cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Awtar Express አውታር ሚዲያ

በቻናሉ #ፈጣን ፥#ትኩስ #ወቅታዊ እና #አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል ! Get updated information on our Channel Share For Your Friends ለማንኛውም ሀሳብ፣አስተያየት፣ጥቆማ እና ማስታወቂያ ለ ማሰራት ከ ስር ባለው ሊንክ ላይ ይፃፉልን ። @awtarex

Більше
Рекламні дописи
457
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
-830 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступнеДивитись в Telegram
በጎንደር ቡዳ ሁነህ እህቴን በልተሃታል በማለት የግድያ ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጣ ተከሳሽ  ደሴ ቢወጣ ጎበዜ የተባለ ግለሰብ ሆን ብሎ ሰው ለመግደል አስቦ ታሕሳስ 8 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 4:00 ሲሆን ምዕራብ ደንቢያ ወረዳ ጫሒት ከተማ ቀበሌ 02 ስላሴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራ ልዩ ቦታ ሟች አቶ ግርማው አድማስ ይባል የነበረው ከከተማ አመሽቶ ወደ መኖርያ ቤቱ በመሔድ ላይ እንዳለ ተከሳሽ ክላሽ ጠመንጃ ይዞ መንገድ ጠብቆ በመቆየት እህቴን ወ/ሮ አዲሴ ቢወጣን ቡዳ ሆነህ የበላሀት አንተነህ  በማለት በያዘው ክላሽ ጠመንጃ አንድ ጥይት ተኩሶ ማች አቶ ግርማው አድማስን መትቶ ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል። የምዕራብ ደንቢያ ፓሊስ ጽ/ቤት ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ አጣርቶ ለማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ በመላክ የዞን ዐቃቤ ሕግ የተላከለትን የምርመራ መዝገብ መርምሮ የኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 539/1/ሀ/ የተመለከተውን ጠቅሶ ክስ መስርቶበታል። የተመሰርተውን ክስ ለማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በማቅረብ ጉዳዩ በክርክር ቆይቶ በመጋቢት 06 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ባቀረበው የመከላከያ ምስክር የዐቃቤ ሕግን ክስ እና ማስረጃ  ማስተባበል ባለመቻሉ በተከሰሰበት የወንጀል ሕግ አንቀፅ 539(1)(ሀ) ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ፍ/ቤቱ መወሰኑን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በላከው መረጃ ተመላክቷል። መናኸሪያ ሬዲዮ
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አገኘች በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አግኝታለች፡፡ ትላንት በተደረገው ከ23 አመት በታች የነጠላ ወንዶች ብስክሌት ውድድር ኪያ ጀማል 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝቷል። ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ ሞሪሺየስ 3ኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች። በብስክሌት ኢትዮጵያ የመጨረሻ ውድድሯን በዛሬው ዕለት በድብልቅ ዘርፍ ታደርጋለች። በሰለሞን በቀለ [FBC]
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አርሰናል 🙈 የቼልሲን ካሶቶኒ(ጋምባሌ) ለብሶ ራሱ ቼልሲን የገጠመው አርሰናል ተሸንፏል!!! አርሰናል ለወሳኝ ጨዋታ ወደ ቼልሲ ሜዳ ቢያቀናም ተመሳሳይ ካሶቶኒ ይዞ በመምጣቱ ጨዋታው ለ30 ደቂቃ ተራዝሟል። በመጨረሻም አንድ የክለቡ ሰው ከቼልሲ ሱቅ የቼልሲን ካሶቶኒ በመግዛት አርማው ላይ ማስቲሽ ለጥፎ ለጨዋታው ቀርቧል። አርሰናል ሴቶች 3ለ1 ከመረታታቸው በላይ የካሶቶኒው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል!😝 BBC
