ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Відкрити в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Показати більше669
Підписники
+124 години
+37 днів
-330 днів
Архів дописів
"እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ መረመረ፤ ነገር ግን እንደ ማርያም ያለች ንጽሕትና ቅድስት አላገኘም፤ ስለዚህም ማደሪያው ትሆን ዘንድ መረጣት።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ። ትርጉም “ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባዋል የማርያም ሞት ግን እጅግ ያስገርማል።የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨ 💿💿💿💿💿💿💿💿💿💿💿
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ እንኳን ለ፹፬ኛ ዓመት የልደት በዓልዎ በሰላምና በጤና አደረስዎ !
ቅዱስነትዎ በመንበረ ፕትርክናዎ ለረጅም ዓመታት በሰላምና በጤና እንዲቆዩ ምኞታችን ነው !
የቅዱስነትዎ ቡራኬ አይለየን !
#ገብርኤል_ሆይ ለሐና ልጅ ለማርያም ደስ የሚያሰኝ ምሥራች እንዳበሠርካት። ለኔም የምጸድቅበትን የምድንበትን የምሥራች አብሥረኝ፡፡ መልካም የምሥራች ማብሠር ለአንተ ክፍልህ ነውና።
ዜና እረፍት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ጥር አሥራ ስምንት በዚህች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ ይድራስ በተሰኘ ተራራ ላይ የተበተነበት የመታሰቢያው ዕለት ነው፡፡
🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ገድሉ የበዛ የተትረፈረፈ ኃያል፤ ተጋዳይ ብርቱ ሰው፤ በተዘረጋ ዙፋን ላይ ኃይልን ያሳየ በሰማይና በምድር መካከል ያለ የማይቆጠር የክብር ኮከብ፤ ተዓምሩ እንደ ባሕር አሸዋ የበዛ የኾነ፤ የፀሐየ ጽድቅ የኢየሱስ ክርስቶስ ሰማዕት ለኾነ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰላምታ ይገባል።"
ተዓምኆ ቅዱሳን
ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለእግዚአብሔር ምሥጋና ይኹን እኛንም በከበረ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር🙏 አሜን።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ወንድሞች ሆይ ሁላችን እንሞታለን። በዚህ ዓለም ሳለን እርስ በርሳችን የማንዋደድ ከሆነ ከባድ ይሆንብናል። ከጠላቶቻችን ጋር ፈጥነን የማንታረቅ ከሆነ ያስቀየምናቸውንም ወገኖች ይቅርታቸውን የማናገኝ ከሆነ አንዱ ሌላውን የሚኮንን ከሆነ ይቅርም ካላልነው ችግር ይፈጠርብናል። በሚመጣውም ዓለም ዘላለማዊ ሕይወትን አናገኝም። ሰማያዊው አባታችን ኃጢአታችንን ይቅር አይለንም።
"ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ"
ይህን ያውቁ ኖሯል?
ከእውነት በላይ እምነት የለም።
ከኦርቶዶክስ በላይ እውነት የለም።
ከሰይጣን በላይ ክፉ የለም።
ከመንግሥተ ሰማያት በላይ ተድላ የለም።
ከገሀነም በላይ መከራ የለም።
ከመስቀል በላይ ሕይወት የለም።
ከኅብረት በላይ ግላዊነት የለም።
ከሐዋርያዊነት በላይ ርቱዕነት የለም።
ከሥላሴ በላይ ምሥጢር የለም።
ከመላእክትና ከሰው በላይ ክቡር ፍጥረት የለም።
ከወንጌል በላይ ሕግ የለም።
" አሁን በሕክምና ላይ ነው ያለሁት ፤ ደህና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን " - ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያለፉት በዓላት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቁ አስተዋጽኦ ለነበራቸው ሁሉ ምስጋናቸውን አቀረቡ፡፡
ቅዱስነታቸው በሸገር ሀገረ ስብከት በኮየ ፈጨ ክፍለ ከተማ በፋንታ መድኃኔዐለም ደብር የከተራ በዓል እለት ሕይወታቸውን ላጡ ኦርቶዶክሳዊያንም ሐዘናቸውን ገልጸዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በክብረ በዓላቱ ያልተገኙት ባጋጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት መሆኑንም ጠቁመው አሁን በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
ቅዱስነታቸው ባለፉት ቅዱሳት የቤተክርስቲያን በዓላት በአካል ባይገኙም ሥነ ስርዓቱቶችን ግን ከአባቶች እና ከመገናኛ ብዙሃን መከታተላቸው አስታውሰዋል፡፡
አያይዘውም " አሁን በሕክምና ላይ ነው ያለሁት ፤ ደህና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን ፤ በሃገር ውስጥም በውጭም ያላችሁ ወገኖቼ በእውነቱ በጣም እንዳሰባችሁ እሰማለሁ፤ ስለ ሐሳባችሁ ስለመጨነቃችሁ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ፤ ሁላችሁም በጸሎት አስቡን ’" ብለዋል፡፡
ቅዱስነታቸው በመጭዎቹ በዓላት ልክ እንደወትሮው ሁሉ አባታዊ ቡራኬ ለመስጠት እግዚአብሔር አምላክ እንደሚያበቃቸው ባለ ሙሉ ተስፋ መሆናቸውንም አመላክተዋል።
©EOTCTV ©tikvahethiopia
"ዘመኔን ሁሉ በኀጢአት ያሳለፍኩት ኀጥእ አባሲ የምሆን እኔን የንስሓ ሥራ እንድጠብቅ አድርገኝ
ታላቁን ታናሹን ኃጢአቴን ይቅር በለኝ በልቡና ሐዘን ወደአንተ ትማልዳለችና በቸርነትህ ሕይወትን ገንዘብ አደረግ ዘንድ።"
ማር ይስሐቅ
"እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው ምንድን ነው? ፍትሕን ታደርግ ዘንድ ምህረትንም ትወድ ዘንድ በአምላክህም ፊት በትህትና ትራመድ ዘንድ አይደለምን ?"
ሚኪ 6÷8
