uk
Feedback
Orthodox⛪anthems ❀‍🩹

Orthodox⛪anthems ❀‍🩹

ВіЎкрОтО в Telegram

ሃይማኖታዊ ወሬዎቜ, ምስሎቜ, ግጥሞቜ, ስዕሎቜ እና መዝሙሮቜ ብቻ Just impressing our soul by anthems❀‍🩹🎶

ППказатО більше
1 417
ПіЎпОсМОкО
+424 гПЎОМО
+227 ЎМів
+2530 ЎеМь
Архів ЎПпОсів
ዚማትገመት ሰው ሁን... ቀተሰቊቜህ ጠዋት ተኝቷል ብለው ሲያስቡ ቀተክርስትያን ሄደህ ጾበል ተጠምቀህ ተመለስ

​በአርሲ ምድር በኊርቶዶክሳውያን ወገኖቻቜን ላይ እዚተፈጞመ ያለው ስልታዊ እና አሚመኔያዊ ግድያ መቆም አልቻለም። ትናንትም፣ ዛሬም ዚንጹሃን ደም እንደ ጎርፍ እዚፈሰሰ ነውፀ ታሚዱ፣ ተሰደዱ፣ ማሚፊያ
​በአርሲ ምድር በኊርቶዶክሳውያን ወገኖቻቜን ላይ እዚተፈጞመ ያለው ስልታዊ እና አሚመኔያዊ ግድያ መቆም አልቻለም። ትናንትም፣ ዛሬም ዚንጹሃን ደም እንደ ጎርፍ እዚፈሰሰ ነውፀ ታሚዱ፣ ተሰደዱ፣ ማሚፊያ አጡ። ​ይሁንና ኚእነዚህ ወገኖቻቜን እልቂት እኩል እያስደነገጠ ያለው ዚእኛ "ዚዝምታ ዋጋ" ነው። ​ዛሬ በአርሲ ያሉ ወንድም እህቶቻቜን ዋጋ እዚኚፈሉ ያሉት በማንነታ቞ውና በእምነታ቞ው ብቻ ሳይሆን በእኛም ድንዛዜ ጭምር ነው። ዚአንድ ንጹህ ሰው ህይወት ሲቀጠፍ "ለኔ አልደሹሰም" ብሎ በ቞ልታ ማለፍ፣ ነገ ተራው ወደ እኛ ቀት ሲመጣ ዚሚጮኜልን ሰው ማጣትን ያስኚትላል። ​ሀዘናቜን በ ዚፖለቲካ ትርክትና ፍርሃት ኹቆለፈው አንደበታቜን በላይ ዚንጹሃን ነፍስ አትበልጥም? ለገዳዮቜ ግድያውን እንዲቀጥሉበት ትልቁን ዚሞራል ስንቅ እዚሰጣ቞ው ያለው ዚእኛ ግብሚ-አልባነት እና ግድዚለሜነት ነው። ​ ወገን በገዛ ሀገሩ፣ በገዛ ቀዬው ሲታሚድ አይቶ እንዳላዚ ማለፍ ኚገዳዮቹ እኩል ዚታሪክ ተጠያቂ ያደርገናል። ​ዚኊርቶዶክሳውያን ደም ማንም መጫወቻ ሊያደርገው ዚሚነሳበት ሜዳ መሆን ዚለበትም። መንግስትም ሆነ ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ዚዜጎቜን በህይወት ዹመኖር መብት ዚማስኚበር ቀዳሚ ግዎታ቞ውን እንዲወጡ ድምጻቜንን በአንድነት ልናሰማ ይገባል። ​ዛሬ ለአርሲ ካልጮህን፣ ነገ ለራሳቜን ዚምናለቅስበት አንደበት እንኳ አይኖሚንም። ዝምታቜን ይበቃልፀ ፍትህ በአርሲ ኊርቶዶክሳዊያን ለሚታሚዱ ንጹሃን!

