uk
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Відкрити в Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Показати більше
672
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
-130 днів
Архів дописів
በአሰላ ደብረ ሣህል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን የአባታችን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ አመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በታህሣስ 11 በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

✨✨✨ታህሳስ 28 እንገናኝ✨✨✨
✨✨✨ታህሳስ 28 እንገናኝ✨✨✨

"መብላትና መጠጣት ብቻውን ጓደኝነት አይስብለውም፣እንዲህ ዓይነቱ ጓደኝነትማ ዘራፊዎች እና ነፍሰ ገዳዮች እንኳ አላቸው። ነገር ግን ወዳጆች ከሆንን፣ እርስ በርሳችን ከልብ የምንተሳሰብ ከሆነ፣ እርስ በርሳችን በመንፈሳዊነት የምንረዳዳ፣ ጓደኞቻችንን ወደ ገሃነም የሚወስዱ እንቅፋት አናድርገው።       ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

የአባታችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶ የንግስ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
የአባታችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶ የንግስ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ እናቱ ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐ
አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ እናቱ ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለ #አብ ስብሐት ለ #ወልድ ስብሐት ለ #መንፈስ_ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል፡፡ የስማቸው ትርጓሜ የ #አብ#ወልድ#መንፈስ_ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የ #ክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ #ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ #አቤቱ_አለምን ኹሉ የምትገዛ የአባቶቻችን የአብርሃምና የይሥሐቅ የያዕቆብ የጻድቃን ልጆች ኹሉ  #አምላክ_ቸሩ_መድኅኔ_ሆይ!  ቸርነትህና ምኅረትህ ፤መግቦትህና ፤ጠብቆትህ ለዘላለሙ  ፤በልጆችህና በልጅ ልጃቸው ይኹን ስለምታደርግልኝ ሁሉ ለዘለአለም አመሰግን አለኹ።
የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

Profile , History በማድረግ ለሁሉም የከተማችን ምዕመናን እንዲደርስ መልዕክቱ አስተዋጽኦ እናድርግ። የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/Finote
+2
Profile , History በማድረግ ለሁሉም የከተማችን ምዕመናን እንዲደርስ መልዕክቱ አስተዋጽኦ እናድርግ። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

Profile , History በማድረግ ለሁሉም የከተማችን ምዕመናን እንዲደርስ መልዕክቱ አስተዋጽኦ እናድርግ።
+2
Profile , History በማድረግ ለሁሉም የከተማችን ምዕመናን እንዲደርስ መልዕክቱ አስተዋጽኦ እናድርግ።

