cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

💞አውደ💞 ቃል 💞💖

ዚግጥም መንደር አብሚን በቃላት ስሜታቜንን እንገላላፃለን join & share እንዳይሚሳ

Більше
РеклаЌМі ЎПпОсО
452
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
+147 ЎМів
+4930 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ኚአትሮንሱ ስር አንድ ሁልጊዜም መማር ዚማይታክታ቞ው አባት ነበሩ። በጣም ዚተማሩ ቅኔ አዋቂ መፃሕፍትን ዚመሚመሩ ሊቅ ቢሆኑም ሁሌም ኚአትሮንስ ስር ዹማይጠፉ ተማሪ ነበሩ።ይህንን ልምዳ቞ውን á‹«á‹š አንድ ሰው፩ "እርስዎ ብዙ ዚተማሩና ያነበቡ ሰው ነዎት ኹዚህ በኃላ ማሹፍ ሲገባዎት ለምን ጊዜዎን በትምህርት ያጠፋሉ?" አላ቞ው። እርሳ቞ውም ፊ "መልዓኹ ሞት መጥቶ ወደ ፈጣሪ በወሰደኝ ጊዜ 'ዚት አግኝተህ አመጣኞው?' ሲባል ኚአትሮንስ ሥር ቁጭ ብሎ ዹአንተን ቃል ሲሰማ አገኘሁት ብሎ እንዲነግርልኝ ነው"አሉ።    መልዓኹ  ሞት አሁን በዚህ ሰሞን መጥቶ ቢወስድህ ምን ሲያደርግ አገኘሁት ዹሚል ይመስልሃል ? ሲፀልይ? ሲመፀውት? ሲመርቅ? ሰዎቜን በፍቅር ቃል ሲናገር? ሲያማ?ሲሳደብ?ሲያስታርቅ? ሲያጣላ?እውነትም ዚእኚህ አባት ጭንቀት እጅግ ተገቢ ጭንቀት ነበር። እኛም ወደራሳቜን እንመልኚት  🙏🙏🙏 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
ППказатО все...
🔥 1
አይጥ ጠላ ጠምቃ ጠጥታ ጠጥታ ⚒ዱላ ስጡኝ አለቜ ድመት ልትመታ 🐱 ♡ ã…€  âŽ™ã…€  âŒ²  http//me:/AWDEKALALT_2112 @AWDEKALAT_2112      
ППказатО все...
          ዘመም ይላል እንጂ (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ጊዜው መክፋት እንደ ግፉ መስፋት እንዳገሩ ክስመት እንዳገሬው ጥመት እንደሰው ጭካኔፀ እንደ ልቡ ፍሬ ታምር ነው መትሚፍሜ ፀ ታምር ነው መኖሬ:: ዹበጎ ሰው ሀሳብ ፀ ሲካድ እለት በለት ጉድጏድ ተምሶለት ሰብእና ሲቀበርፀ በዚህ ምድር መኖር ፀ አያስመኝም ነበር:: ምድሩ ሳር ቅጠሉፀ በስጋት ተሞልቶ ዚማለዳው ሰማይፀ እንዳንቀልባ ቀልቶ ታሚደ ነደደ ኚዘብጥያ ወጥቶ ዘብጥያ ወሹደ ዹሚል ዜና ብቻ አዚሩን ሲሞላው ሰው በገዛ ጥላው በርግጎ ሲሞበር በዚህ ምድር መኖር ፀአያስመኝም ነበር:: አዎ ለጊዜውም ቢሆንፀ ግፍ ያደነዝዛል በደል ያስተክዛል ጊዜም ጠብን ሜሮፀ ወደ ፊት ይጏዛል በልብ ሰሌዳ ላይ ፀቂም ይደበዝዛል በነገ ያመነ ልጁን ቀብሮ መጥቶፀ ሚስቱን ያስሚግዛል:: ይቅርታና ምህሚት ፍቅርና ህብሚት ኹግፍ ጋር ፍልሚያ቞ው ፀ ቢሆን ዚሞት ሜሚት ዳገት ይወጣሉ ፀ በንጥፍጣፊ አቅም ዹመኖር ፍላጎት ዘመም ይላል እንጂ ፀ ተገርስሶ አይወድቅም:: Join us https://t.me/AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
ППказатО все...
💞አውደ💞 ቃል 💞💖

