ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Відкрити в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Показати більше670
Підписники
-224 години
+57 днів
+130 днів
Архів дописів
ሰው ሆይ! ጻድቅ መሆንን ትወዳለህን? አዎን ትለኝ እንደሆነ፥ እንግዲያውስ ለራስህ ንፉግ ለሌላው ግን ቸር ሁን፡፡
🍁️️✨✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️✨✨✨🍁️️🍁️️🍁️️
መልካም ቀን🙏
" ሰው ስለድካሙ ሊወድቅ ይችላል፤ የማይወድቅ ማንም የለምና ይሁን እንጂ አንድ ሰው ንስሐ መግባትና ከውድቀቱ መማር አለበት።" አቡነ ሺኖዳ
መልካም ቀን🙏
ሦስቱ ፈተናዎች የት ይገኛሉ?
ብዙ ጊዜ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳም ተቀብሎ የመለሳቸውን ፈተናዎች በቃል እንጠቅሳቸዋለን እንጂ መገኛ ቦታቸውን ብዙም አንጠቅሰውም።
የስስት መገኛው የት ነው?
የትዕቢት መገኛውስ የት ነው?
የፍቅረ ንዋይ መገኛውስ የት ነው?
አሁንም ድረስ እነዚህ ሦስቱ የኃጢአት ሥሮች ጌታችንን መስሎ ለማይመልሳቸው ተብትበው መያዛቸው አይቀርም።
ሁሉም በሁሉ ቢገኙም በአንዱ ድል የተነሣ በሁሉም ቢነሣም ልዩ ቦታ ግን አላቸው።
[ ] የስስት ቦታው ከመነኮሳት ልቡና ነው።
[ ] የትዕቢት ቦታው ከካህናት ልቡና ነው።
[ ] የፍቅነ ንዋይ ቦታው የሹማምንት ልቡና ነው።
እነዚህ ሦስቱ ብዙ ቅርንጫፍ ልጆች አሏቸው፦ትውዝፍት፣ዝሙት፣ቅንዓት..የመሳሰሉ ዝርዝሮች አሏቸው።
[ ] የትውዝፍት (የምንዝር ጌጥ)ቦታው የሴተች ልቡና ነው።
[ ] የዝሙት ቦታው የጎልማሶች ልቡና ነው።
[ ] የቅንዓት ቦታው የመሪዎች ልቡና ነው።..
እያንዳንዳቸው አንዱ በአንዱ እየገቡ ሥራቸውን ቢሠሩም ይበልጥ የሚጸኑበት ግን በየ ምድባቸው ነው።
ከነ ማደሪያቸው ከተረዳናቸው ሊያድሩብን ሲመጡ እንዴት መመለስ እንዳለብን እንረዳለን ማለት ነው።
👉 ዘወረደ ብለን የጀመርነውን ተነስቷል ብለንም ለማክበር ለማመስገን እግዚአብሔር በሠላም ያድርሰን !!
መልካም ሱባኤ ለሁላችንም 👏
ዘወረደ(ጾመ ሕርቃል)
🙏እንኳን ለዓቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ በሰላም አደረሳችሁ!!🙏
''ጾም የስጋ ረሃብ አደለም የስጋ ልዕልና እና ንፅህና ነው እንጂ'' አቡነ ሽኖዳ
🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹
እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ ስለ ኃጥአን ለምነው ማልደው ይቅርባይ ከሚሆን አምላክ ዘንድ የምሕረትን ቃል ኪዳን ላስገኙ ከናፍሮችሽ ሰላምታ ይገባል ።
🍁️️️️️️ ✨✨✨
የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ ለዕውነተኛዋ ቃል ኪዳንሽ በየክብረ በዓሏ ከገሊላ እስከ ጎልጎታ የተመላለሽበትን የክብር አክሊል በኔ በኃጥኡ አገልጋይሽ ራስ ላይ አቀዳጅኝ
"ጾምን የምንጾመው ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::" ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የዐቢይ ጾምን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ !
የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው መነሻ <<ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡>> በማለት የጌታችንና አምላካችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጾሙን ጥንተ ነገር አውስተዋል።
ቅዱስነታቸው በአርባ ቀናት ውስጥ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዲያቢሎስ መፈተንና ድል መንሳትም አብራርተው ሲያወሱ <<በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤>> ብለዋል።
ቅዱስነታቸው የመጾማችንን ምክንያት ሲያጠይቁ <<...የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ ልዕልና ነው ማለት ነው::... ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን>> ብለዋል።
ስንጾምም <<የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤>> በማለት አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አለምን ዞሬ አየሁትአለምን ዞሬ አየሁት ሁሉን በተራ ቀመስኩት /2/ ፈፅሞ የለም /2/ ሰላም እንደ ልጂሽ ቤት ሀብቴን ንብረቴን ጨረስኩና ጉልበቴ ሁሉ ደከመና /2/ ጎስቋላ ሆንኩኝ /2/ ደካማ የሌለው ጤና ስቃ አሳስቃ ተቀብላ መልኳን አስውባ ተኳኩላ /2/ ዛሬ ጣላችኝ /2/ ይቺ አለም አይረባም ብላ የትላንትናው ወዳጆቼ ዛሬ ሲሆኑ ጠላቶቼ /2/ ባክኜ ቀረሁ /2/ በዓለም ላይ ተንከራትቼ የአባቴ ቤት ሲናፍቀኝ ፍቅሩ ምህረቱ ትዝ ሲለኝ ሁሉንም ትቼ/2/ ድንግል ሆይ ዛሬ መጣሁኝ ልጁም አንድባል ባይገባኝ ባሪያህ እሆን ዘንድ ቢፈቅድልኝ /2/ ጎስቋላ ልጁ ደካማ ልጁ ድንግል ሆይ ዛሬ መጣሁ እናቴ አንቺን ንቄ ትቼ የአባቴን ቤት እረስቼ ተሰቃየሁን ተንከራተትኩኝ ልደሰት ባለም ገብቼ አባቴ ሲያየኝ ተደስቶ ጎረቤቶቹን ሁሉን ጠርቶ ሠርጉን ደገስ /2/ የበደልኩትን ረስቶ እስካሁን ድረስ በድያለው አለም ደና ሁኝ አብቅቻለው ወደ አባቴ ቤት/2/ ዳግመኛ ተመልሻለው መልካም አዳር🙏
በሰማይ ሰልፍ ሆነ ውጊያው ተጀመረ
በሚከኤል ነገድ ሳጥናኤል አፈረ
ያቃጥላል ክንፉ የጠላትን ሰፈር
አያልቅም ቢወራ የሚካኤል ነገር
ዘንዶው ተወርውሮ ከምድር ወደቀ
የቀድሞውም እባብ በክንዱ ደቀቀ
ሚካኤል ሲነሳ ከሳሽ ይሸበራል
በአይለ መስቀሉ ተሰብሮ ተጥሏል
ዳቢሎስ አልቻለም ሚካኤል ፊት መቆም
በተማመነበት በነገዱ አልዳለም
የሰማዩን ስፍራ ለቀቀ ተመቶ
ሳጥናኤል ጨለመ ሚካኤል አብርቶ
የሐሴት አባቷ ዛሬ ስፍራ አቷል
መላካዊው አይሉን በትቢት ተነጥቋል
ሆኗል ምድረ በዳ እጅግ ተቅበዝብዞ
አብረው የወደቁት ነገዶቹን ይዞ
ስሙን እንጠራለን አይሉን እንዲሰጠን
የማሸነፊያውን ክብሩን እንዲያለብሰን
በመንገዳችን ላይ ሚካኤል ስላለ
ሁሉንም አለፍነው በእርሱ እየቀለለ
ቅዱስ ሚካኤል ከሚመጣብን ክፉ ነገር ይጠብቀን🙏
"ኃጢአት አድርጋችሁ ስትጎሰሙ ብትታገሡ፥ ምን ክብር አለበት? ነገር ግን መልካም አድርጋችሁ መከራን ስትቀበሉ ብትታገሡ፥ ይህ ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ምስጋና ይገባዋል። የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።"፩.ጴጥ.፪፥፳
በጅማ ዞን በርካታ ክርስቲያኖች መሰደዳቸውና መኖርያ ቤታቸው መቃጠሉ ተገለጸ !