Story

ስሙት❀‍🩹
ስሙት❀‍🩹

Story

አንድ ቀን ሰዉ እንሆናለን🥺💔

Repost from Dn Eyuel Habtamu
አንድ ቀን ሰው እሆናለሁ .mp31.05 MB

ክፍል ሁለት ፈቃደ እግዚአብሔር 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ዚእግዚአብሔርን_ፈቃድ_ዹምናውቀው_እንዎት_ነው? እግዚአብሔር ፈቃዱን ለእኛ መግለጥ ፍላጎቱ ነው። ሥነ ፍጥሚትን ዚፈጠሚው፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ዚሰጠው፣ በኋላም ዚባሕርይ ልጁን በሥጋ ዹላኹው ፈቃዱን በግልጥ እንድናውቅ እንዲሁም በዚያ መሠሚት እንድንመራና እንድንኖር ጜኑ ፍላጎቱና ፈቃዱ ስለሆነ ነው። ሐዋርያው “እንደ አሳቡ፥ ዚፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና” ያለው ለዚህ ነው። /ኀፌ.፩፥፱/ዚእግዚአብሔርን ፈቃድ ዚምናውቅባ቞ው ዋና ዋና መንገዶቜ 1,✅መጜሐፍ ቅዱስፊ እግዚአብሔር ፈቃዱ ምን እንደሆነ በቅዱሳት መጻሕፍት በተለያዚ መንገድና ሁኔታ በግልጜ አስተምሮናል። ቅዱሳት መጻሕፍት ዚተሰጡበት ዋና ዓላማ ኚእግዚአብሔር ጋር እንዎት መኖር እንዳለብን? ለመዳን ምን ማድሚግ እንዳለብን? እግዚአብሔር ዚሚወድደውና ዹሚጠላው ምን እንደሆነ? በአጠቃላይ ዚግዚአብሔር ፈቃድና ለሰው ልጆቜ ያለው ዓላማ ምን መሆኑን ለእኛ ለመንገርና ለማሳወቅ ነው። ይኜን በተመለኹተ ቅዱሳት መጻሕፍት ብዙ ይናገራሉ። ነቢዩ ዳዊት “እግዚአብሔር ይነግሮሙ ለሕዝቡ በመጜሐፍ ወለመላእክቲሁኒ እለ ተወልዱ በውስ቎ታፀ እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጧም ለተወለዱት አለቆቿ በመጜሐፍ ይነግራ቞ዋል” ይላል። /መዝ.፹፮፥፮/ እንዲሁም “ኚትእዛዝህ ዚተነሣ አስተዋልሁ፣ ስለዚህ ዚሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዮ ብርሃን ነው” ይላል። /መዝ.፻፲፰፥፻፭/ ዚእግዚአብሔር ትእዛዝ አእምሯቜንንና ልቡናቜንን ፈቃዱን ለማወቅ ብሩህ ዚሚያደርግ ስለ መሆኑ ሲናገር ደግሞፀ “ትእዛዙ ለእግዚአብሔር ብሩህ ወያበርህ አዕይንተ - ዚእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል” ይላል። /መዝ.፲፰፥፰/ ቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙሩን ጢሞ቎ዎስን “ኚሕፃንነትህም ጀምሹህ ክርስቶስ ኢዚሱስን በማመን፥ መዳን ዚሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ ዚሚቜሉትን ቅዱሳት መጻሕፍትን አውቀሃልፀ” በማለት ዋናውና መሠሚታዊ ዹሆነው ዚእግዚአብሔር ፈቃድ ማለትም ዚእኛ መዳን በቅዱሳት መጻሕፍት አማካኝነት ዹተሰጠና ዹተገለጠ መሆኑን ተናግሯል። /፪ ጢሞ.፫፥፲፭/ ✅ስለሆነም ዚእግዚአብሔር ፈቃዱ ምን እንደ ሆነና እንዳልሆነ በቅዱሳት መጻሕፍት በግልጜ ዹተነገሹ ነው። “ዚእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዎት አድርጌ ላውቅ እቜላለሁ? ኚዚትስ አገኘዋለሁ? ዹሚል ጭንቀት ሊኖር አይገባምፀ በቅዱሳት መጻሕፍት በዓዋጅ ዹተነገሹ ነውና። ለዚህ ደግሞ ዚእግዚአብሔር እስትንፋስ ዚሆኑትን ዚቅዱሳት መጻሕፍትን ቃል መብላትና በውስጣ቞ው ባለው በትምህርታ቞ው መጥገብ ግድ ይላል። ለነቢዩ ለሕዝቅኀል እንዲህ ተብሎ እንደ ተነገሹ፩ “እርሱምፊ ዹሰው ልጅ ሆይ፥ ያገኘኞውን ብላ፣ ይህን መጜሐፍ ብላ፥ ሄደህም ለእስራኀል ቀት ተናገር አለኝ። አፌንም ኚፈትሁ፣ መጜሐፉንም አጎሚሰኝ። እርሱምፊ ዹሰው ልጅ ሆይ፥ አፍህ ይብላ፥ በምሰጥህም በዚህ መጜሐፍ ሆድህን ሙላ አለኝ። እኔም በላሁት፥ በአፌም ውስጥ እንደ ማር ጣፈጠ።” /ሕዝ.