cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

መዝሙር ዘምር ዘምር አለኝ

መንግስተ ሰማዐያት ቀርባለችና ንስሀ እንግባ

Більше
Рекламні дописи
1 933
Підписники
-124 години
-187 днів
+8630 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

✞ፀጋህ ይብዛልኝ✞ ፀጋህ ይብዛልኝ ምህረትህ አይራቀኝ አማኑኤል ሆይ ስራ ደነቀኝ ተመስገን ልበል ላቅርብ ምስጋና 2 በአንተ ቸርነት ቆሚያለሁ እና 2 ፀጋህ በዝቶልኝ እዘምርልሃለሁ በምስጋና ላይ ምስጋና አበዛለሁ አለኝ ሺ ቃላት አለኝ ብዙ ቋንቋ አንተን መግለጫ ለዓለም የሚበቃ አዝ የተናገርከው የአሰብክልኝ ሆነ የልቤም መሻት ይህንን ነበረ አስተካከልከኝ ከኃያላን ጋራ አማኑኤል ሆይ እፁብ የአንተ ስራ አዝ በለምለሙ መስክ አሳድገህኛል ያን የጭንቁን ቀን አሳልፈህኛል የምስጋና እርሻ ሆነልኝ ደጃፌ አባት ሆይ ስልህ ማርማር አለው አፌ አዝ በአዝን ብደሰት ብወድቅም ብነሳ እስከ አሁን አለሁ ከአንተ የተነሳ መረቤን ጥዬ ተስፋ አደርግሃለሁ እንደ ምትሞላው እተማመናለሁ
Показати все...
👍 5
🌹ያችን ቀን እናፍቃለሁ🌹 ያችን ቀን እናፍቃለሁ አይቀርም ይሳካል ህልሜ ምስክር እሆነዋለሁ በአውደ ምረቱ ቆሜ ደግሞም ባይሆንልኝ ያሰብኩት በቀኑ ለኔ አስቦልኝ ነው አባት በመሆኑ ድንጋይ ዳቦ መስሎኝ ለማኘክ ስሞክር ጌታ ከለከለኝ ጥርሴ እንዳይሰበር አዝ... ስላደረክልኝ ስለ ፀሌቴ መልስ ተመስገን አምላኬ ስምህም ይቀደስ ያልተቀበልኩትም ያልሆነ በህይወቴ ለበጎ ነውና ተመስገን አባቴ አዝ...... እድል ፋንታየ ነህ ተስፋ አደርግሀለው የማዳንህን ቀን እጠባበቃለሁ አንተን ለናፈቀች ለተጨነቀች ነፍስ ትደርስላታለህ እንባዋን ልታብስ አዝ...... ወንድሞቸ ጠልተው ቢሸጡኝ ባንድነት በፊድፍራ ጎጆ ብኖር በባርነት በሀሰት ወንጅላ በወህኒ ባድር ለኔ መሰላል ነው መውጫ ወደ ክብር አዝ..... ልጁ ዳቦ ሲለው ድንጋይ የሚሰጠው ከሰው ልጆች መሀል ከቶስ እርሱ ማነው መልካም ካደረገ የምድራዊይዩ አባት ከዚህም ይሰፋል ያንተ መልካምነት
Показати все...
✞ የልቤን ሁሉ ✞ የልቤን ሁሉ ለማን ለማክር  እመቤቴ ሆይ ካንቺ በቀር  ለደካማ ሰው መጠጊያ እኮ ነሽ  ሀዘን ጭንቀቴን የምረሳብሽ  ቅዱሳን አበው አንቺን መረጡ ፪ ከሲኦል አለም ስላመለጡ  ጻዲቅ በስራው ያኔ ሲድን ፪ እጠራሻለው ድንግል አንቺን  አዝ ====== የጭንቄ ደራሽ አክሊሌ ነሽ ፪ ቂም በቀል አያውቅ የዋህ ልብሽ  ልቤ ለፍቅርሽ ሰፊ ስፍራ አለው ፪ በአዘንኩኝ ሰአት እጠራሻለው  አዝ ====== ዋሴ ነሽ ለኔ ድንግል እናቴ ፪ ስምሽ ጠበቀኝ ከልጅነቴ  ሁል ጊዜ ለኔ በጎ አረግሽልኝ  ምን ልበል ላንቺ ቃላታም የለኝ  አዝ ====== ላዘንኩኝ ለኔ ደስታዬ ነሽ ፪ ያረጋጋሽኝ ፈጥነሽ ደርሰሽ  ስምሽ ኃጥአንን የሚቀድስ፪ ከሞት ወደ ህይወት የሚመልስ  አዝ ====== የመንገዴ ስንቅ የረሀቤ መርሻ ፪ ለታመመ ሰው ነሽ መፈወሻ  ለተማጸነሽ በስምሽ አምኖ ፪ ማን አፍሮ ያውቃል አንቺን ለምኖ  
Показати все...