#Ethiopia | በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ዋላ ቀበሌ ቦሬ ከተማ በሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ በሆኑ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያን አማኞች ላይ ባነጣጠር ጥቃት መኖርያ ቤቶቻቸው እንዲሁም የንግድ ሱቆቻቸውን ጨምሮ ንብረቶቻቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ምንጮች በስልክ ተናግረዋል፡፡
የጥቃቱ መነሻ ምን እንደሆነ እስከ አሁን በውል ባይታወቅም ፤ ጥቃቱ ከትናንትና ወዲያ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በተተኮሰ ጥይት የተጀመረ ሲሆን በቀበሌው የሚገኙ ስምንት አብያተ ክርስቲያናት ከፍተኛ ስጋት ላይ ናቸው ተብሏል።
ጉዳዩን ለማረጋጋት የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሥፍራው ቢገኙም ጥቃቱ እስከ አሁን እንዳልቆመና ወደ ሌላ ቀበሌ እየተዛወረ ነው ተብሏል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ጥቃቱን ሸሽተው ወደ አጎራባች የደቡብ ክልሎች እየሄዱ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
በጅማ ሀገረ ስብከት በአብያተ ክርስቲያናት እና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን ላይ መሰል የእሳት ቃጠሎ አደጋ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያ አለመሆኑ የሚታወስ ነው፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
+• እንደ ፈቃድህ ይሁን •+
ብዙ ጊዜ "ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች፥ እንዲሁም በምድር ትሁን" እያልን እንጸልያለን። ይህንን የምንለው ግን እየጎረበጠን ነው። ደግነቱ ጸሎቱ የአባታችን ሆይ ክፍል ስለሆነ አይዘለልም። ጸሎት ከእምነት ይመነጫል፥ "እንደ ፈቃድህ ይሁን" ማለትም እምነትን ይጠይቃል። እምነታችን ግን ደካማ ስለሆነ ይህንን ጸሎት በሙሉ ልብ ለማለት ይተናነቀናል። በእኛ አስተሳሰብ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መጠየቅ ማለት ያሰብነውን ሁሉ እንዲከለክለን ማመቻቸት እንደሆነ እናስባለን። "ፈቃድህ ይሁን" ብለን ስንጸልይ ቸር አባትነቱን እንረሳና፥ ሁሉን ከልካይ እንጀራ አባት አድርገነው "ይከለክለኝ ይሆን? ያስቀርብኝ ይሆን?" እያልን በሰቀቀን ውስጣችን ይናወጣል። እግዚአብሔር ግን ለልጆቹ መልካም የሆነውን ሁሉ የሚለግስ አባት ነው።
ድሮ በጨዋታ መሃል ሰዎች "እስቲ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" ሲሉኝ እናደድ እንደነበር አስታውሳለሁ። ቃል ገብተው ቃላቸውን ሊያጥፉ፥ ከቀጠሩኝ ቦታም ሊቀሩ እያንገራገሩ ይመስለኝ ነበር። በወቅቱ ለእኔ "እንደ ፈቃዱ ይሁን" ማለት ያለመወሰናቸው ምልክት ነበር። ለካ ጉዳዩ ሌላ ነው። የእግዚአብሔር ቃል "ነገ የሚሆነውን እንኳ አታውቁም። ሕይወታችሁ ምንድን ናት? ለጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት ናችሁ። ይልቁንም፣ “የጌታ ፈቃድ ቢሆን እንኖራለን፤ ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን” ማለት ይገባችኋል።" (ያዕቆብ 4:14-15) ይለናል።
ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ጠይቆ ለመቀበል ከመዘጋጀት፥ የእኛን ፈቃድ ፈርሞ እንዲያጸድቅልን መጠየቅ እንመርጣለን። በዚህ መንገድ የሄድነው አካሄድ ግን ጉዳቱ ብዙ እንደሆነ ለማወቅ ሕይወታችንን መለስ ብሎ ማሰቡ ብቻ በቂ ነው። በራሳችን መንገድ ሄደን ያዋጣናል ያልነው ሲከስር፥ እረፍት ይሰጠናል ያልነው ሲበጠብጥ፥ ያስደስተናል ያልነው ሲያሳዝን፥ ያሳርፈናል ያልነው ሲያቅበዘብዝ አይተናል። በራስ መንገድ የተጓዙት እንደማይበጅ በብዙ ማሳያዎች አረጋግጠናል።
ወገን፥ አይበቃም ወይ? እግዚአብሔርን አምኖ እና እጁን ይዞ "እንደ ፈቀድከው ይሁን" ብሎ መከተል አይሻልም ወይ?