✨✨✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿 "እግዚአብሔርን 'ለምን አልሰጠኸኝም?' ብለህ አትጠይቀው፤ ይልቅስ 'እንደ አንተ ፈቃድ ይሁን' በለው። እርሱ ለአንተ የሚጠቅምህን ከአንተ በተሻለ ያውቃልና።"                   ✨✨ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
"አእምሮህ በጸሎት ጊዜ ሲበተን አትውቀሰው ይልቅስ እንደ አዲሰ ወታደር መልሰህ ወደ ሰልፍ አስገባው።"
                   ✨✨ ቴዎፋን ዘሬክሉስ “አንተ ሰው የበደለህን ይቅር ሳትል ወደ ጾም አትግባ፡፡ አንተን በበደለህ ሰው ላይ በቁጣ እያለህ የምትጾመው ጾም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርም አይቀበለውም፡፡ ጾምህን በፍቅርና እርሱን ተስፋ በማድረግ በእምነት ካላደረግኸው አንተን ፈጽሞ ሊረዳህ አይችልም፡፡ በጠብ ሆኖና በውስጡ ጠላትነትን አንግሦ የሚጾም ጸዋሚ እግዚአብሔርን ይጠላዋል፤ ከመዳንም ፈጽሞ የራቀ ነው፡፡"                        ✨✨ ቅዱስ ኤፍሬም
"እጅግ ምርጡ ጸሎት 'ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ የፈቀድከውን አድርግልኝ።' ማለት ነው።"
                       ✨✨ ባሕታዊ ቴዎፋን ጠዋት ከእንቅልፍህ ተነስተህ ሥራህን ከመጀመርህ በፊት የእግዚአብሔር ቃል አጥና። አንተ የእግዚአብሔር ቃል የዘውትር ወዳጅህ አድርገህ የምትይዘው ከሆንህ በዓለማዊ ነገሮች ባተሌ አትሆንም፥ አትታወክም፥ ኃጢአት አትሠራም ።                       ✨✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ✨✨✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜ እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።🙏 💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐
⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜⚜⚜🔱🔱🔱⚜ እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።🙏 💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐 ✨ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተመረጡ የተመረጠች፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእናቷ ከቅድስት ሐናና ከአባቷ ቅዱስ ኢያቄም በእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ከተወለደችበት ዕለት ግንቦት ፩ ቀን ጀምሮ በወላጆቿ ቤት ለሦስት ዓመት ከኖረች በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ‹‹በዓታ ለማርያም›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡: ✨ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ‹‹ልጄ ሆይ ስሚ እይ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን የአባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ ክርስቶስ ውበትሽን /ንጽሐ ባሕርይሽን/ ወድዷልና›› መዝ 44፡10-11 ብሎ እንደተናገረ ለወላጆቿ የብጽአት ልጅ የሆነችው ድንግል ማርያም  ከእናት ከአባቷ ተለይታ ታህሣሥ ፫ ቀን በ ፫ ዓመቷ ወደ መቅደሰ ኦሪት ገብታለች፡፡ 💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐 ለአባ ሕርያቆስ፣ ለቅዱስ ኤፍሬም፣ ለቅዱስ ያሬድና  ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን🤲 አሜን ለበላኤ ሰብዕ የተለመች እመ አምላክ ለኛም ትለመነን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን። 🤲 አሜን! የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

✨✨✨✨ኑ በደጁ እንሰባሰብ!✨✨✨✨ የፊታችን ታህሣስ 5 እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ለከተማችን የጥምቀት በዓል አገልጋይ ወጣቶች ልዩ መርሐግብር ተዘጋጅቶ ይጠብቃቹሀ
✨✨✨ኑ በደጁ እንሰባሰብ!✨✨✨✨ የፊታችን ታህሣስ 5 እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ለከተማችን የጥምቀት በዓል አገልጋይ ወጣቶች ልዩ መርሐግብር ተዘጋጅቶ ይጠብቃቹሀል። ስለሆነም ከዚህ በፊት ጥምቀት በዓል ላይ ምንጣፍ በማንጠፍ ፣ በመሸከም፣ በመጠቅለል፣ በማስተባበር እና በልዩ ልዩ አገልግሎት ያገለገላችሁ እንቁ የደብረ መድኃኒት ወጣቶች እንዲሁም ዘንድሮ ማገልገል የምትፈልጉ የከተማችን ወጣቶች በዕለቱ እንድትገኙ ስንል ጥሪያችንን በቸሩ መድኃኔዓለም ስም እናስተላልፋለን። ✨✨ ቸር ያገናኘን🙏✨✨