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ 430 የጋራ መኖሪያ ቤቶች #ለመምህራን በዕጣ መተላለፋቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል። ዛሬ የተላለፉት ቤቶች ከዚህ በፊት ለመምህራን ተላልፈው ከነበሩ 5,000 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ውል ሳይፈጸምባቸው የቆዩ 435 ቤቶች ከተለዩ በኃላ መሆኑን ገልጸዋል።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የቲክቶክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የመተግበሪያው ተጠቃሚዎች የአሜሪካን ውሳኔ እንዲታገሉ ጥሪ አቀረቡ የቲክቶክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሹ ዚ ቼው የመተግበሪያው ተጠቃሚዎች አሜሪካ ቲክቶክን ለማገድ የምታደርገውን ጥረት እንዲታገሉ ጥሪ አቅርበዋል። የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት በባይትዳንስ የሚተዳደረው ቲክቶክ በአሜሪካ እንዲታገድ የሚያስችል ረቂቅ ውሳኔ በድምጽ ብልጫ አፅድቋል። በምክር ቤቱ የፀደቀው ረቂቅ በሴኔቱ ተቀባይነት ካገኘ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እንደሚፈርሙበት ገልጸዋል። ይህን ተከትሎም የቲክቶክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቲክቶክን ማገድ በሺዎች የሚቆጠሩ አሜሪካውያንን ህይወት አደጋ ላይ መጣል ነው ብለዋል። የምክር ቤቱን ውሳኔ አሳዛኝ ያሉት ሥራ አስፈጻሚው ይህ አካሄድ ከባድ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል ሲሉም አስጠንቅቀዋል። ውሳኔው የተንቀሳቃሽ ምስሉን በመጠቀም የሚተዳደሩ አሜሪካውያንን አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉም ሁኔታው በደንብ እንዲጤን ጠይቀዋል። በምክር ቤቱ የፀደቀውን የዕግድ ረቂቅ ለማስቀየርም ቲክቶክ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥልም አስረድተዋል። ከ170 ሚሊየን በላይ አሜሪካውያን ቲክቶክን እንደሚጠቀሙ መረጃዎች ያመላክታሉ። Arada_Fm
Показати все...
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በአራት በመቶ ነፃ ቀዘፋ የውሃ ዋና ውድድር ኢትዮጵያ 4ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች በአፍሪካ ጨዋታዎች በሴቶቹ ዘርፍ በተደረገው የአራት በመቶ ነፃ ቀዘፋ የውሃ ዋና ውድድር ኢትዮጵያ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። አትሌቶቹ ርቀቱን ለመጨረስ 5 ደቂቃ 18 ሰከንድ ከ96 ማይክሮ ሰከንድ ወስዶባቸዋል። ግብፅ በርቀቱ የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን በማሻሻል የወርቅ ሜዳሊያ ስታገኝ፤ አልጄሪያ እና ዚምባቡዌ የብር እና የነሀስ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆነዋል።
Показати все...
ተማሪዎች በትራማዶል ሱስ ተለክፈዋል! “ከድንገተኛ ሞት እስከ ቀጣይነት ያላቸው የጤና እክሎች ያስከትላል“ (ዶ/ር መስፍን በኃይሉ) ትራማዶል የሚባለው የህመም ማጥፊያ መድሐኒት ያለ አግባብ በወጣቶች ኪስ ተዘውትሯል። ከስምንተኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በዚህ መድሐኒት ሱስ ተለክፈዋል። መድሐኒቱ ያለ በቂ ምክንያትና ተዘውትሮ ሲወሰድ ወደ ሱስነት ይሸጋገራል። አንድ የገጠመኝ ተማሪ በቀን 26 ትራማዶል ክኒን መውሰድ ደረጃ የደረሰ ነበር። በቀን 26 ማለት ለመውሰድ ቀርቶ ለመቁጠር የሚታክት ነው። ሱስ የማያደርገው የለምና እያደረገ ቆይቷል። ከዚህ ደረጃ የደረሰው በአንድ ቀን አልነበረም። በቀን አንድ ተጀምሮ ቀስ በቀስ መላመድ ስላለው የሚፈለገውን የሱስ ቃና ስለማያስገኝ መጠኑን እንዲጨምር በሱስ ትዕዛዝ ሁለት፣ አራት፣ ስድስት፣.....እያለ ሀያ ስድስት ክኒን ላይ ደርሷል። የትራማዶል ሱስ በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ የሚገኝ አደገኛ የስነ አእምሮ ችግር ነው። ከመድሐኒት ጋር ተያይዞ የሚመጣ የስነ አእምሮ ችግር የማይነካው ማዕዘን የለም። የግለሰብ፣ የቤተሰብና የማህበረሰብ ጤና፤ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብሮችን አደጋ ላይ ይጥላል።