🖋 ፍሬሰንበት አድሓኖም
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
"ይህቺ ጥፊ የኔ ናት"
መነኮስ አባ አርሳንዮስ በገባበት ገዳም ዉስጥ እግዚአብሔርን እያገለገለ ሲኖር አንድ ቀን ከገዳሙ ሕግ ዉጭ የሆነ ነገር ይፈጽማል፡፡ ጥፋቱ ከገዳሙ አበምኔት ይደርስና አበምኔቱ አስበዉ ብገስጸዉ ያፍራል፣ ዝም ብል ጥፋቱ ጥፋት ሳይመስለዉ ሊቀር ነዉ አሉና፡፡ የሱን ረድዕ ጠርተዉ እንዲህ አሉት፡፡ "አርሳንዮስ ያጠፋዉን ጥፋት እኔ እያየሁህ በእርሱ ፊት አንተ አጥፋ ከዛ በጥፊ እመታሃለሁ፡፡ ያኔ እርሱ በአንተ ጥፊ ይማራል አሉት፡፡" እንደተመካከሩት በአርሳንዮስ ፊት ረድኡ የእርሱን ጥፋት አጠፋ አበምኔቱም ተቆጥተዉ በጥፊ መቱት በዚህ ግዜ ነገሩን የተከታተለዉ አርሳንዮስም "ይህች ጥፊ የኔ ናት" ብሎ ተናገረ፡፡
እግዚአብሔር እኛን ባጠፋነዉ ቅጣት የግድ እስከሚቀጣን ቁጭ ብለን መጠበቅ የለብንም ፣ከሌላዉ ጥፋት፣ ከሌላዉ ቅጣት መማር አለብን፡፡ ከሌላዉ ጥፋት መማር ትልቅ ዕዉቀት፣ ታላቅ ማስተዋል ነዉ፡፡ አርሳንዮስ ጓደኛዉ በጥፊ ሲመታ፣ ይች ጥፊ የኔ ናት አለ እንጂ ባጠፋዉ ጥፋት ነዉ የተቀጣዉ ብሎ አልፈረደበትም፡፡ እኛም ቁጣ፣ መቅሰፍት፣ እኛ ጋር እስኪመጣ መጠበቅ የለብንም ከጓደኞቻችን ከጎረቤቶቻችን በሌላም ሀገር ከምናየዉ ከምንሰማዉ ተምረን ንስሓ መግባት አለብን ጾም ማለትም ይህ ነዉ፡፡ ንስሐ የምንገባዉም ኃጢአታችንን ስናስተዉል ነዉ፡፡ ማስተዋል ከሌለን ኃጢአቱን እንደ ጽድቅ ቆጥረን ለንስሐ አንበቃም፡፡
ማስተዋልን ገንዘብ ያደረገ ምዕመን በሌላ ላይ የተደረገ ቅጣት በርሱ ላይ እንደመጣ ይጠነቀቃል፡፡ እንደ ርግብ የዋህ እንደ እባብ ብልህ በመሆን የነገሮችን ሁኔታ በማስተዋል ይከታተላል፡፡ ከሰብአ ትካት ከሰዶም ይማራል ሎጥ የዳነበትን መንገድ ይከተላል ቃሉን በመስማት በኖህ መርከብ በተመሰለች ቅድስት ቤተክርስቲያን ይገኛል እራሱን በንስሐ በሥጋ ወደሙ በጸሎት በእግዚአብሔር ቸርነት ከሚመጣዉ መቅሰፍት ያድናል፡፡
የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡
“ሃሎ መምህር” የተሰኘ ለሃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ምላሽ የሚሰጥ አገልግሎት መጀመሩ ተገለጸ።
የካቲት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት “ሃሎ መምህር” የተሰኘ ለሃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ምላሽ የሚሰጥ አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል።
የስብከተ ወንጌልና ዕቅበተ እምነት ዋና ክፍል ምክትል ኃላፊ ዲያቆን ዐቢይ ጌታሁን እንደገለጹት አገልግሎቱ በዋናነት የስብከተ ወንጌልን ተልዕኮ ለማዳረስ በተለይ በቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ምዕመናንን በእምነታቸው እንዲጸኑ ለማድረግና ከአዳዲሰ አማንያን የሚመጡ ጥያቄዎችን ለመመለስ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