ዚግጥም መንደር አብሚን በቃላት ስሜታቜንን እንገላላፃለን join & share እንዳይሚሳ

ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
ወንድሞቌን በኢሞጂ እኔ 🥰❀ እናንተስ ?? @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
ППказатО все...
🥰 2
‍ እያጣሁኝ እንጂ እያነሰኝ አቅሜ እንዲህ አልነበርንም እኔና ቅዳሜ ኑሮ እዚጚመሚ ሲራቆት ሕይወቮ ቅዳሜን በስራ እሁድን በቀ቎ አሳልፈው ጀመር በሀሳብ በትካዜ ዹዚ ሁሉ ምክኒያት አንቺ ነሜ ደሞዜ ዹሚል ሲንግል ልልቀቅ አልልቀቅ? ? 😁🀔🀔 @AWDEKALAT_2112 @AWDEKALAT_2112
ППказатО все...
👍 1
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
ППказатО все...
👍 2
00:53
ВіЎеП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
እዚህ ውስጥ ስምሜ ዹሌለ ኢትዮጵያዊ አደለሜም ግን ዹኔም ዹለም ስምሜ ዹሌለ ዳይ ወደ comment @ @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme 😅
ППказатО все...
             💔ናፍቀሜኛል_ሆዎ💔                                  መንገድሜ መንገዮ                      ሆኖ ዹዘለቀው                    ፍቅርሜ ስለገዛኝ                ባሪያሜ ስለሆንኩ ነው                    ሆዮ ናፍቀሜኛል                   ምፈልገው ቢሟላ                  ዚጠዚኩትንም ባገኝ                   አልጠግብም እኔ                  አይንሜ ነው ዚራበኝ                    ፍቅር ናፍቀሜኛል                    ሆዮ ናፍቀሜኛል                   አንቺን ለማግኘት                ልቀ አጥብቆ ይመኛል፡፡    👇👇👇👇👇👇👇👇     join us @awdekalat_2112 join us @awudekalat_2112    
ППказатО все...
👍 1
ውሞታም ይገርማል ሰው ነገሹኝ ሰማሁ ዚእውነት ወድጄህ በውሞት አለም ጠፋሁ ደሞ አምኜሀለሁ ያንቺ ነኝ ስትለኝ በቃልህ ሾንግለህ ልቀን ስትሰርቀኝ ግን እውነቱ ይሄ አደለም አንተ ዹሌላ እንጂ ዹኔ አይደለህም አለቜ ደሞ እንደኔ ዚምታደማት እወድሻለሁ እያልክ ዚምታታልላት ግን ውሞታም ነህ አስመሳይ ለቀሹበህ ፃዲቅ መሳይ እንደኔ ያመነህን ደሞ አታላይ አሁን ግን አውቂያለሁ እውነቱን ሁሉ ሰምቻለሁ ፍቅሹኛ እንዳለህ ዹሌላ እንደሆንክ ተሚድቻለሁ ግን ስላሳለፍና቞ው ዚውሞት ጊዚያት አመሰግናለሁ።።።።። 💔💔💔💔💔💔💔💔 @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme @yetbebaleme
ППказатО все...
👏 1
Repost from N/a
🕊 [ † እንኳን ለነቢዚ እግዚአብሔር ቅዱስ ኀርምያስ ዓመታዊ ዚዕሚፍት በዓል በሰላም አደሚሳቜሁ ፀ አደሚሰን። † ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † †  ðŸ•Š  ቅዱስ ኀርምያስ  ðŸ•Š †    † ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኀርምያስ ኚዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በስድስት መቶ አካባቢ ዹነበሹ ነቢይ ነው:: አባቱ ኬልቅዩ ይባላል:: ኚካህናተ እስራኀል አንዱ ነበር:: እግዚአብሔር ኀርምያስን ዚጠራው ገና በሕፃንነቱ ነበር:: "ኚእናትህ ማኅጾን ሳትወጣ መርጬሃለሁ: ቀድሌሃለሁ" ሲልም በገሃድ መስክሮለታል:: [ኀር.