፫፥፩-፫/ ✅ቅዱሳት መጻሕፍትን ያልተማሚ ሰው ፈቃደ እግዚአብሔርን ለማወቅ በእጅጉ ይ቞ገራል። በአኗኗራቜን፣ በአነጋገራቜን፣ በምርጫዎቻቜን፣ ወዘተ ዚምናያ቞ው ምስቅልቅሎቜና ኹፈቃደ እግዚአብሔር ጋር ዚማይስማሙ ድርጊቶቻቜን አብዛኛዎቹ በቅዱሳት መጻሕፍት ዹተገለጠውን ዚእግዚአብሔርን ፈቃድ ጠንቅቆ ካለመሚዳት ዚሚመነጩ ና቞ው። ስለዚህ ዚእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መማርና ለተማርነውም መታዘዝና ታማኝ መሆን ይገባል። በትንሹ ስንታመን፣ ላወቅነው ቃለ እግዚአብሔር አክብሮት ስንሰጥና በሕይወታቜን መተግበር ስንጀምር ሌላውንም በ቞ርነቱ እዚገለጠልንና እዚሚዳን ይሄዳል። ፈቃዱን ለማድሚግ ዚሚጥርን ሰው እግዚአብሔር ዹበለጠውን ዚጥበቡን በር እዚኚፈተለት ይሄዳል። ጌታቜንና መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ “ፈቃዱን ሊያደርግ ዚሚወድ ቢኖር፥ እርሱ ይህ ትምህርት ኚእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ኚራሎ ዹምናገር ብሆን ያውቃል” ያለው ለዚህ ነው። /ዮሐ.፯፥፲፯/ ✅መጜሐፍ ቅዱሳዊውን እውነታ አዲስ በሚገጥሙ ዚተለያዩ ሁኔታዎቜ ላይ መተግበር መጜሐፍ ቅዱስ አጠቃላይ አቅጣጫ ዚሚያሳይና ዋና ዋና ዹሆኑ መሠሚታዊ ጉዳዮቜን ዹሚነግሹን ነው እንጂ በእያንዳንዱ ዝርዝርና ተራ ጉዳይ ውስጥ ገብቶ እኛ በአእምሯቜን እያብሰለሰልነው ያለውን ጉዳይ ሁሉ በቀጥታ “እንዲህ አድርግ” ወይም “አታድርግ” እያለ ዹሚነግሹን አይደለም። መጜሐፍ ቅዱስ ሀገራት “ሕገ መንግሥት” እንደሚሉት ያለ ነው። ዚሀገራት ሕገ መንግሥት ዚዚያን ሀገር ሕዝብ በተመለኹተ አጠቃላይ መሠሚቱን ዚሚጥልና ወሰኑንና ዳርቻውን ዚሚወስን ነው። ስለ እያንዳንዱ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ፣ ፍትሐ ብሔራዊ፣ ወንጀል ነክ፣ ወዘተ ጉዳይ ገብቶ አንቀጜ ዚሚያትት አይደለም። ነገር ግን በዚያ በሕገ መንግሥቱ መሠሚትነት ዚተለያዩ ዚማስፈጞሚያ ሕጎቜና መመሪያዎቜ በሹጃ በደሹጃ በዚዓይነቱ ይወጣሉ። ✅መጜሐፍ ቅዱስንም በዚህ ዓይነትሁኔታ ልናዹው እንቜላለን። ስለ መዳናቜንና ዘለዓለማዊ ሕይወትን ለማግኘት ምን ማድሚግ እንዳለብን በቅዱሳት መጻሕፍት በግልጜ ተነግሮናል። ኚዚያ ውጭ ስላሉ ሌሎቜ ጉዳዮቜ ግን አጠቃላይ አቅጣጫና መመሪያ በመስጠት ዳሩንና ድንበሩን ያሳዚናል እንጂ ዝርዝር ነገር ላይነግሹን ይቜላል። ለምሳሌም እያንዳንዱ ሰው በምን ዓይነት ዚሥራ መስክ መሰማራት እንዳለበት፣ ማንን ማግባት እንዳለበት፣ ምን ዓይነት ቀት እንደሚሠራ፣ ወዘተ አይነግሚውም። ስለዚህም ዚመጜሐፍ ቅዱስን ቃል በሚገባ በመማርና በማስተዋል መጜሐፍ ቅዱስ ላይ በግልጥ ያልተነገሩ ወይም በግልጜ ያልተናገሚባ቞ው ጉዳዮቜ ሲገጥሙን ቃሉን በሚገባ ዚተሚዳን ኹሆነ ጥሩ መሠሚትና መነሻ እናገኛለን። አጠቃላዩን ዚቅዱስ መጜሐፍ አቅጣጫና መመሪያ በዚያ በገጠመን ዝርዝር ጉዳይ ላይ በመተግበርና ኹቃሉ አንጻር በመመዘን ምን ማድሚግ እንደሚኖርብንና እንደማይኖርብን ፍንጭ እናገኛለን። ክፍል ሊስት ይቀጥላል,,,,,,,,,,, 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ❀ ✞_✞_✞ ❀ ለማንኛውም ጥያቄና አስተያዚት              👇👇👇👇👇👇         👉@sewargegn27 👈             ☝☝☝☝☝☝ 💐አደራቜሁን ዚእግዚአብሔር ቃል እንዲስፋፋ ቻናሉን ለዚትኛውም ዚተዋሕዶ ልጆቜ እንዲቀላቀሉ join በማስደሚግ ያበሚታቱንፀአሁኑኑ join ያስደርጉ!!! https://t.me/yehiwotbirhan27