5👏 1
በማህፀን ቅኔ በማህፀን ቅኔ ለማርያም ተሰማ በተራራማ ሃገር በኤፍሬም ከተማ ዮሐንስ ይናገር በረሃ ያደገው ድንግል ስትናገር ምን እንዳዘለለው /2/ የእናቱ ማህፀን የቅኔ ርስት ሆነች ድንግል የአምላክ እናት ፊቱ ስለቆመች በሃሴት ዘለለ ዘመረ በደስታ ከድንግል ሲወጣ ታላቁ ሰላምታ አዝማች... በድንግል ማህፀን ስላየ ጌታውን ከመወለድ ቀድሞ ሰማነው መዝሙሩን ትንቢቱ ሲፈፀም በሆዷ ሲነግስ ሰገደ ለአምላኩ የስድስት ወር ፅንስ አዝማች... ጀመረ ስብከቱን ገና ሳይወለድ ተፈጥሮ መች ቻለ ነብዩን ለማገድ አፉ ተከፈተ በታላቅ ምስጋና በእናቱ ማህፀን ድምጽን አሰማና አዝማች... የዮሐንስ እና ኤልሳቤጥ ገረማት ልጇ በማህፀን ቅኔ ሲቀኝባት ድምጿን ከፍ አደረገች አለም እንዲሰማ ሞላት መንፈስ ቅዱስ ለመዝሙር ለዜማ
Показати все...
👍 1
መዝሙር 108👏 "በቃለ ስብሀት" ዘማሪ አቤል መክብብ👏
Показати все...
👍 1 1
እዩና እመኑ ሰዎች እዩና እመኑ ሰዎች ድንጋዩ ተፈነቃቅሏል ኢየሱስ በኩለ ሌሊት በሀይሉ ሞትን ድል ነስቷል/2/ እልልታ ለዚህ ይገባል ግርግርታ ለዚህ ይገባል የሞት ሀይል ተዋርዷል ዛሬ ሲኦልም ተመሰቃቅሏል/2/ መላዕክቱ ነጭ ለብሰዉ ምስራቹን አበሰሩ ተነስቷል ኢየሱስ ብለው ለዓለም እዲናገሩ/2/ 👥@yemezmurgetemochet.me/KIDAN_MEHRET_ENATEbot @EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs
Показати все...
8👏 1
#እርሱ_ነው_ቀን_የሚይወጣ ከዳን እስከ ቤርሳቤህ ዛሬ ሞልቷል ምስጋናህ ተነሳ ልቤ ዘምር ለጌታ ለእግዚአብሔር 3 አዝ።።።።።።።።።።።።።። በገና ተነስ እንዚራ ማዳኑን እንድናወራ ብትቀርቡ ብትከተሉ ሁላችው ሆሳህና በሉ 2 አዝ።።።።።።።።።።።።። እግዚአብሔር ዘመን ከሰጠ ይዘምር የተለወጠ እልልታ ይሁን ለስሙ ለዋጀን በወርቅ ደሙ 2 አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።። የክብሬ የቤቴ ጌታ የነፍሴ ባለውለታ ኤፉድ ነው በፍታ ነው ልብሴ ዘማሪ ነኝ ለንጉሴ 2 አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።። ሰገነት ላይ የወጣችው ዝምታን የመረጣችው ከአፋችው ወረት አይውጣ እሱ ነው ቀን የሚያወጣ 2 አዝ።።።።።።።።።።።።።።።
Показати все...
