Orthodox new mezemure
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የሆነውን የህይወት ቃል ጌታ እግዚአብሔር በገለጠልን ፀጋ መጠን የምንካፈልበት ሲሆን! " ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤"ቲቶ 2÷11 ስለዚህ ፀጋ ያየነውን የዳሰስነውን በስልጣን ቃል ለትውልድ ሁሉ በእምነት እናውጃለን!! ቤተሰባችን ስለሆናችሁ በክርስቶስ ፍቅር እንወዳችኃለን!!
Більше207
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
_አዲስ_ዝማሬ_ተናገር_አለኝ_Tenager_Alegn_ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል_መክብብ_Offic_tRYLzgENjK0.m4a1.49 MB
_አዲስ_ዝማሬ_ዮሐንስ_ፍቁረ_እግዚእ_ዘማሪ_ዲያቆን_አቤል_መክብብ_mahtot_oxg1Ltt03j0_599.m4a1.25 MB
_አዲስ_ዝማሬ_በቅዱስ_አጠራርህ_ዘማሪ_ዲያቆን_ዘለዓለም_ታከለ_ዘጎላ_New_Mezmur_B_qRX7Tnl7rrs.mp37.60 MB
_አዲስ_ዝማሬ_ማርያም_ዘማሪ_ዲያቆን_ዘለዓለም_ታከለ_ዘጎላ_New_Mezmur_Maryam_hVLx8FBYWEE.m4a1.74 MB
_ዘማሪት_ሲስተር_ልድያ_ታደሰ_አሳዳጊዬ_New_Orthodox_Mezmur_Asadagiye_P4nVRiL1TQU.m4a3.01 MB
👍 2
Показати все...
TikTok · አንድ ቀለም ከዲ/ን ዶ/ር ጋር
12.3K likes, 178 comments. “#ከሡከሡ #ከሡ_ከሡ#ጋር #አብይፆም🙏 #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ፀንታ_ለዘለዓለም_ትኑር #ሀገሬኢትዮጵያ🇪🇹💚💛❤️ #ቃለህይወት_ያሰማልን #foryoupage #fyp #foryou #habeshatiktok #ተዋህዶ #ኦርቶዶክስ ”
👍 2
እንዲህ ጹሙ
በፆም ውስጥና ከፆም ውስጥ ያለውን ምሥጢር ለመለየት በፆም ውስጥ ከፆም መጠቀም ያስፈልጋል ። ክርስቲያን በንግግሩና በሕይወት አካሄድ መስመሩ እግዚአብሔርን ያከብራል ። ግን ደግሞ ክርስቲያን በአንድ ነገር አምላኩን ለማክበር ይቸገራል ፦ በሀሳቡ ። ሀሳብ እግር ካገኘ የትግበራ ቁልፍ ነው ። ብዙ ኃጢአቶች ምንጫቸው ሀሳብ መሆኑ ግልጽ ነው ። በትምህርት ክፍለ ጊዜ ሀሳብ በጽሑፍ ይታሰራል ። በክርስትናው ሕይወት ደግሞ ሀሳብ በፆምና በጸሎት ይታሰራል ። ጸሎት ስለችግር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር ናፍቆንም ሲሆን እርካታ አለው ። ፆምም ከምግብ አድማ ይልቅ የመንፈስ ሲሆን በረከት አለው ።
ፆም የክርስቲያኖች ዕድል ነው ። ዕድልነቱ ደግሞ የተመረጠ መሆኑን ይሰብካል ። ፆም ክርስቶስን የምንመስልበትም አንዱ መንገድ በመሆኑ ክቡር ነው ። ፆም ክርስቶስ ቀጥሎም ክቡራን አባቶች ያለፉበት በመሆኑ የክርስትናው ቁልፍ ነው ። ፆም የዓመትበአል ናፍቆት ሳይሆን የመንፍስ ናፍቆት ነው ። ብዙዎች በፆም ውስጥ ከፆሞ አይጠቀሙም ። ፆም የታሪክ ዝክር የሚመስላቸው ብዙ ሰዎች አሉ ። ፆም ግን በትውልድ መካከል ክርስቲያን በእምነት ታሪክን ለትውልድ እንዲያስቀምጥ ያደርጋል ። ጌታችን አርባ ቀንና አርባ ሌሊት የጦመው ለምንም ዝክር አይደለም ። በጦም ግን የመንፈስ ቅዱስ አብሮነት ፣ የሕይወት ምሪት ፣ የክርስትናው ካርታ ፣ የፀጋ ሞተር ከጸባዖት ይፈስሳልና ለክርስቲያን የዓመትና የወራት ትውስታው እንዳልሆነ መጽሐፍ ቅዱስ አስርግጦ ይናገራል ።