ፈቃደ እግዚአብሔር ክፍል-1 🌹🌹🌹🌹🌹🌹 #ዚእግዚአብሔር_ፈቃድ🊋➻➻🊋✅ዚእግዚአብሔር ፈቃድ (ፈቃደ እግዚአብሔር) ምንድን ነው?ዚእግዚአብሔር ፈቃድ ስንል እግዚአብሔር ወድዶና ፈቅዶ እንዲሆን ዚሚያደርገውን ነገርና እንዲሆንዚሚፈቅደውን (ዹማይኹለክለውን) ነገር ያመለክታል።ዚእግዚአብሔር ፈቃድ ዚእግዚአብሔር ባሕርይ ዚሚገለጥበት አንዱ መንገድ ነው። ለምሳሌ እግዚአብሔር ቾር ነው፣ መሐሪ ነው፣ ደግ ነው፣ ... ፈቃዱም እንዲሁ ነውፀ እርሱ ወድዶና ፈቅዶ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እነዚህ ዚባሕርያቱ መገለጫዎቜፊ ቞ርነት፣ ደግነት፣ ምሕሚት ወዘተ አሉ።እንዲሁም ዚእግዚአብሔርን አሠራር ዚሚመራውና ክሂሉን ዚሚወስነው ፈቃዱ ነው። እግዚአብሔር ዚሚያደርገው ነገር ማድሚግ ዚሚቜለውን ሁሉ ሳይሆን ፈቃዱ ዹሆነውን ብቻ (ኚባሕርዩ ጋር ዚሚስማማውን ብቻ) ነው ዚሚፈጜመው። ለምሳሌ እግዚአብሔር ዓለምን ማጥፋትና እንዳልተፈጠሚ ማድሚግ ይቜላል። ነገር ግን ማድሚግ ስለሚቜል ብቻ (ይህን ለማድሚግ ክሂል ስላለው ብቻ) አያደርገውምፀ ፈቃዱ ማጥፋት አይደለምና። ስለሆነም ማንኛውንም ጉዳይ እግዚአብሔር ማድሚግ ስለሚቜል ብቻ ያደርገዋል ማለት ስህተት ነው። እርሱ ዚሚያደርገው ኚቅድስናውና ኚባሕርዩ ጋር ተስማሚ በሆነ መንገድ ነው። ይኜ ደግሞ ፈቃደ እግዚአብሔር ዹምንለው ነው። ዚእግዚአብሔር ፈቃድ እጅግ ትልቅና ሹቂቅ ነው። መጜሐፍም እንዲህ ይላልፊ“ዚጥበቡን ምስጢር ቢገልጥልህ! ማስተዋሉ ብዙ ነውና። . ዚእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ልትመሚምር ትቜላለህን? ወይስ ሁሉን ዚሚቜል አምላክ ፈጜመህ ልትመሚምር ትቜላለህን? ኹሰማይ ይልቅ ኹፍ ይላልፀ ምን ልታደርግ ትቜላለህ? ኚሲኊልም ይልቅ ይጠልቃልፀ ምን ልታውቅ ትቜላለህ? ርዝመቱ ኚምድር ይልቅ ይሚዝማል፥ ካባሕርም ይልቅ ይሰፋል። እርሱ ቢያልፍ፥ ቢዘጋም፥ ጉባኀንም ቢሰበስብ፥ዚሚኚለክለው ማን ነው?” ኢዮ.፲፩፥፮-፲ ክፍል ሁለት ይቀጥላል,,,,,,,,,,

ГПлПсПве пПвіЎПЌлеММя00:46

"ማግባት ለሚሹ” ዚቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር ኹምንም በፊት ዚጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባቜሁ፡፡ በሕይወታቜን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መሚዳት አለባቜሁ፡፡ ኹዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ ዚጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን ዹሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠውፀ እንዲህ ያለውንፊ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮውፀ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ኚድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው ዹሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው ዹሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው ዹሚለው? ኚዝሙት እንጠበቅ ዘንድፀ ራሳቜንን መቆጣጠር እንቜል ዘንድፀ ንጜህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድፀ በትዳር አጋራቜን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያቜሁ ይኌ ነው ዚጋብቻ ስጊታው ይኌ ነው ዚጋብቻ ፍሬውፀ ይኌ ነው ዚጋብቻ ጥቅሙ፡፡ ስለዚህ ልጆቌ! እማልዳቜኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታቜሁት ዓይናቜሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ ዚትዳር አጋርን ስትመርጡ ዚሀብት ጉዳይ ዚእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኟን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ ዚትዳር አጋርን መምሚጥ ድንቁርና ነውፀ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይቜላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር ዚምትመርጡት ሰው ኹምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልኚቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ ዚሚጠቅማቜሁ ይኌ ነውና፡፡ አባቶቜ ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለትፊ ሀብትን አላዚምፀ ዚንጉሣውያን ቀተሰብን አልተመለኚተምፀ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደሚገምፀ ወይም ይህን ዹመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደሚደሚም፡፡ ዚነፍስ ንጜህናን እንጂ፡፡ እናቶቜ ሆይ! ሎት ልጆቻቜሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋ቞ው፡፡ እናንተ ማግባትን ዚምትሹ ወጣቶቜ ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉትፊ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ ዚኚበሮንና ዚዋሜንት ጫጫታን፣ ሌላውንም ዚዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋቜሁ ቀን አታስቡ፡፡ ኹዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማቜሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደሚጋቜሁ እንደኟነ ትዳራቜሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ ዚሌለበት ኟኖ ይፀናላቜኋል፡፡ ይህን ያደሚጋቜሁ እንደኟነ፥ ሌላው በሚኚትም ተትሚፍርፎ ይመጣላቜኋል፡፡ ዹአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያቜሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡ እናንተ ልጃገሚዶቜ ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ ዚትዳር አጋራቜሁን ፍጹም ለማፍቀር ዚተዘጋጃቜሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደሚጋቜሁ እንደኟነ ቀታቜሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻቜሁ ዚምትልዋ቞ውን ዚሚያደርጉና በፍቅራቜሁ ዚሚንበሚኚኩ ይኟናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኟኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ ዚሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡ ዚቀት ዕቃዎቜን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ ዚሻጮቹን ማንነት አይተን፣ ዹዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው ዚምንሞምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ኹዚህ ዹበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ ዹገዛነው ዕቃ ቜግር ቢኖርበት ለሾጠልን ሰው መመለስ እንቜላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቀተሰቊቿ መመለስ አንቜልምፀ እስኚ ዕድሜአቜን ፍጻሜ ድሚስ ኚእኛ ጋር ነው ዚምትኟነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠሚት አመንዝራ እንኟናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ ዚሀገራቜሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡፀ ኚኹሉም በፊት ሕገ ቀተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡ - ዲያቆን ሔኖክ ጣሰው

Story

አለማዊ channel ያላቜሁ forward አርጉልኝ

ፕሮ቎ስታንት እና ሙስሊም ወንድም እና እህቶቜ ስለ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ዹማወቅ ፍላጎት ያላቜሁ ወይም ደሞ ወደዚ ሕይወት መቅሚብ ዚምትፈልጉ እንዲሁም ኊርቶዶክስ ሆናቜሁ ጥያቄዎቜ ያልተመለሰላቹ @yematbelawef dm ፃፉልኝ ዹማቀውን ለማስተማር ዝግጁ ነኝ

The words make my feel right 🀌🥹
The words make my feel right 🀌🥹

ዚት ጠፋቹ እሺ😭

Story

Vc ገብተን እንተዋወቅ እንዎ guys ?

Story