cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Dave ( ባለ በገና)🍎🍇🎸🪗

I looked, and rose up,Nehemiah 4:14 ☞በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ መሰናዶች ይቀርባሉ! ➩ #አዳዲስ_መዝሙሮች ➩ #ቆየት_ያሉ_ዝማሬዎች #መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎች ➩ #Live_WORSHIP_እና_studio_live_worship ➩ #ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እና የተለያዩ ትምሕርት ነክ ዝግጅቶች ይቀርባሉ። ለሃሣብ እና አስተያየት ደግሞ @Dave_one_Bot አለላችሁ።

Більше
Рекламні дописи
1 035
Підписники
Немає даних24 години
-177 днів
+55130 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

የአስደናቂዋ ሴት ማስታወሻ እዉነተኛ ታሪክ! በDave ባለ በገና የተሰናዳ. ክፍል 25. በዓለም የመጨረሻው ቦታ ሰሜናዊ ንፍቀ ክበብ፣ እልም ያለ በርሃ ሰው የማይኖርበት የበረዶ ስፍራ፣ ሳይቤሪያ ነው። ፡ ማንም በዚህ የግዞት ስፍራ ቢጣል ሮጦ ወይም ተጉዞ የትም አይደርስም፡፡ ሰፊ የበረዶ በረሃ ቀዝቃዛና አስቸጋሪ ቦታ ነው፡፡ በሳይቤሪያ በሌላው ዓለም እንደሚታየው አስራ ሁለት ሰዓት ፀሃይ አስራ ሁለት ሰዓት ጨለማ የሚባል ነገር የለም፡፡ ለስድስት ወር ጨለማ ሲሆን ለስድስት ወር ደግሞ ብርሃን አለ፡፡ ብርሃን ማለት የሚያቃጥል ጃንጥላ የሚያዘረጋ የፀሃይ ብርሃን ሳይሆን ለወጉ ያህል የሚታይ ብርሃን እንጂ፡፡ እነ አንድርያና በዚህ ስፍራ ነበር ለአስራዎቹ አመታት የሚሰቃዩት፡፡ ሳይበሪያ የምድር ሲዖል፡፡ መርዝ ጠጥተው ሆድቃቸውን ዘርግፎ እንዲገደሉ በታሰበበት ቀን ያልጠበቁት ነገር የገጠማቸው እስረኞች በሆነው እየተደነቁና እየተገረሙ እርስበእርስ መተያየት ሆነ ስራቸው፡፡ የሚተዋወቀውም ሆነ የማይተዋወቀው ሁሉ በግልፅ መተያየት ጀመረ፡፡ አንዱ የራሱን ቁስል ጉዳትና አካለሰንካላነት ረስቶ በሌላው ወገኑ ላይ በሚያየው ጉዳት ማልቀስና ማዘን ጀመረ፡፡ ምን ያህል እንደተጎዱ እንኳን ለማወቅ እድል የማይሰጥ እስርቤት መታጎር እጅግ አስከፊ ነው፡፡ በሳይቤሪያ የሆነውም ይህ ነው፡፡ ሁሉም የመርዶ ያህል እያለቀሰ መሬት እየደበደበ አንተንም እንዲህ አደረጉህ? አንቺንም እንዲህ አደረጉሽ? ጌታ ይመስገን!!፡፡ ስንት አመት ታሰርክ? አንተስ? አንቺስ? በሚል ጥያቄ ጨዋታው ደርቶ ለቅሶና ሳቅ ተቀላቅሎ አዲስ ትኩስ ሬሳ የወጣበት ቤት መሰለ፡፡ ‹‹እኔ እገሌ ነኝ እኔ ደግሞ እገሊት እባላለሁ፡፡ ጀኔራል እገሌ፣ መከላከያ ሚኒስትርና የባህር ኃይል ልዩ ኮማንዶ አዛዥ እገሌ ነኝ፤ የኮሚኒስት ተማሪዎች አባል ነኝ፤ እኔ ደግሞ ለአምስትደቂቃ የሰማሁትን ኢየሱስ አማኝ ነህ ተብዬ ተያዝኩ ያንጊዜ ሲይዙኝ አማኝ እንዳልሆንኩ ለማስረዳት ብዙ ጣርኩኝ ይሁን እንጂ የሚሰማኝ አጥቼ ታፍሼ ወደዚህ ገባሁ፡፡ እዚህ ከገባሁ በኋላ ግን ጣፋጩን ኢየሱስን አገኘሁት፡፡›› ይላል፡፡ በዚህ መሃል ነበር ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት አከባቢአስደንጋጭ ትረካ የተሰማው፡፡ እንዴት ወደ ሳይቤሪያ እንደመጣ አንድ ፀጉሩ የተጨፈረረ የቀኝ ዓይኑ በግርፋት የፈሰሰ ወገቡ በኃይለኛ ምት ተሰብሮ መቀመጥ ያልቻለ ሰው እየሳቀ ከፊቱ የደስታ ፈገግታ የድል ስሜት እየታየበት ተንበርክኮ መናገር ጀመረ፡፡ ያሳለፈው የእስር ዘመኑ እንዴት እንደተያዘ ከመያዙ በፊት ከነበረው ህይወት ይልቅ ተይዞ ወደዚህ የምድር ሲኦል ሳይቤሪያ ስለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተቀበለው መከራ ደስተኛ እንደሆነ ይመሰክራል፡፡ እርሱ ሲመሰክር እስረኞቹ በሙሉ እንባ በእንባ ሆነው