ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Відкрити в Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Показати більше669
Підписники
-224 години
+57 днів
+130 днів
Архів дописів
"
ኃጢአት ሲሠራ ባየኸው ወንድም ላይ አትፍረድ፥ አንተ ግልጽ የወጣ ኃጢአቱን እንጅ በስውር ለካህን የሚነግረውን ንስሐ አታውቅምና። ስለዚህ የራስህን ድካም ተመልከት።"ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“... እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ ከመጀመሬ በፊት ስለ ጢሞቴዎስ የተጋድሎ ሕይወት እና ስለ ጳውሎስ አባታዊ የፍቅር አሳቢነቱና እንክብካቤው ትንሽ ነገር እንድል ፍቀዱልኝ፡፡ እንደዚያ ባሉ ብዙ አስቸጋሪና ፋታ በሚነሱ ሁኔታዎች ውስጥና ሩቅ ከሆነ ቦታ ላይ ሆኖ እያለ እንኳ ስለ ደቀ መዝሙሩ ጤና ያን ያህል እንደሚያስበውና እንደሚጨነቀው፣ እናም የጤናው ችግር የሚስተካከልበትን ነገር እንደ ጻፈው እንደዚህ አባት ያለ ርህሩኅና አሳቢ ማን አለ? የጢሞቴዎስን የተጋድሎ ሕይወት የሚያህልስ ምን አለ? ከትህርምቱ ጽናትና ከጾሙ ብዛት የተነሣ ሕመም ላይ እስከሚወድቅ ድረስ ድሎትንና ተድላ ሥጋን ናቀ፡ የላመና የጣመ ምግብ ያለበትን ማእድ ከእርሱ አራቀ፡፡ ጳውሎስ ያለው ትንሽ ወይን ጠጣ' ብቻ ሳይሆን አስቀድሞ ወደ ፊት ውኃ ብቻ አትጠጣ ካለው በኋላ ነው ወይን እንዲጠጣ የመከረው፡፡ ይህ 'ወደ ፊት ውኃ ብቻ አትጠጣ' የሚለው አባባል እስከዚያ ጊዜ ድረስ የሚጠጣው ውኃ ብቻ የነበረ መሆኑንና ከዚህም ከትህርምት ብዛት የተነሣ ሆዱ መታመሙን የሚያሳይ ነውና፡፡ . . . "(ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፣ ክፍለ ትምሀርት 1፣ ቁ. ) ✨✨✨🍂🌿🍂
የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ባስልዮስን ስድስተኛው የቤተክርስቲያኒቱ ፓትርያርክ አድርጋ መረጠች !
ኅዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
+9
ፎቶ ፦ ትላንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በቻይና ምድር የመጀመሪያዋን ደብር በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ አከናውናለች።
ለሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና እንደሚገኙት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና ምድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምዕምናንን አቁርበዋል።
በቻይና የመጀመሪያው አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም ሾመዋል።
ከቻይና ክፍላተ ግዛቶች የተሰባሰቡ ምዕመናን ፣ ቻይናውያንና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ተሳፍተዋል።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
+8
“ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።”
— መዝሙር 133፥1
የመጀመሪያ ዙር የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መርሀ ግብር
የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አድነት የቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ያጋሩ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/ardssu👈
👉https://t.me/ardssu 👈
👉 https://t.me/ardssu👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
“ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።”
— መዝሙር 133፥1
የመጀመሪያ ዙር የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መርሀ ግብር
የአርሲ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አድነት የቴሌግራም ቻናልን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ያጋሩ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/ardssu👈
👉https://t.me/ardssu 👈