1
✞ሆሣዕና✞ ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና ሆሣዕና ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት ህፃናቱ ሁሉ ድንጋዮች ሳይቀሩ ለዘመሩለት ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ እርሱ የተባረከ ነው ቅዱስ ነው መንፈሱ ሰላምን የሚሰብክ የሚናገር ፍቅርን በአህያ ውርንጫ መጥቷል ንጉሣችን አዝ= = = = = ዘንባባውን ይዘው ህፃን አዛውንቱ ልብሳቸውን ሳይቀር አንጥፈው በፊቱ ሆሳሣና ብለው ዘመሩ በእልልታ ግባ ንጉሣችን የሠራዊት ጌታ አዝ= = = = = ዘመንን ለሰጠን እንዘምርለት የምስጋናን መስዋዕት በፊቱ እንሰዋለት እንኳን እኛን ቀርቶ ድንጋይ ያናግራል ከሚጠቡ አንደበት ምስጋናን ይወስዳል አዝ= = = = = መድሃኒት ለሰው ልጅ ስለተገለጠ የመርገም ጨርቃችን ስለተወጠ ሰላም በሰማያት ሆነ በምድር ክብርና ምስጋና ለእርሱ ለእግዚአብሔር አዝ= = = = = እኛ ለክርስቶስ እናስፈልጋለን ቅዱሳኑን ልኮ መፈታትን ይስጠን በትህትና ወድቀን በልባችን ይግባ እንደ ህፃናቱ እንያዝ ዘንባባ መዝሙር ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ የዮሐንስ ወንጌል ፲፪፥፲፫ መዝ ፰፥፪
Показати все...
✝️✝️✝️2አንችን ብቻ ቤተልሔም✝️✝️ ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ አንቺን ብቻ ቤተልሔም አንቺን ብቻ በዚያ ግርግም ዮሀንስነ በገሊላ በኤፍራታ አላየንም አንቺን ብቻ ቀራንዮ አንቺን በኮረብታ ዮሴፍንም አላየንም ሊጣስትራ ጎልጎታ አዝ... ገና በማለዳ በናዝሬቷ መቅደስ ገብርኤል በስራት ይዞ ከገሊላ ሲደርስ ያን ዜና ስሰሚ ደነገጥሽ በብርቱ አንቺ ብቻ ነበርሽ ብላቴናይቱ አዝ.... ሕፃኑን ስትወልጅ ግርግም የነበሩ የሉም በመከራው ቀራንዮን ፈሩ በልደቱ እንጂ የታሉ በሞቱ አብረሹ ነበርሽ አንቺ ብቻ እናቱ አዝ... የግብፅ በረሀ አብረውሽ የወጡ በቀያፋ ግቢ እንደምን አልመጡ እርሱ ለሚገረፍ እነሱ እያፈሩ አንቺን ብቻ ትተው በመንደር ነበሩ አዝ.. ሐሙስ ዕለት ፋሲካን ሲበሉ ያመሹ አርብ ዕለት ተነሥተው ከቶ ወዴት ሸሹ ቃል ገብተው ነበር ላይክዱት መሀላ ድንግል ካንቺ በቀር ማን ነበር ሌላ አዝ... በሠላሳ ዘመን በሥጋ ወራቱ መች ነበሩ ከቶ ደቀመዛሙርቱ የእጆቹን ታምራት ቀን ከሌሊት እያየሽ በቃሉ በርታት ፊት አንቺ ነበርሽ አዝ... ቤተልሄም ያሉ ቀራንዮ የሉም ቀራንዮም ያሉ ግርግም አልነበሩም በሆነበት ዘመን በመስቀል ሞቱ አብረሹ ነበርሽ አንቺ ብቻ እናቱ
Показати все...
👍 4
✞ ምስጋናዬን ✞ ምስጋናዬን ላምላኬ አቀርባለው በማደሪያው ገብቼ ሠግድለታለው ኤልሻዳይ ነው ጌታ ሁሉን ቻይ ይፈፀማል አምናለሁ የልቤን ጉዳይ(2) ዘንባባዬን ይዤ እደህፃናቱ ሆሣና ልበለው ሠግጄ በፈቱ ምንም ባዶብሆን እውቀት ቢጎድለኝ ለሥሙ ልዘምር ከልካይም የለኝ(2)          አዝ= = = = = አምላኬ በፈትህ ቃል አለብኝ እኔ ቋንቋዬ መዝሙር ነው ያንተ እደመሆኔ ባሚናዳ ደጃፍ በቅድመ ታቦቱ ያየክብርህ ውደር ጠራኝ ማህሌቱ (2)          አዝ= = = = = የህይወት ትርጉሜ አንተነህ ደሥታዬ ስምህን ማገልገል ክብሬነው ሥራዬ ለታመነው ጌታ ምስክር የሆኑ ከብረው ተመለሱ ለበረከት ሆኑ(2)          አዝ= = = = = መነሻዬ አንተነህ ጉልበቴና ክብሬ መድረሻዬም አንተ መደምደሚያ ቅጥሬ በፂሆን ተራራ ስትገለጥ ያኔ ነጩን ልብሥ አልብሠህ አስነሳኸኝ ለቅኔ (2)                     መዝሙር በ    ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮   
Показати все...
3👍 1