፩፥፭] (1:5) ኚቅዱሳን ነቢያት እንደ ኀርምያስ ዹተሰቃዹና ያለቀሰ ዹለም:: ኚሰባ ዘመናት በላይ ስለ ወገኖቹ አልቅሷልና ሊቃውንት "ነቢዚ ብካይ" [ባለ እንባው ነቢይ] ይሉታል:: ዘመኑ ዘመነ-ኃጢአት [ዘመነ ዐጞባ] ነበር:: እሥራኀላውያን ኚመሪዎቻ቞ው ኹነ ሎዎቅያስ ጋር በክፋት ተባብሚውም ነበርና ኀርምያስን አልሰሙትም:: ይልቁኑ ክፉ ቊታ ውስጥ አስሚው አሰቃዩት:: እግዚአብሔር ግን በኢትዮጵያዊው አቀሜሌክ አማካኝነት ኚመኚራው አዳነው:: ዹተሰበኹላቾውን ዚንስሐ ጥሪ አልሰሙምና ስልምናሊር ዚሚባል ዚአሕዛብ ንጉሥ መጥቶ አሥሩን ነገድ ማርኮ በ፯፻፳፪ [722] አሩር [ነነዌ] አወሚዳ቞ው:: በኋላ ደግሞ በኃይለኝነቱ ዚታወቀው ዚባቢሎን ንጉሥ ይማርካ቞ው ዘንድ ወደ ሁለቱ ነገድ ኢዚሩሳሌም ደሹሰ:: ኀርምያስ ወደ ኹተማዋ ዳር ወጥቶ ስለ ኢዚሩሳሌምና ስለ እግዚአብሔር ቀተ መቅደስ አለቀሰ:: ኚቀተ መቅደስ ንዋያት እኩሉን ለምድር አደራ ሰጣትና ሞሞገቜው:: ነቢዩ ዹተናገሹው አይቀርምና ንጉሡ ናቡኚደነጟር እኩሉን ገድሎ: እኩሉንም ማርኮ: ኢዚሩሳሌምን አቃጥሎ: ዚአሕዛብ መዘባበቻ አድርጐ በ፭፻፹፮ [586] ባቢሎን አወሚዳ቞ው:: ቅዱስ ኀርምያስን ግን ትሩፋን [ኚመኚራው ዚተሚፉት] ይዘውት ወደ ግብጜ ወሚዱ እንጂ አልተማሹኹም:: በዚያም ተአምራትን አድርጐ አራዊትን አጥፍቷ቞ዋል:: ትንሜ ቆይቶ ግን እውነተኛ አባት : ነቢይ : መምሕርም ነውና ወደ ሕዝቡ [ወደ ባቢሎን] ወሹደ:: በዚያም ትንቢትን እዚተናገሚ : ሕዝቡን ኚሰባ ዓመታት በኋላ ወደ ሐገራ቞ው እንደሚመለሱ እያስተማራ቞ው በባቢሎን ቆይቷል:: ያለ በደሉም በመኚራ቞ው ተካፋይ ሆኗል:: ሰባው ዘመን ሲፈጞም እግዚአብሔር እንደ ቃል ኪዳኑ በኀርምያስ መሪነት እሥራኀል ወደ ኢዚሩሳሌም ተመለሱ:: አሁንም ግን ክፋታ቞ውን ይተው ዘንድ ፈቃደኞቜ አልነበሩምና ኀርምያስ ገሠጻ቞ው:: በዚህ ተበሳጭተው ሊወግሩት ሲሉ ጾጋ በዝቶለት : ምሥጢርም ሰፍቶለት ስለ ነገሹ ሥጋዌ [ስለ ክርስቶስ ዚማዳን ሥራ] አምልቶና አጉልቶ ትንቢት ተናገሹ:: አንዮ ልቡና቞ው ታውሮ ኀርምያስ ነው ብለው ድንጋዩን በድንጋይ ሲወግሩት ውለዋል:: ዘግይቶ ግን ኀርምያስ ራሱን ገለጠላቾው:: ስለ እነርሱ ሲል ሰባ ዘመን ያለቀሰውንና ምትክ ዹሌለውን አባታ቞ውን ወግሹው ገደሉት:: ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኀርምያስ ሃምሳ ሁለት ምዕራፎቜ ያሉት ሐሹገ ትንቢት ተናግሯል / ጜፏል:: ዜና ሕይወቱ ኚራሱ ዚትንቢት መጜሐፍ በተጚማሪ በተሹፈ ኀርምያስ : በመጜሐፈ ባሮክ : በገድለ ኀርምያስ : በዜና ብጹዐን : በመጜሐፈ ስንክሳርም ተጜፏል:: † ቾር እግዚአብሔር በኀርምያስ ምልጃ ሃገራቜንን ኚጥፋት: ሕዝቊቿን ኚስደትና ኚመቅሰፍት ይሰውርልን:: 🕊 [ † ግንቊት ፭ [ 5 ] ቀን ዚሚኚበሩ ዓመታዊ ዚቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ኀርምያስ ነቢይ [ኚታላላቆቹ ነቢያት አንዱ] [ † ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ጎጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት ፪. ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ፫. አቡነ ገብሚ መንፈስ ቅዱስ ፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ ፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ † " ኢዚሩሳሌም ሆይ ነቢያትን ዚምትገድል : ወደ እርሷ ዚተላኩትንም ዚምትወግር : ዶሮ ጫጩቶቿን ኚክንፎቿ በታቜ እንደምትሰበስብ ልጆቜሜን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳቜሁምም:: እነሆ ቀታቜሁ ዚተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል:: እላቜሁአለሁና : በጌታ ስም ዚሚመጣ ዚተባሚኚ ነው እስክትሉ ድሚስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም :: " [ማቮ. ፳፫፥ፎ፯-ፎ፱] [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   ðŸ•Š                    ðŸ’–
ППказатО все...
👍 1