👉 https://t.me/ardssu👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
Repost from የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
“ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።” መዝ ፻፴፫፥፩ልዩ መርሐ-ግብር በኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጀው ልዩ መርሐግብር እሁድ ህዳር 29 ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በአሰላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አዳራሽ በአሰላ ከተማ የሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች የተሳተፉበት እንዲሁም የሚታደሙበት ልዩ መርሐ-ግብር። በዕለቱ > ቃለ ወንጌል በተጋባዥ መምህራን > ልዩ ልዩ ዝማሬ በአንድነቱ ዘማሪያን > የኪነጥበብ ዝግጅቶች ሁሉም ሰ/ት/ቤቶች በዕለቱ ጸዲቅ ይዘው ከየአድባራቱ ይጎርፋሉ እርሶም መጥተው የመርሐ ግብሩ ተካፋይ ይሁኑ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለመቀላቀል 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 👉 https://t.me/ardssu👈 👉https://t.me/ardssu 👈 👉 https://t.me/ardssu👈 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
በመብልና በሆዳምነት የዛገውንና የደነዘውን ሰውነትህን በጾም ሳለው፡ ወልውለው ሰንግለው'' ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚወስደውን መንገድ ያዝ መንገዱ ጠባብና የማይመች ቢሆንም አንተ ግን በዚህ መንገድ ለመሄድ ምረጥና ተጓዝበት፡፡ ይህን ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው? ሰውነትህን በማስገዛትና በቁጥጥር ስር እንዲውልና እንዲገዛ በማድረግ ነው፡፡ መብልና ሆዳምነት ትልቅ መሰናክል ናቸውና፡፡ በዚህ ሁሉ የሕይወት ተጋድለ ጾም ታላቅ መሠረትና መምህር ሆኖ ያገለግለናልና”(ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ትምሀርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት 3 ቁ. 7) ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“በጣም ከዓቅማችሁ በላይ የሆኑ ምሳሌዎችን መከተል ምን ያደርግላችኋል? በምግባር ስትሰማሩ በዓቅማችሁ መጠን እንጂ ለራሳችሁ ታደርጓቸው ዘንድ የማይመከሩና ከዓቅማችሁ በላይ የሆኑ ነገሮችን ባታደርጉ መልካም ነው፡፡ በአፈጻጸም ደረጃ በወንጌል የተፈጸሙ ታሪኮች ዛሬ አፈጻጸማቸው ከዚያን ጊዜው ለየት ያሉ ነገሮች አሉና፡፡ ለአብነትም ክርስቶስ የጾመው ከመፈተኑ ጥቂት አስቀድሞ ነበር፣ እኛ ደግሞ ከትንሣኤ በፊት እንጾማለን፡፡ የጾመን የጊዜ ርዝመት በተመለከተ ቀናቱ ያው [አርባ ቀናት] ናቸው፣ የጾሙን ዘመን በተመለከተ ግን ልዩነት አለ፡፡ ለእኛ ጾመ ከክርስቶስ ጋር ለመሞታችን አምሳል ነው፣ ጾማችን ራሳችንን ለትንሣኤው በዓል ለማዘጋጀት የምናነጻበትና የምንቀድስበት መሣሪያ ነው፡፡ እንዲሁም ጌታችን ለአርባ ቀናት በተከታታይ ጾመ፣ እርሱ እግዚአብሔር ነውና፡፡ እኛ ግን ስንጾም በተከታታይ ሳይሆን እስከ ተወሰነ ሰዓት እየጾምን እንደ ዓቅማችን መጠን እናደርጋለን፤ ምንም እንኳ አንዳንዶች ለጾም ካላቸው ልዩ ፍቅርና ቅንዓት የተነሣ ጾማቸውን ረዘም ላሉ ሰዓታትና ቀናት ቢያራዝሙም፡፡ እንደ ገናም ለደቀ መዛሙርቱ ምሥጢረ ቁርባንን የሰጣቸው በደርብ ፎቅ ላይና ከራት በኋላ፣ ከስቅለቱ አንድ ቀን አስቀድሞ ነበር፡፡ እኛ ግን ምሥጢረ ቁርባንን የምንፈጽመው በቤተ ክርስቲያን፡ ከምግብ በፊት እና ከትንሣኤ በኋላ ነው፡፡ እርሱ ያደረጋቸው ነገሮች ከእኛና እኛ ከምናደርጋቸው የተለዩ አይደሉም፡ ሆኖም ግን አፈጻጸማቸውን በተመለከተ ከጊዜና ከሁኔታዎች ጋር ፍጹም የሆነ ተመሳሳይነትናአንድነት የሌለባቸው ነገሮች አሉ ሆኖም ለእኛ የተላለፉልን ማድረግና መፈጸም ለሚገባን ነገሮች አርአያና መሠረት እንዲሆኑን ነው፡፡(ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ ትምህርት በእንተ ጥምቀት፡ ቁ. 30) ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
አመጋገብን በተመለከተ የምትከተሉት መመሪያችሁ ይህ ይሁን፣ በጾም ጊዜ ከሚመገቡት የምግብ ዓይነት የተነሣም ብዙዎች ይሰናከላሉና፡፡ .