ከፍቅር የተነሣ ጋሼ ከማለት በቀር በአንቱታ የማንጠራው በኵረ መዘምራን ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሙሉ ዕድሜውን ሠውቶአል:: ከወልቂጤ እስከ ወሊሶ ፣ ከወሊሶ እስከ አሰላ ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ፒተርስበርግ ፣ ከሞስኮ እስከ ሀንጋሪ ከዚያም በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ክፍለ ሀገራት ዞሮ የቤተ ክርስቲያን ድምፅ ሆኗል:: የቅዳሴ ያህል ተከብሮ በሚሰማው ዝማሬው የያሬዳዊ ዜማን ጣዕም አማርኛ ብቻ ለሚሰሙ ምእመናን ማቅመስ ችሏል:: ኪነ ጥበብ ከማሕሌታውያን መሪጌቶች እስከ ቀዳስያን ካህናት ፣ ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እስከ ዲያቆናት ፣ ከሰባክያን እስከ ዘማርያን ሁሉም መርጦ የሚያነሣው የመዝሙር ማዕድ አለው:: ቀሳውስት "ወገዳምኒ ገዳምኒ አንትሙ" ሲላቸው ሰምተው በትካዜ ይዋጣሉ ፣ መሪጌቶች "ያንተ ሥራን" ሲሰሙ "ይኼ እኮ ቀጥታ ዝማሬ ላይ ያለ ዜማ ነው!" ይላሉ ፣ ሰንበት ተማሪዎች ኪነ ጥበብ ዜማውን የደረሰውና የዘመረውን  "ደስ ይበለን እልል በሉ አልቀረም ተቀብሮ ተገኘ መስቀሉ" ሲሰሙና ሲዘምሩ ነፍስ አይቀርላቸውም:: ጾም የገባ እንደሆን "እኔስ በምግባሬ" እና "ድንግል ወላዲተ ቃል"ን ማን ይረሳል:: አስቀዳሽ ምእመናን ደግሞ "ይህ ቁርባን ክቡር ነው" እያሉ የኪነን መዝሙር ይዘምራሉ:: ቤተ ክርስቲያንን በሩቅ የሚያውቃት እና አልፎ አልፎ የሚሳለም ምእመን እንኳን "እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን" በሚለው የኪነ ጥበብ ዝማሬ በንስሐ ዕንባ ሳይታጠብ አልቀረም:: ኪነ ጥበብ ተወዳጅ ቀዳሽ ዲያቆን ፣ የመንፈሳዊ ኮሌጅ ትጉሕ ተማሪ ፣ ቤተ ክርስቲያን ውጪ ተማር ብላ ስትልከው የቁራ መልእክተኛ ሳይሆን በአግባቡ ተምሮ የተመለሰ ፣ ለደረጃው የማይመጥን ሥራ ሲሠጠው አክብሮ የሠራ ፣ ቤተ ክርስቲያንን ከሰዎች ለይቶ በማየት ብዙ በደል ተቋቁሞ ተገፍቶ የኖረ ፣ ሰንበት ትምህርት ቤት በማደራጀት የጉባኤ መልክ በማስያዝ ብዙ የደከመ ፣ በመዝሙሩ ምክንያት በኮሚኒስት መንግሥት የታሰረ ፣ የቤተ ክርስቲያንን ዜማ በማክበሩ ቤተ ክርስቲያንን በማያውቁ ሰዎች የተናቀ ፣ የቤተክርስቲያን ነገር የእግር እሳት ሆኖ የሚያንገበግበው ብሶተኛ ፣ ብዙ ሠርቶ ምንም እንዳልሠራ በቁጭት የሚነድድ የቤተ ክርስቲያን ክብር ነው:: ኪነ ጥበብ ለቤተ ክርስቲያን ላሳለፈቻቸው ውጣ ውረድ የተሞሉ የመከራ ዓመታት የማጀቢያ ድምፅ ሆኖ አገልግሏል:: ወደ መድረክ የሚወጣው ለመታየት ሳይሆን ፈጣሪውን ለማሳየት ነው:: በስድስት ክንፋቸው ራሳቸው ሸፍነው እንደሚዘምሩት ሱራፌል በስድስት ዐሠርት ዓመታት ውስጥ ራሱን ደብቆ የዘመረው የዝማሬ ማኅቶት ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ ነው::  መብራትን አብርቶ ከዕንቅብ በታች ማኖር ስለማይገባ የኪነ ጥበብን ውለታ ለማውሳትና ለትውልዶች ላደረገው ታላቅ አበርክቶ እናመሰግናለን ለማለት እጥፍ ክብር ማሳያ ልዩ ዝግጅት ስናሰናዳ ስድስት ወራትን አሳልፈናል:: በርካታ መምህራን የተሳተፉበት ኪነ ጥበብ የተሰኘ ዶክሜንታሪ ፊልም በሲኒማቲክ ስክሪን ይታያል:: ኪነ ጥበብ የተሰኘ መጽሔት ይመረቃል:: የአገልግሎት አቻዎቹና ልጆቹ በተገኙበት በሚደረገው የማክበሪያ ዝግጅት ላይ ብዙ ኪነ ጥበባዊ ጉዳዮችም ይፋ ይሆናሉ:: የኪነ ጥበብ ውለታ ያለባችሁ እናመሰግናለን ለማለት የምትፈልጉ ሁሉ ከቦታ ውስንነት አንጻር ነገ እኩለ ቀን ላይ እዚሁ ገጽ ላይ በምናስቀምጠው መመዝገቢያ ተመዝግባችሁ ታደሙ:: ኪነ ጥበብ ሆይ እጥፍ ክብር ይገባሃል የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም.