ያደምጡታል፡፡ የኮሚኒዝምን ክብረ በዓል ለማክበር ከሰልፍ ተመልሰን ወደ መሰብሰቢያ አዳራሽ ስንገባ እህታችን እንበላትና አንድርያና ያ የተለመደው ኃይለኛ አነጋገርዋን ስትናገር አምላኬን ስትሳለቅበት ሰምቼ ማለፍ አቃተኝ፡፡ ሃሳባውያን አላችሁ? ከሌንን ወዲያ መሪ ከኮሚኒስት ወዲያ ፓርቲ በዓለም ላይ የለም ስትል ጊዜ ጌታዬ ከሁሉ በላይ መሆኑን መግለፅ እንዳለብኝ ልቤ መሰከረልኝ! ለመጣልኝ ሀሳብ እምቢ ማለት ስላልቻልኩ ወጥቼ ራሴን ገለጥኩ፡፡ ሌሎችም እንደዛው፡፡ ያን ጊዜ አንድርያና ጀርባዬንና ወገቤን በዚያ ጫማዋ ስትረግጠኝ እንደምንም ብዬ ‹‹እንወድሻለን›› ብያት እኛ እያለቀስን እስዋ እየሳቀች ተለያየን እዚህ ቦታ ከመጣሁ እነሆ አስራ ስድስት ዓመት አልፎኝ አስራ ሰባተኛዬን ልይዝ ነው፡፡ ጌታ ይመስገን፡፡›› አለ ሌላውም መናገር ጀመረ ‹‹አጠቃላይ ስብሰባ መሃል ሳለን ለብዙ ጊዜ ያስቸገረን ጉዳይ በድንገት ተሳካልኝና ሳላስበው በዚያ በቆምኩበት ስፍራ ‹ሃሌ ሉያ! ጌታ ይመስገን› ብዬ ተናገርኩ፡፡ ጉባዔው ለብዙ ጊዜ የተቸገረበትን የክዋክብት የብርሃን ዓመትና በጨረቃ ላይ ያለው ጉም ነገር ምንነት በምርምር በማግኘቴ ልዩ ነገር ሊሸልመኝ መንግስት ተዘጋጅቶ ሳለ ‹ሃሌሉያ በማለቴ ተደናግጠው ታላቁ ሰው የማይገባውን ነገር አመነ ተብዬ ሽልማቴ ቀርቶ ሳይቤሪያ ገባሁ፡፡ እዚህ ከመጣ ሃያ ዓመት ሞላኝ፡፡›› አለ ሁሉም በሳይበሪያ ያሉት ቅዱሳን በሚሰሙት ነገር እንባቸው በጉንጫቸው መሃል ይፈሳል፡፡ ይሁን እንጂ የሌሎቹ ለቅሶ ሌላ ነው የአንድርያና ለቅሶ ግን ሌላ ነበር፡፡ ** ሌላዋ ተነሳች እኔ በትምህርት ቤታችን የተማሪዎች ህብረት ሰብሳቢ ነበርኩ የሁለት ዓመት ቦይ ፍሬንዴ ለካ እኔ ሳላውቅ ጌታን ያመልክ ነበር፡፡ የመጨረሻ ስድስት ወራት ሁሉ ጠባዩ ፈፅሞ ተለወጠብኝ፡፡ መዝናናት መውጣት ሁሉ አቆመ፡፡ አንድ ቀን ስለኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ስለመሞቱ ታሪክ ሲነግረኝ በጣም ሳቅሁኝ፡፡ ያንን ታሪክ ስሰማ ከመገረሜ የተነሳ ስለ ሰው ኃጢአት ሲል ራሱን ለስቃይ ለስቅላት አሳልፎ የሚሰጥ እሱ ሞኝ መሆን አለበት ብዬ አሾፍኩኝ፡፡ ምናለ የአንተ ኢየሱስ ህይወት ያህል ነገር ለማይረባ ዓላማና ተከታይ ለማያገኝበት ፓርቲ ራሱን በከንቱ አሳልፎ ከሚሰጥ ቢቀርበት? ያሳዝናል አልኩት፡፡ ቢያንስ ዘመድ አዝማድ የለውም? መክሮ የሚያስተወው? ብዬ አስባለሁ፡፡ እሱ ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ለኔ መመስከሩን ቀጠለ፡፡ በመጨረሻም እሱ ጠፋብኝ ምናልባት በወጣበት ተይዞ አልያም ተገድሎ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ እሱ ይጥፋ እንጂ ያ የተናገረኝ ቃል ግን ሁል ጊዜ በልቤ ያቃጭላል፡፡ ሞቱ ስቅላቱ ኮ ስላንቺ ሀጢአት ብሎ ነው ያለኝ ቃል እረፍት ነሳኝ ፡ እኔን ሳያውቀኝ ስለኔ ሀጢአት ሲል የሚሞት ማነው? በሚል ጥያቄ ስላለስ ቀናት አለፉብኝ፡፡ በመጨረሻም ጌታን ባገኘሁ በዓመቴ በአንድርያና ልዩ ትዕዛዝ ወደ ዚህ ወደ ጌታ ቤት የህይወት ማጣሪያ ወንፊት ስንዴና እንክርዳድ መለያ ሳይቤሪያ መጣሁ፡፡ ዛሬ አስራ ስድስት ዓመት ከአራት ወር ሆኖኛል፡፡ጌታ ይመስገን፡፡ አንድርያና ባለችበት ቦታ ጌታ ይባርካት ስለእርስዋ መፀለይን አናቋርጥም ወገኖቼ ሳዖልን የለወጠ እሱዋንም ይለውጣታል፡፡ ደግሞም ውደድዋት፡፡›› በማለት ስትጨርስ ሌሎችም ቀጠሉ በታሪካቸው መጨረሻ ላይ ንግግራቸውን የሚቋጩት ‹‹አንድርያና ልካኝ አንድርያና ይዛኝ .... አንድርያና ገርፋኝ፡፡›› በማለት ነበር፡፡ ክፍል 26 ይቀጥላል. ቻናላችንን ለመቀላቀል https://t.me/Heavenly_Grace_1 በምለዉ ልንክ በኩል ገብተው ጆይን ይበሉ። ለሃሳብ እና አስተያየት ደግሞ፣ @Dave_one_Bot የምለዉን ይጠቀሙ። ሼርም እንዳይረሳ!
Показати все...
Dave ( ባለ በገና)🍎🍇🎸🪗