... ከሥጋና ከወይን በመከልከልና እነዚህን በመተው የምንጾመው የረከሱ ነገሮች ናቸው ብለን በመጸየፍ አይደለም፤ ነገር ግን እነዚህን የሚታዩትን ቁሳዊ ነገሮች በመናቅና በመተው መንፈሳዊና ሰማያዊ ተድላ ደስታን እናገኝ ዘንድ ተስፋ በማድረግ ነው እንጂ በጾማችን ሥጋንና ወይንን የምንተወው ሰማያዊ ዋጋን ከእግዚአብሔር ዘንድ እናገኝ ዘንድ ተስፋ ስለምናደርግ ነው፣ በለቅሶ ዘርተን በደስታ እናጭድ ዘንድ ነው እንጂ መዝ. 125፡5 ... ከእነዚህ ነገሮች ራሳችሁን ስትከለክሉና ስትታቀቡ የተጠና የረከሱ ነገሮች እንደሆኑ አድርጋችሁ አስባችሁ መሆን የለበትም እንደዚህ የምታስቡ ከሆነ ጾማችሁ ምንም ዋጋ የለውም፡፡ ነገር ግን ሥጋና ወይን በተፈጥሯቸው መልካም ነገሮች ቢሆኑም በፊትህ ስለ ተዘጋጁልህ የበለጡ መንፈሳዊ ነገሮች ስትል በጾም ጊዜ እነርሱን ተዋቸው፡፡"ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም፡ ትምህርት 4 ቁ. 27 ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“ቅዱስ ያዕቆብ እኁሁ ለእግዚእነ የጌታችንን ጽዋ ከጠጣበትና ቅዱስ ሥጋውን ከበላበት ከጸሎተ ሐሙስ ማታ አንሥቶ ጌታችንን ከሞት ተነሥቶ እስኪያየው (እስከ ትንሣኤው) ድረስ ምንም ነገር እንደማይቀምስ ለራሱ ቃል ገባ፡፡ ስለዚህም መድኃኒታችን እንደ ተነሣ ወዲያውኑ ለያዕቆብ ተገለጠለትና እንዲመገብ አዘዘው፡፡ 1 ቆሮ. 15፡8”📝ቅዱስ ጄሮም ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨
"ታቦተ ሕጉ ለእግዚአብሔር በካህናት ሕጽርት ወበመንፈስ ቅዱስ ክልልት ንጉሥኪ ጽዮን ኢትመዋዕ ለፀር ወኢየኃድጋ ለሀገር"።ትርጉም፦ የእግዚአብሔር ታቦት ሕግ በካህናት የታጠረች ናት ጽዮንን ንጉሥሽ በጠላት አይሸነፍም ሀገርንም አሳልፎ አይሰጥም። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ ✨✨✨
ሁላችሁም ምርጫዎቻችሁን አስቀምጡ።
ጥያቄ:- የአእላፋት ዝማሬ በአሰላ ከተማ በአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ይዘጋጅ?
ሁላችሁም ምርጫዎቻችሁን አሰቀጥጡ።
ጥያቄ :- የአእላፋት ዝማሬ በአሰላ ከተማ በአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ይዘጋጅ?