ሞኝ ሰው እንዲ ብሎ ይጸልያል የሚያሳድዱኝን አሳዳቸው ክፉ የዋሉብኝን ክፉ ዋልባቸው እድሌን የዘጉትን እድላቸውን ዝጋባችው መንገዴን የዘጉትን መንገዳቸውን ዝጋባቸው ይላል ብልጥ ግን በተቃራኒው ምቀኛዬን አበርታው ቀናተኛዬን አጽናው መንገዴን ለሚዘጋው ጉልበት ሁነው ለሚጨክንብኝ ሀይልን ስጠው ተንኮል ለሚያስብብኝ መንገዱን አሳየው ለጠላቴ ቀን አውጣለት ግን የኔ ጌታ ጠላቶቼ ሲነሱ የምመክትበት ብርታት ስጠኝ የማሸንፍበት አንተ ጉልበት ስጠኝ ጠላት ሲቀድም አንተ ፊቴ ቅደም እነሱ በስጋ ያበረቱኛል አንተ በመንፈስ ጠብቀኝ ለእነርሱ አቅም እንደሰጠህ ለኔም ሀይልህን አድለኝ እያለ ይጸልያል። ጠላት ቢከበን ሞት ቢያንጃብብ ችግር ቢከበን ሀዘን ቢያጠላብን እግዚአብሔርን ይዘን ምን እንሆናለን? ምንም። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

ናና_አማኑኤል_ናና ናና አማኑኤል ና መድኃኒቴ ፍቅርህን አልብሰኝ ይቅር መራቆቴ [፪] የምሕረት አባት.... አማኑኤል የቸርነት ጌታ........ አማኑኤል ፊትህ የተመላ...... አማኑኤል ሁሌ ለይቅርታ..... አማኑኤል ካለው ፍቅር በላይ... አማኑኤል አባት ለአንድ ልጁ.... አማኑኤል አምላክ ይወደናል.... አማኑኤል አልቀረንም ደጁ...... አማኑኤል            አዝ መድኃኒቴ ልበል..... አማኑኤል ድኛለው በሞትህ.... አማኑኤል ቁስሌ ተፈውሷል..... አማኑኤል በቁስልህ በሞትህ... አማኑኤል ብሸጥህ አቀፍከኝ... አማኑኤል ስወጋህ አይኔ በራ... አማኑኤል በፍቅርህ አወጣኸኝ... አማኑኤል ከዚያ ከመከራ.......... አማኑኤል       እዝ አንተ ከኔ ጋር ነህ... አማኑኤል አዎ ከኔ ጋራ......... አማኑኤል ድል አርገህልኛል.... አማኑኤል የጭንቄን ተራራ...... አማኑኤል በጉባኤ መኃል....... አማኑኤል አፌ አንተን አወጀ.... አማኑኤል የከበረ ደምህ....... አማኑኤል ነፍሴን ስለዋጀ...... አማኑኤል       እዝ የድንግሏ ፍሬ.... አማኑኤል የብላቴናዋ........ አማኑኤል የቤቴ ምሰሶ....... አማኑኤል የነፍሴ ዋናዋ..... አማኑኤል መሰሬቴ አንተ ነህ.... አማኑኤል ያሳደገኝ እጅህ........ አማኑኤል አተወኝም አንተ........ አማኑኤል ስለሆንኩኝ ልጅህ..... አማኑኤል
 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