ክርስቲያኖች አንድ ነገር እናስተውል የምንይዘውና የምንፈታው ፆም የለም ። ወደ ዓለም ከመኮብለል የሚይዘን ፣ ከዲያብሎስ ሽንገላ የሚፈታን ፆም ግን አለ ። ፆም ይዣለሁ አይባልም ነውር ነው ። የምንፆም ከሆነ ፆሙ እንደያዘን ሕይወታችን ፣ ውሎችን ፣ ንግግራችን ይመሰክራል ። ፆምን ፈታው አይባልም ነውር ነው ። የመንፆም ከሆነ ከዲያብሎስ እስራት የተፍታው ሕይወታችን በራሱ ምሥክር ነውና መናጋርም አያስፈልግም ። አዎ የምይዘውም የምንፈታውም ፆም የለም ። አዎ ፆም የምግብ አድማ አይደለምና ክብር ይግባውና ጌታችን ጦምን በጦመበት ገዳመ ቆርንጦስ ውስጥ ከመግበታቱ ቀፊት የበላው ስጋ ሲወጣም የበላው ሥጋ የለም ። ፆም ለእግዚአብሔር እሺ ማለትነውና ለሰይጣን እንቢታን ይፈልጋል ። ክርስቲያኖች በፆም ጊዜ ሥጋና ገንቢ ምግቦችን የማንበላበት ዋና ምክንያት የሥጋ ሀሳብና ስሜትን ለሞቆጣጠር ቢሆንም ፤ በዛው ልክ ለሰይጣን እንቢ ማለትም ፍቱን መድኀኒት ነው ። ሰይጣንን እንቢ ሳይሉ ሥጋ አለመብላት ምስኪንነት ነው ። ትክክለኛው ፆም እግዚአብሔር እሺ በሚል ልብ በፊቱ መንበርከክ ነው ። ሰይጣን ፆምን ሊያስፈታ ሥጋ አያበላንም ። አዳምን ላስታውሳችሁ ። አዳም እፀ በለስን የበላው በመንፋሱ ሳይሆን በእጁና በአፉ ነው ። በፆም ሰዓት ሥጋ ነክ ነገር ብንቀምስ መንፈሳችን ሳይሆን በአእምሮአችን ትዕዛዝ በእጅና በአፋችን ነው የምቀምሰው ። ይህ የሥጋ ፆም ነው ።
ብዙ ክርስቲያኖች የፆም አቅማቸው የሥጋው ስርዓት ላይ ነው ። ይህ ግን የፆም አንዱ ክፍል ይሁን እንጂ የፆም ሙሉ አካል ነው ማለት አይቻልም ። የብዙ ክርስቲያኖች ፆም ቢሆን በሚጠቅም ባይሆን በማይጎዳ ስርዓት ላይ እየተራመደ ነው ። በፆም ውስጥ ሥጋ ስለበላን የሚጎዳ ሰው የለም ። ሥጋ ስላልበላን ግን የፆምን ጉልበት ማግኘት ይቻላል ። ቢሆንም አይጎዳም ባይሆንም አይጎዳም ። እንግዲህ ፆም ክቡር ነውና አጀንዳ ያስፈልገዋል ። ፆም ግብ አለውና ትጋት ያስፈልገዋል ። ፆም የምሪት ስንቅ ነውና የቃሉ መግቦት ያሻዋል ። ፆም በእግር ኅሊና ሰማይ መድረስ ነውና ጽሞና ያስፈልገዋል ። ፆም ከራስ መዳን ነውና አርምሞ ያሻዋል ። ፆም የንስሐ በር ነውና ቅዱስ ቁርባን ያስፈልገዋል ። ፆም መንፈሳዊ ደጅን ለሕይወት መክፈት ነውና ንጹህ ልብ ያሻል ። መንፍስ ሲፆም ፆም ፆም ይሆናል ። በሥጋ ዓይንና ስርዓት ብቻ የሚፆም ፆም ስራ ሆኖ ያደክማል ። በመንፈስ የሚፆም ፆም ግን ናፍቆት ሆኖ ያረካናል ። የመንፈስ ፆም ምንድነው ? የሕይወት መጽሐፍ እንዲህ ይላል ፦ ''ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም። " /ማቴ 6:14/።