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
ራሳችንን ፍሬ በሌለው መንገድ በከንቱ እንዳናደክም ጥቂት ነገሮችን እንበል፡፡ በርግጥ አሁን የምታደርጉት ነገር - ጾማችሁና መሬት ላይ መተኛታችሁ - በጣም የተመሰገነ ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ከእነዚህ ጋር ሌሎች በጾም ጊዜ ሊፈጸሙ የሚገባቸው ተግባራት ካልተጨመሩ በስተቀር ከጾም የምናገኘውን ዋጋ ያሳጡናል፡፡ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንዴት ይቅር እንደሚል አሳይቶናል፡፡ በጥንት ዘመን የነነዌ ሰዎች ኃጢአትን ባደረጉ ጊዜ በኃጢአት ቁስላቸው ላይ ጽኑ የሆነ የጾምን መድኃኒት አደረጉ፡፡ መሬት ላይ በመተኛት ማቅና ዓመድ ለበሱ፣ ለቅሶንና ሐዘንን በኃጢአት ቁስላቸው ላይ መድኃኒት አድርገው አፈሰሱ፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከዚህ ሁሉ ጋር ደግሞ ሕይወታቸውን ከክፉ ወደ መልካም ለወጡ፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር እግዚአብሔር በምን ምክንያት እንደ ማራቸው ሲናገር እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ ሥራቸውን አየ፣እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም' ይላል። ዮና 3፡10 ስለዚህ ከመጾም ጋር ከክፉ መመለስንና ከክፉ ነገር መጾምንም እንፈጽም ዘንድ መዘንጋት የለብንም፡፡"📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ ቆሮንቶስ ቀዳማዊ፣ ክፍለ ትምህርት 4፣ ቁ. 6 ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
ጾም ምን እንደሚያደርግ ተመልክት፤ ደዌን ይፈውሳል፡ አጋንንትን ያባርራቸዋል፣ ክፉ ሃሳቦችን ያስወግዳቸዋል፡ ልብን ንጹሕ ያደርጋል፡፡ በርኩስ መንፈስ የተያዘ ሰው እንኳ ቢኖር በጌታ ቃል መሠረት እንዲህ ያለው መንፈስ ያለ ጾምና ጸሎት በስተቀር እንማይጠጣ ይወቅ, ማቴ. 17-21📝ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨🍂🌿🍂
✨✨✨ የቀጠለ ...
✨ጾም በቅዱሳን አባቶች ትምህርት ✨
ስለ ጾም ጠቃሚነትና አስፈላጊነት፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ሰማያዊ ዋጋ ያለው ስለ መሆኑ፣ በጾም ጊዜ
የእንስሳት ተዋጽኦዎች (ዓሣን ጨምሮ) እንደማይበሉ፣ እና በመሳሰሉት ጾምን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ
ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምረዋል፡፡
“በጾማችን የነፍሳችንን ክፉ ልማዶች ካላስወገድን ከሥጋ መከልከላችን ብቻውን ምን ይጠቅመናል? ስንጾም ውለን ጾም ከመግባቱ በፊት እንመገበው የነበረውን ምግብ ለውጠን መናኛ የሆነ የጾም ምግብ በማዕዳችን አቀረብን፡ ሆኖም ግን በጸሙ የምንመገበውን ምግብ እንደ ለወጥን ክፉ ግብራችንን እና ሕይወታችንንስ አብረን ለውጠናል ይሆን? በእውነት እኔ ግን እንዲህ ያደረጋችሁ አልመሰለኝም፡፡ እንዲህ ከሆነ መጾማችሁ ጥቅሙ ምንድን ነው? ስለዚህ ከጾማችሁ ጋር ልማዳችሁንና ሕይወታችሁን ወደ መልካምነት ትቀይሩ ዘንድ በተከታታይ እንድታስቡበት አደርጋችሁ ዘንድ ስለዚህ ነገር እናንተን ማስተማርንና መገሠጽን አላቋርጥም፡፡ በጾማቸው መንፈሳዊ ፉክክር የሚፎካከሩ እንዳሉ ሁሉ በዚህም አስደናቂ የሆነ ተጋድሎን የሚጋደሉ እንዳሉ ሁሉ፡ ሁለት ሙሉ ቀናትን በተከታታይ ምንም ነገር ሳይቀምሱ የሚጾሙ አንዳንዶች አሉና፡፡ ሌሎች ደግሞ በጾም ጊዜ ወይን እና ዘይትን መተው ብቻ ሳይሆን ሌላውን ነገር ሁሉ ትተው መላውን ዐቢይ ጾም በደረቅ ዳቦና በውኃ ብቻ የሚጸ አሉና፡ . . .📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ 📚ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት 4 ቁ 12 ✨✨✨🍂🌿🍂
