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና። የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቀር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100 ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው። ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ8ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል። ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል። ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡ ስንክሳር ዘወርኃ ጥቅምት