የመንፈስ ፆም ከሆኑቱ አንዱ ይቅርታ ነው ። ይቅርታ የቂም ማረከሻ መድፍ ነው ። ይቅርታ ባለበት ስፍር ቂም ይንቀጠቀጣል ። ይቅርታ የዘመናት ትኩስ ዜና ነው ። ክርስቶስ ዛሬም ፍቅሩ የማይለመድ ትኩስ ዜና የሚሆንብን ይቅርታ ሕይወቱ ስለሆነ ነው ። ይልቅስ ፆም አንዱ መሥፈርቱ ንስሐ ነውና ይቅር ባይነትን በፆም ውስጥ እንደ መሥፈርት ማካተት ያስፈልጋል ። ይቅር ብትሉ አለ ጌታችን ። በሉና መባለን ፈልጉ እንደማለት ነው ። ለመሆን መሆንን መኖር ያስፈልጋልና ። የሰዎችን በደል አንድ ብለን ከቆጠርን ያልቃል ። ኃጢአታችንን ግን አንድ ብለን ለመቁጠር ስንነሳ አለማለቁ ተደቅኖብን ዝም እንላለን ። አዎ ጌታችን በጢቂቱ ታምነሃልና በትልቁ እሾምሃለሁ /ማቴ25:21/ ያለውን በዚህ ስፍራ ማስታወስ ያስፈልጋል ። ትንሹን ይቅር ብላችሁ ትልቁን ተቀበሉ ማለቱ ነው ። የእግዚአብሔር ይቅርታ ትልቅ ነው ። እግእግዚአብሔር ትልቅ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን በቂ ስለሆነም እረፍት ነው ። ጌታ ይቅርታው ልክ የሌለው ከምሕረቱ የሚበልጥ ትልቅ ኃጢአት ስለሌም ጭምር ነው ። ከትልቁ እግዚአብሔር የነሰነስ ትንንሽ ይቅርታ የለም ። ለትልቁ ኃጢአታችን ታላቁ ምሕረቱ አለ ። ያለ ይቅርታ መፆም ልክ እንደ አርቴፊሻል አበባ ነው ። ወይ አይለመልም ። ወይ ይደርቅ ። ወይ መዓዛ የለው ። ወይ ማደግ አይታይበት ። ወይ መትረፍ አይታይበት ። ልክ እንዲሁ ደግሞ በይቅርታ ልብ መፆም የሕይወት ልምላሜ በእግዚአብሔር ቃል ማግኘት ነው ። የልብ ስፋት በመንፈስ ቅዱስ አቅም መሞላት ነው። ለወድም መቆረስ የተሰጠን በመስጠት ማረፍ ነው ።
ፆም የንስሐ በረከት ነውና ንስሐ የይቅርታ መቃተት ነው ። ለዚህ መቃተት ደግሞ የሌሎች ነፍስ ታስራ ከሆነ መልስ አይገኝለትም ። ቃሉን ማስተዋል ያስፈልጋል ። ''ብትሉ" ነው የሚለው ። ሲሉ መባለን መጠበቅ ጥሩ ነው ። መግቢያን ማሳመር ነውና ። ሰድበው የተደባደቡ አሉ ይቅር ብለው ደግሞ የሚተቃቀፉ አሉ ። ይቅርታ የጥሩ መግቢያ ብቻ ሳይሆን ጥሩ መግባብያ መሆኑን መዘንጋት አያስፈልግም ። ጌታችን በሉና መባልን ጠብቁ አለ ። እንግዲህ የሰዎችን ነፍስ አስራችሁ ዛሬ በፆሙ ነጭ የለበሳችሁ አስተውሉ ። በሉና መባልን ፈልጉ ። በሉና የመባልን በረከት ተቀበሉ ። አዎ ይቅርታ ስትሉ ይቅር መባልን ትታቀፋላችሁ ። ይቅርታ የፆም መሥፈርት በመሆኑ እንዲህ ጹሙ ፦ በይቅርታ ።
እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነው ። ይቅር ባይ ሰውም ይወድዳል ። እግዚአብሔር መሐሪ ነው ለምሕረት ልቡን የሚከፈተውን ይወድዳል ። እግዚአብሔር እንደ ልቤ እንዲለን ይቅርታ አንዱ መንገድ መሆኑን መዘንጋት ጥሩ አይደለም ። እግዚአብሔር የዘመኑን ምሥጢር እንዲገልጥልን ጸሎት ፤ እግዚአብሔር ከዘመኑ ክፋትና ነውር እንዲያስመልጠን ፆም አትራፊ መሆኑን መረዳት ይገባል ። በመንፈስ ፆም እግዚአብሔር ይባርካችሁ !!
ዲያቆን እስጢፋኖስ ደጀኔ
መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ.ም
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.