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ግንቦት 20 በሀገር አቀፍ ከሚከበሩ በዓላት ዝርዝር ውስጥ እንዲወጣ ተደረገ‼️ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብ በዓላትንና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በተረቀቀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ረቂቁን ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል። መንግሥት በ1967 ዓ፣ም የወጣውን ረቂቅ አዋጅ ሙሉ በሙሉ በመቀየር አዲስ ረቂቅ አዋጅ ያዘጋጀው፣ ነባሩ አዋጅ የሕዝብ በዓላቱን ዝርዝር የአከባበር ስነ ሥርዓት የማይገልጽና በዓላቱ ሊሰጣቸው የሚገባቸውን የመገናኛ ብዙኀን ሽፋን የማይዘረዝር በመኾኑ እንደኾነ ተገልጧል። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ታስበው ለሚውሉ ኹለት አገር ዓቀፍ በዓላት፣ አራት ብሄራዊ በዓላት እና ስምንት የሐይማኖት በዓላት ዕውቅና የሰጠና የአከባበር ስነ ሥርዓታቸውን የደነገገ ነው። ረቂቅ አዋጁ ግንቦት 20ን በአገር ዓቀፍ ደረጃ ከሚከበሩ በዓላት ዝርዝር ውስጥ አስወጥቶታል።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በ14 ዓመቷ 3 መፅሐፍትን በማሳተም በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ስሟን ያሰፈረችው ታዳጊ በልጅነት ዕድሜ የ3 መፅሐፍት ደራሲ መሆን አይደለም፤ መፅሐፍትን አንብቦ ለመረዳት በአብዛኛው የወላጆች ድጋፍ የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው። ለ14 ዓመቷ ደራሲ ሪታ ሁሴን አልሃዚ ግን ይህ ከባድ አልነበረም። ታዳጊዋ ደራሲ ሪታ ሁሴን አልሃዚ የተወለደችው በምስራቃዊ ሳኡዲ ዓረቢያ ዳኅራን ግዛት ውስጥ ነው። ዓረብኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፋ መናገር እና መፃፍ የምትችለው ሪታ፤ አሁን ላይ ጃፓንኛ ቋንቋ እየተማረች ነው። ሪታ የ6 ዓመት ሕፃን እያለች ነበር ወላጆቿ ለትምህርት ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሌላ ሀገር ሲሄዱ የስኬት መንገዷን አንድ ብላ የጀመረችው። የተለያዩ አስተማሪ ታሪኮችን የማጥናት፣ የማወቅ እና የማንበብ ልምድ የነበራት ሪታ፤ በ7 ዓመቷ ወደ ቤተ-መፅሐፍት በመሄድ አጫጭር ታሪኮችን ማንበብ የጀመረው ጉዞዋ ዛሬ ላይ ገና በ14 ዓመቷ 3 መፅሐፍትን በማሳተም በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ስሟን እንድታሰፍር አግዟታል፤ EBC
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በግራንድ አፍሪካን ራን ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት ተዘጋጀ በአሜሪካ ዋሽንገተን ዲሲ በሚካሄደው የ’ግራንድ አፍሪካን ራን’ ለሚሳተፉ አትሌቶች የመኪና ሽልማት መዘጋጀቱ ተገለፀ፡፡ ግራንድ አፍሪካን ራን በየአመቱ ጥቅምት በገባ በሁለተኛዉ ቅዳሜ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ የሚደረግ የ5 ኪሎሜትር የሩጫ ዉድድር ነዉ። በዚህ ውድድር ለሚሳተፉ በአሜሪካ ግዙፉ የቶዮታ መኪና አከፋፋይ የሆነው አሌክሳንደሪያ ቶዮታ በዉድድሩ ላይ ለሚሳተፉ ሰዎች የመኪና ሽልማት ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። የውድድሩ ተሳታፊዎች አንደኛም ሆነ መጨረሻ ቢወጡ የመኪና ሽልማቱን የማሸነፍ እኩል እድል ያላቸዉ ሲሆን በዉድድሩ ቀን በሚወጣ የሎተሪ እጣ የመኪናዉ አሸናፊዉ ይለያል ተብሏል። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሚሳተፉበት ዉድድሩ ለቀጣዩ ወር ከግንቦት ጀምሮ ምዝገባ እንደሚከናወን አዘጋጆቹ ይፋ አድርገዋል። በዚህ ውድድር ከዚህ ቀደም ደራርቱ ቱሉ፤ ቀነኒሳ በቀለ፣ ጥሩነነሽ ዲባባ፣ ገንዘቤ ዲባባ፣ ስለሺ ስህን፣ ሚሊዮን ወልዴ፣ በላይነህ ዴንሳሞ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ብርሃኔ አደሬ፣ ቁጥሬ ዱለቻ እና ሌሎች ስመ ጥር አትሌቶች ተሳተፈውበታል፡፡ (ኤፍ ቢ ሲ)
Показати все...