''ሳንለምነው ዐውቆ የሚሰጠን" ሆኖ ሳለ ለምን ወደ እግዚአብሔር እንጸልያለን? መምህሬ በውይይታችን መካከል ልናስብባቸው የሚገብ ጥያቄዎች ብሎ ጥቂት ጥያቄዎችን አጋራኝ።አንደኛው ጥያቄ ሳንለምነው ዐውቆ የሚሰጠን" ሆኖ ሳለ ለምን ወደ እግዚአብሔር እንጸልያለን? የሚል ነው። ከዚህ በፊት ጥያቄውን በተለያዩ ውይይቶች መካከል ሲነሳ ሰምቻለው። ከኃጢአት በስተቀር ሁሉም ነገር ወደ እግዚብሔር መቅረብ አለበት። እርሱን ሳናማክር የእርሱን ፈቃድ በጸሎት ሳንጠይቅ የምንሰራው ስራ ሊኖር አይገባም። የሚል አስተሳሰብ ስለነበረኝ ረበሸኝ።ይህን ከመፈጸም የዘገየው ብሆንም። በትክክል ክርስቲያኖች ፈቃዳቸውን ወደ ፈቃደ እግዚአብሔር የሚያቀርብበት መንገድ ጸሎት ነው። ክርስቲያኖች ሕይወታቸው እንደ ንጹህ መሥዋዕት ለአምላክ የሚያቀርብት በጸሎት ነው። እንደውም የማትጸልይበት የሕይወትህ ክፍል አይኑር ይባላል። ታዲያ የጸሎትን ይዘት በተመለከተ ለእግዚአብሔር የምናቀርበው የሚያቀውን መሆን አለበት? ስለ እያንዳንዱ ነገር እንጸልያለን? ምን ይቅደም? ምን ይከተል? የጸሎታችን ይዘት ምን መሆን አለበት? የአባ ፖርፎርዮስ ምክር እንዲህ ይላል በአጭሩ መሸከም ያለብንን ሸክሞች እንዲያሸክመን እንጸልያለን እንጂ ስለሁሉ ችግሮቻችን እና መከራችን በእርሱ ፊት አንቆምም። ሁሉን ለእኛ መልካም ስሆነ ነገር የሚያውቅ እና የሚሰጠን ለእርሱ በርጉዕነት ከምኞቶቻችን ነጻ ሆነን ጸሎቱን እናቅርብ። ስለዚህ ስንጸልይ ስለ መንፈሳዊ ድኅነታችን ብቻ ይሁን ሌላው ጭማሪ ነው ጌታ በወንጌል እንደገጸው። ምስጢሩ አንድ ነገር ብቻ አለመጠየቅ ነው። (ጸሎት አጀንዳ መስጠት አይደለምና) ይህን ስጠኝ ይህን አድርግልኝ ከማለት ተቆጥበን ከክርስቶስ ጋር ስላለን ህብረት ብቻ ልናስብ ይገባል። የሚያስፈልገንን ከእኛ በተሻለ እርሱ ያቃል። ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነ በምድር ይሁን እንበል። ፈቃዱ ብቻ ይሁን። እርሱ ሁሉንም ይሰጠናል ነገር ግን When There is even a trace of egotism, noting happens. (Wounded by love pp117) አባ እንጦኒ ብሉም በጸሎት ስመለኖር ባስተማሩትም ይህ ተመዝግቧል (Living prayer pp80 -82):- ጠይቁ ይሰጣችኋል ቢልም ( ማቴ 7:7) የምንጠይቀዉን በእምነት ማቅረባችን የጥያቄ ጸሎቶች (Prayer of petition) ይፈጸማል ብለን በሙሉ እምነት ማቅረብ የተናቀ ነገር አይደለም ይሉናል። የእምነታችን መገለጫ ነው። ያልተመለሱ ጸሎቶቻችን ከእምነት ማነስ : የሚጠቅመንን ካለማወቅ መልካም ቢመስለንም እና ክርስቶስ እንደጸለየው ካለመጸለይ የሚመጣ ነው። መደምደሚያ:- ''ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር መዋሐድ ነው''። ይህንና ያን ስጠን ማለት ከዚህ ያነሰ ነው። ቢደረግም በሙሉ እምነት መደረጉ ይሻላል። ''እንዲህ አድርግልን'' ብለው ወደ ጌታ የተጠጉ ስለነበሩ።የተፈጸመላቸውም ያልተፈጸመላቸውም አሉ። እኛ ስንጸልይ ጌታ እንዳስተማረን በጌቴሴማኒ አርአያ እንደሆነን ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁም በምድር ትሁን ብቻ እንበል። በእውነተኛ ጸሎት ላይ ላለ አረጋዊው እንዳለ ስዕለት አስተብቁዖት አያሻውም። 📝 ዲ/ን በረከት አለምሸት