ከተጀመረ 5 ቀን የሆነው ይህ አገልግሎት ከ 30 እስከ 40 ለሚሆኑ ምዕመናን ለጠየቋቸው ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠቱን በመግለጽ ሰዓቱን ያልጠበቁ የስልክ ጥሪዎችን ለማስተናገድ ፈተና እንደሆነባቸው አክለው ገልጸዋል።
በዚህም ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 4፡00 - 10፡00 ሰዓት አገልግሎቱ የሚሰጥ ሲሆን ሰኞ፣ ረቡዕና ዓርብ በኦሮምኛና በአማርኛ እንዲሁም ማክሰኞና ዓርብ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ም/ኃላፊው የምዕመናን ተሳትፎ ጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው “በተለያየ ምክንያት መማር ያልቻሉ፣ ጥያቄ የፈጠረባቸውና በአካል መገኘት ለማይችሉ ምዕመናን በያሉበት ስልክ በመደወል ጥያቄዎችን በመጠየቅ ምላሽ ማግኘት ቢችሉ ከሃይማኖት እንዳይወጡና ከቤተ ክርስቲያን እንዳይለዩ ይረዳቸዋል” በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
#ወር_በገባ_በ6_ሰማዕቷ_ቅድስት_አርሴማ_ናት፡፡
#በጨንቃችሁ_ጊዜ_ሁሉ_እናቴ_ቅድስት_አርሴማ አለው_ትበላችሁ።
#ወቶ_ከመቅረት_ካልታሰበ_አደጋ_ከክፉ_ነገር #ሁሉ_ትሰውረን።
🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
✨ይቅርታ ማድረግ ተሸናፈነት አይደለም አሸናፈው እግዚአብሔር በመስቀል ላይ ሆኖ ይቅርታን ያደረገውም ኃይል አጥቶ አልነበረም፡፡ ሁሉንም ስለ ድፍረታቸውና ንቀታቸው በቅጽበት ሊያጠፋቸው ይቻለው ነበረ እንደ ባብሎን ስዎች ሰቃዮቹን በቋንቋ እንዳይግባቡ ማድረግም ይችል ነበረ፡፡ እርሱ እንኳን. ባያደርገው በድንጋጤና በመደመም ፈዘው የሚመለከቱትን የሰማይ ኃይላት ቅዱሳን መላእክቱን ሊያዛቸው ይችል ነበረ
"ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን? " ማቴ 26: 53እንዳለው ወደ አባቱ "ይቅር በላቸው" ብሎ በመለመን ፈንታ ለጥፋት የታዘዙ መላእክትን መጥራት ይችል ነበረ፡፡ በእርግጥ በመስቀሉ ዙሪያ ያሉ ጠላቶቹን ለማጥፋት የመላእክት ጭፍራ አያስፈልግም አንዱ መላአክ ቅዱስ ሚካኤል መቶ ሰማንያ አምስት ሽህ የሰናክሬምን ሠራዊት ሰይፍ እንኳን ሳይመዝዝ በግርማው ብቻ እንደ ቆሎ አርግፎአቸው እንደነበር አይረሳም (2ኛ ነገሥ 19:35)የሚካኤል ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሠራዊተ መላእክቱ በዚያች ዕለት እንዲዘምቱ አልወደደም፡፡ በዚህ ምክንያት ያቺ ዕለት ለመላእክቱ አስጨናቂ ዕለት ነበረች፡፡ 📚ሕማማት 📝ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ 🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው። አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደኅንነት በሚሰማህ አሳቻ ሰዓት ሳታውቀው ይዘርፈሀል፤ ይገድልህማል። "
🍁️️✨✨ቅዱስ ጎርጎርዮስ