I looked, and rose up,Nehemiah 4:14 ☞በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ መሰናዶች ይቀርባሉ! ➩ #አዳዲስ_መዝሙሮች ➩ #ቆየት_ያሉ_ዝማሬዎች #መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎች ➩ #Live_WORSHIP_እና_studio_live_worship ➩ #ቅዱሱ የእግዚአብሔር ቃል እና የተለያዩ ትምሕርት ነክ ዝግጅቶች ይቀርባሉ። ለሃሣብ እና አስተያየት ደግሞ @Dave_one_Bot አለላችሁ።

1
Share your grace and vision with your family through @Dave_one_Bot!
Показати все...
👌 1
📌ራሴን ስመለከት እንዴት ልድን እንደምችል አይታየኝም ክርስቶስን ስመለከት እንዴት ልጠፋ እንደምችል አይታየኝም፡፡ ማርቲን ሉተር Join and follow👇👇👇👇👇👇 @Heavenly_Grace_1
Показати все...
👍 1
👍 1🔥 1
ሕይወት ኢየሱስ ነው ✨ " ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:2) በሞት ተሸንፎ ለወደቀው አለም፣የተገለጠው ሕይወት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ⚡ኢየሱስ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የዘላለም ሕይወት ሕይወት ነው።(1ኛ ዮሐንስ 5:20) ⚡በጥንታዊው ሰው አዳምና በአጋሩ በሄዋን አለመታዘዝ ምክንያት፣ሕይወት የውሃ ሽታ ሆኖ፣የገነት ደጃፎች ተዘግተው፣የስኦል መግቢያ በር ተከፍቶ፣ከአበል ግድያ እስከ ክርስቶስ መስዋእትነት ድረስ እጅግ ብዙ ነፍሳትን ውጧል ሞት በሀጥያት ምክንያት የመጣብን የበደላችን ዋጋ ስለሆነ፣ከህይወት ተለይተን ኖረናል። ⚡የዲያብሎስን ስራ እንድያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ እንዳለው (1ዮሐንስ 3:18) ጌታችን የመጣው የተተበትበውን የሞት መረብ በጣጥሶ ነፃነት ልሰጠን ነው። ⚡ ወንድሞቼ ያለ ምንም ጥርጥር አንድ ነገር ላስረግጣችው ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ሕይወታችን ነው፣ያውም ደግሞ የዘላለም ሕይወት። ⚡የዘላለም ሕይወት ማለት፣ እግዚአብሔር ያዘጋጀልን በኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት የወረስናት(የምንወርሳት)ዮሐንስ በራዕይ ከሰምይ ስትወርድ ያያት፣አድስ ሰማይና አይስ ምድር ናት።በዚህች ዘላለማዊ እና ሰሜያዊ አገራችን፣ጩኽት፣ስቃይ፣ህመም፣ሃዘን ወዘተ አያገኙንም። 👉 " እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።" (የዮሐንስ ወንጌል 5:24) 👉ዮሐንስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁷ በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤ ²⁸ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም። 👉 follow @tiwuldnenaterf
Показати все...
🙏 3👍 1
👍 1
5
👏 2😁 1
2👍 1