ገብርኤል በሰማይ ገብርኤል በሰማይ ኤልሳቤጥ በምድር (2) ይመሰክራሉ ድንግል ያንቺን ክብር (2) አዝ ትጸንሲ ሲልሽ በከበረ ዜማ ይሁንልኝ አልሽው ትውልደ እንዲጽናና ከገብርኤል ሰምተው መላዕክቱ ሁሉ ለበጉ ማደሪያ ክብርን ይሰጣሉ ብፅዕት እንላለን እኛም አደግድገን የራማውን ልዑል አብነት አድርገን አዝ ስርሽ በምድር ነው ማዕረግሽ በሰማይ ንፁ መሰቦ ወርቅ የተሞላሽ ሲሳይ የማይፀንሽ ፍሬን በላነው ጠጣነው በኤፍራታ ሰምተን በዱር አግኝተነው ይተሰወረውን መና በልተነዋል ከተመረጡት ጋር ብፅዕት ብለናል አዝ ከተፈጥሮ በላይ ፅንስን ያዘለለ የእሳት ምሶሶ ባንቺ ተተከለ የእግዚአብሔር ሀገሩ የእንጀራ ቤታችን ምንኛ ድንቅ ነው ክብርሽ እናታችን ብፅዕት እንላለን እኛም አደግድገን ቅድስት ኤልሳቤጥን አብነት አድርገን አዝ ተወልዶ በግርግም ተኝቶ ስላዩት ሰውና መላዕክት አብረው አከበሩት የጥሉ ግድግዳ በልጅሽ ፈረሰ በዳግሚት ሄዋን የአዳም ዘር ተካሰ እጅ እንነሳለን ሆነን በትህትና ክብርሽን መመስከር ክብራችን ነውና
የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel

አንጨነቅ ይህን በማድረጋችን የምናተርፈው ምንም ነገር የለምና። ከልክ በላይ በማሰብ ራሳችንን ነው የምናሰቃየው አሰብነውም አላሰብነውም እግዚአብሔር ይሰጣል! እንዲያውም አብዛኛውን ጊዜ ሳንጨነቅ።ስለዚህ በመጨነቅ ምን እናገኛለን ራሳችንን ከመቅጣት ውጪ?” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 6 ለወዳጆቻችን ሼር እናርግላቸው ምናልባት ተጨንቀው ይሆናል እንዲጽናኑ። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel