uk
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Відкрити в Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Показати більше
669
Підписники
+124 години
+37 днів
-330 днів
Архів дописів
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እንቁ እና ታታሪ አገልጋዮቻችን ወንድሞቻችን ዲ/ን ማቴዎስ ነጋሽ፣ ዲ/ን ጎሳ መንገሻ፣ ዲ/ን ኢዮብ ሞላ እና እህታችን ለምለም በቀለ እንኳን ደስ አላችሁ
+3
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እንቁ እና  ታታሪ አገልጋዮቻችን ወንድሞቻችን ዲ/ን ማቴዎስ ነጋሽ፣ ዲ/ን ጎሳ መንገሻ፣ ዲ/ን ኢዮብ ሞላ እና እህታችን ለምለም በቀለ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን አደረሳችሁ።    መልካም የስራ እና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላችሁ መላው የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ወንድሞች እና እህቶቻችሁ እንመኝልላቹሀለን።        ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

"ከክፉ ሽሽ መልካምንም አድርግ፤ ሰላምን እሻ ተከተላትም።" - መዝሙረ ዳዊት 34፥14 -

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እንኳን ለዚህ አበቃህ ወንድማችን ቀጣይ የአገልግሎት ዘመንህ የተባረከ እና ፍሬ የምታፈራበት እንዲሆንልህ እንመኛለን።🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
+3
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እንኳን ለዚህ አበቃህ ወንድማችን ቀጣይ የአገልግሎት ዘመንህ የተባረከ እና ፍሬ የምታፈራበት እንዲሆንልህ እንመኛለን።🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

እንኳን ደስ አላችሁ! በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአርሲ ሀገረ ስብከት በደብረ ቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም የካህናት ማሰልጣኝ ሲሰጥ በነበረው የተተኪ መምህራን  የካህናት (ስልጠና) ትምህርት  ላይ የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ የሆነው ወንድማችን ዲያቆን ኤርሚያስ አለሙ አርሲ ሀገረ ስብከት አሰልጥኖ ካስመረቃቸው 60 ደቀመዛሙርት መካከል አንደኛ በመውጣት ፍኖተ ወንጌልን በመልካም ስም አስጠርቷልና እንኳን ደስ አላችሁ።

“ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፥ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቈረጡ ያነጥፉ ነበር” ማቴ.21፣8 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፥ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቈረጡ ያነጥፉ ነበር” ማቴ.21፣8  የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለተ ሆሳዕና ለምስጋና የተከፈተ አንደበት ሁሉ ለስድብ ተከፈተ ለማንጠፍ የተዘረጋ እጅ ሁሉ ለዱላ ተዘረጋ ከእግረ መስቀሉ ዮሐንስና እመቤታችን ብቻ ተገኙ:: ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለተ ሆሳዕና ለምስጋና የተከፈተ አንደበት ሁሉ ለስድብ ተከፈተ ለማንጠፍ የተዘረጋ እጅ ሁሉ ለዱላ ተዘረጋ ከእግረ መስቀሉ ዮሐንስና እመቤታችን ብቻ ተገኙ:: ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የሆሳዕና እና የመጋቢት መድኃኔዓለም በዓልን በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል!

​"ልጆች የወላጆቻቸውን ቃል ከማዳመጥ ይልቅ የወላጆቻቸውን ሕይወት አብልጠው ይመለከታሉ፤ እንዲሁም በለጋ ነፍሶቻቸው ውስጥ ያንጸባርቁታል።" — ቅዱስ ቲክሆን ዘዛዶንስክ

ኒቆዲሞስ ሰው ሳያየው በሌሊት ወደ ክርስቶስ እየሄደ ተማረ። ይሁዳም ሰው ሳያየው በሌሊት ወደ አይሁድ እየሄደ ጌታውን ሊሸጥ ይስማማ ነበር። ይሁዳ ሥዉር ክፋት በሚፈጽምት ሌሊት፥ ኒቆዲሞስ በሥዉር ወንጌል ተምሮ ጸደቀበት። የክርስትና ሕይወት ሲያድግ ከሥዉር ክፋት ወደ ሥዉር በጎነት ከፍ ያደርጋል።
ሊቀ ሊቃውንት ሥሙር አላምረው
የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

የሌሊቱ ተማሪ ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፥ ከአይሁድ አለቆችና መምህራና አንዱ ነው። በዮሐ. 3÷1 ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው እንደነበረና እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን መጥቶ እንደተማረ ተጠቅሷል። (ዮሐ 1÷2) በአይሁድ አለቆች ፊትም ”ሕጋችን አስቀድሞ ሳይሰማ የሠራውንም ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” በማለት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የተናገረ እሱ ነው ኒቆዲሞስ “መምህር ሆይ ልታስተምር ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን እግዚአብሔር ከርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርገውን ይህን ተአምር ሊያደርገ የሚችል የለምና።" በማለት ተናገረ።(ዮሐ3፥2) በዚህ ጊዜ ጌታችን የገነት በር ስለሆነው ስለ ምስጢረ ጥምቀት አስፍቶና አምልቶ በምሳሌ ጭምር አስረዳው። "እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ዳግመኛ ያልተወለደ ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማየት አይችልም” (ዮሐ 3፥3) በማለት መንፈሳዊ እውቀት የጎደለው መሆኑን አሳይቶ ዳግመኛ ያልተወለደ ሰው ከእግዚአብሔር መንግሥት ውጪ እንደሚሆን አስርግጦ ነገረው። በዚህም ታላቅ ምስጢርን ሊገልጥለት ወደደ። ይህ አነጋገር ከአይሁድ አለቆች አንዱ ለሆነው ፈሪሳዊ ሰው ከባድ ነበር። ምሥጢሩም ቢጸናበት ጊዜ ጌታን እንዲህ በማለት ጠየቀው “ሰው ከሸመገለ በኋላ እንደምን ሊወለድ ይችላል? ዳግመኛ ይወለድ ዘንድ ወደ እናቱ ማሕጸን ተመልሶ ሊገባ ይችላልን?“። (ዮሐ 3፥4) ጌታችንም ለኒቆዲሞስ መልሶ የአዳም ልጆች ሁሉ ከውሃና ከመንፈስ ዳግም ካልተወለዱ (በመንፈስ ቅዱስ መታደስን በሚያሰጥ ጥምቀት ካልተጠመቁ) መንግሥተ ሰማያትን መውረስ እንደማይችሉ ነገረው። ወስብሀት ለእግዚአብሔር!!!

የበገና ተማሪዎች የምርቃት ልዩ መርሃ ግብር! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ሲያሰለጥናቸው የቆየውን የበገና ተማሪዎች በ3ኛ ዙር ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ ያስመር
የበገና ተማሪዎች የምርቃት ልዩ መርሃ ግብር! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ሲያሰለጥናቸው የቆየውን የበገና ተማሪዎች በ3ኛ ዙር ነገ እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ ያስመርቃል። ስለሆነም ሁላችሁም በመርሐግብሩ ላይ እንድትታደሙ በአምላካችን እና በአባታችን በመድኃኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። " አስር አውታር ባለው በበገና እግዚአብሔር አመሰግናለሁ።" መዝ 32:2

​"እግዚአብሔር የሰጠን እያንዳንዱ እስትንፋስና እያንዳንዱ ሰዓት አደራ ነው። ይህን ጊዜ በከንቱ የምናሳልፍ ከሆነ፣ ነገ በፈራጁ ፊት ስንቆም ስለ እያንዳንዱ ደቂቃ መልስ እንሰጣለን።"        ቅዱስ ባሲልዮስ

✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂 የተሰጠህን ጸጋ እንዳታጣ ያልተሰጠህን አትሻ፡፡ ወደ ጸጋ ወደ ክብር ለመድረስ እግዚአብሔር ቢያበቃህ ያሳየህን እይ ያላሰየህን አያለሁ አትበል። አንድም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፣ በተሰጠህ ጸጋ ለእግዚአብሔር ተገዛ፡፡ ማር አብዝቶ መመገብ እንዳይመች እንደዚህም ሁሉ ያልተሰጠውን መሻት አይገባም አያስመስግንም፡፡     ነፍስ ያልተሰጣትን ጸጋ በመሻት እንዳትደክም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፡፡ የምታየው ማየት ቢኖር እውነተኛውን ምትሐት ሆኖ ታየዋለህ ፤ ሕሊና ያልሰጡትን ጸጋ በመሻት በማውጣት፣ በማውረድ የተሰጠውን ያጣል፡፡     ሰሎሞን መልካም ነገር ተናገረ "በሰጡት ጸጋ የማይኖር ሰው ቅጽር የሌላትን አገር ይመስላል" ብሎ ያን ማንም እየገባ እንዲዘረፈው እሱም የተሰጠውን ጸጋ ያጣል ፤ አንተ ብሩህ አእምሮ ሰውነትህን ያልተሰጣትን ጸጋ እንዳትሻ ከልክላት፡፡     ከቁመተ ሥጋ የወጣ አብዝቶ መገበርን ከአንተ አርቅ ያልተሰጠህን መሻት ከአንተ አርቅ፡፡ ባልተሰጠህና በተሰጠህ ጸጋ መካከል ትሕትናህን፣ ንጽሕናህን መጋረጃ አርጋቸው:: አንድም በተሰጠህ ጸጋ ላይ ያልተሰጠህን ጋርደው፡፡ በንጽሕና፣ በትሕትና፣ በልቡናህ የምታስበውን መንፈሳዊ ክብር ታገኛለህ::     ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ ✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

​"ጌታ መክሊቱን የሰጠን እንድናተርፍበት እንጂ እንድንቀብረው አይደለም። ማትረፍ ማለት ደግሞ የተሰጠንን ጸጋ ለሌሎች ማካፈል ነው። ካልተጠቀምንበት ግን 'ክፉና ታካች አገልጋይ' ተብለን መጠየቃችን አይቀሬ ነው።"       ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዝናንዙ

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በገብርኄር ሳምንት በተሾምንበት አገልግሎት እንድንታመን በምንማርበት ሰሙን ለሥጋ የሚሆነውን መብል ለማሰናዳት ቢሰየምም፣ እርሱ ግን ቃለ እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እና
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በገብርኄር ሳምንት በተሾምንበት አገልግሎት እንድንታመን በምንማርበት ሰሙን ለሥጋ የሚሆነውን መብል ለማሰናዳት ቢሰየምም፣ እርሱ ግን ቃለ እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እና ጸጋ የነፍስ መብልን ለምእመናን አስተምሮ መክሊቱን ያተረፈውን ንዑድ ክቡር የሚሆን የሰማዕታት መጀመሪያ፣ የዲያቆናት አለቃ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገ ወርሀዊ በዓሉ ነው። ቸር አገልጋይ ማነው? ቅዱስ እስጢፋኖስ አይደለምን? ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

ሰበር ዜና! ውድ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት መዘምራን ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁምጋር ይሁን! የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢና የአርሲ ሀገረ ስብከት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት መምህራችን ዲ/ን አበበ
ሰበር ዜና! ውድ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት መዘምራን ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁምጋር ይሁን! የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢና የአርሲ ሀገረ ስብከት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት መምህራችን ዲ/ን አበበ ይልማ በዛሬው ዕለት በብጹዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅጅጋና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ላዕከ ሔራን ተብለው እንዲጠሩ የማዕረግ ስም ተሰጥቷቸዋል። በዚህም መምህራችን በገብረኄር ሳምንት ውስጥ ባገኙት የማዕረግ ስም የሚጠሩ ሲሆን ላዕከ ሔራን አበበ ይልማ ተብለው ከእንግዲህ የሚጠሩ ይሆናል። ሠናይ ዕለት! ላዕከ ሔራን ማለት ምን ማለት ነው? ይገምቱ ይሸለሙ

"ነፍሳችኹን ተመልከቱ ሰውነታችኹንም ንጹሕ አድርጉ የባልንጀራችኹንም በደል አታስቡ ማንም ከወንድሙ ጋራ በቁጣ እንዳይኖር አስተውሉ።"     የጌታ ቅዳሴ

"ጓደኛህን ስትመርጥ ለነፍስህ የሚጠቅማትን ምረጥ ሥጋዊ ወዳጅነት አላፊ ነውና"    ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰላልዊ

​"የምትገናኘው ማንኛውም ሰው፣ እንዴት ልትጠቀምበት እንደምትችል ካስተዋልክ እግዚአብሔር ለመንፈሳዊ ጥቅምህ ብሎ የላከው ነው። ጻድቁ ሰው መልካም ምሳሌነትንና በረከትን ያካፍልሃል፤ ከክፉው ሰው ደግሞ መጽናትን (ትዕግሥትን)፣ የትዕግሥት ጥበብንና ለሌሎች ይቅርታ ማድረግን ትማራለህ።"      አቡነ ሺኖዳ

ዜና ፍኖተ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨                   በአሰላ ደ/መ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ለቀጣይ 3 ዓመታት ሰንበት ት/ቤቱን የሚመሩ የስራ አመራር ምርጫ ተከናወነ። ምርጫውም ሊቀ ስዩማን ጥበበ ስላሴ የመንበረ ጵጵስና ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ መላእከ ምህረት መሪጌታ ወልደ ሰንበት የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች ተጠሪ መላእከ ሕይወት ቆሞስ አባ ፍቅረ ሥላሴ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል አስተዳዳሪ የካቴደራሉ የሰበካ ጉባኤ አባላት የአርሲ ሀ/ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተወካዮች የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አመራሮች እና አባላት በተገኙበት ፍጹም መንፈሳዊነት በተላበሰ ስርዓት ተከናውኖ ተጠናቋል። አዲስ ለተመረጡት የአመራር አባላት መልካም የሥራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን። ፍኖተ ወንጌልን ከከፍታ ወደ ከፍታ የምታሸጋግሩበት ይሁን። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዚህች እለት በተለይም በአሁንዋ ሰዓት ሁሉም አይኑን ጆሮውን በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ላይ ተክሏል። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