ዕቅበተ አእምሮ
Відкрити в Telegram
ይህ #Telegram# ቻናል የወለህ ነቅዐ ሕይወት የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ትምህርት ቤት ገጽ ነው ። የተከፈተበት ዓላማ ኦርቶዶክሳዊ አእምሮን ለመጠበቅና አንድነትን ለመመለስ ነው ። የሚከፋፍሉ አጀንዳዎችን ፖስት ማድረግ ክልክል ነው።።።።
Показати більше1 997
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
1 997
ለትውልዱ ልትደርሱለት ይገባል፡፡
12/7/2017 ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በዋግ ኽምራ ሀ/ስብከት የሚገኘውን የወለህ ነቅዐ ሕይወት የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ ቤት በመንፈሳዊ ጉብኝት ጎበኙ፡፡ ጉባኤውንና ደቀ መዛሙርቱንም ባረኩ፡፡
ብፁዕነታቸው በጉባኤው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ለቤተ ክርስቲያን ዋና መሠረቱ ጉባኤ ቤት ነው ያሉ ሲሆን ከዚህም አያይዘው ድሮ መምህራን በጉባኤ ብቻ እንጅ በዓውደ ምሕረት አይገኙም ነበር፡፡ አሁን ግን እንደ አባ ገብረ ኪዳን፣ እንደ መ/ር ኀይለ ማርያም፣ እንደ መ/ር መዝገበ ቃል ያሉ መምህራን በጉባኤውም በዓውደ ምሕረቱም ብቅ ማለታቸው ለእናንተ እድል ነው፡፡ በሕዝብ ፊት እንዴት መቅረብ እንዳለባችሁ ይነግሯችኋል ብለዋል፡፡
አክለውም ወጣቱ ትውልድ ግማሹ በግዴለሽነት፣ ግማሹ በኑፋቄ ትምህርት ተወስዷል፡፡ ስለዚህ ልትደርሱለት ይገባል በማለት መክረዋል፡፡
1 997
።።።። ዕቅበተ አእምሮ።።።።
አካላችን ሁሉ ቢደክም እንኳ መንፈሳችን ብርቱ እንደ ሆነ እንዲቀጥል ከፈለግን አእምሮአችንን መጠበቅ ግዴታችን ይሆናል የሰው ሙሉ ኃይሉ ያለው በአካሉ ሳይሆን በአእምሮዉ ነው።
የአእምሮ ብርታት ካለ ዘንድ የሁለመናችንን ኃይል አናጣም ያለአእምሮ ጥበቃ የሚፈጸም ማንኛውም ሥራ ፈራሽ ነው።
ያለ እሱ ምን ሥራስ አለ?
ነቢያት የተናገሩት
ክርስቶስ ያስተማረው
ሐዋርያት የሰበኩት
ሊቃውንት የተረጎሙት
መናንያን የኖሩት ሁሉ ዕቅበተ አእምሮ ነው
ያለ ዕቅበተ አእምሮ ስብከት የለም ምኑ ይሰበካል?
ልብ በል አስተውል ሰውን ማዳን ከአማረህ የዕቅበተ አእምሮን አካሄድ ልብ ብለህ መርምር።
1 997
#ከመምህር_ገብረ_መድኅን_እንየው
#የኮሶበር_መንበረ_ሥላሴ_ቤተ_ክርስቲያን
ከእንጅባራ፦ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት ሕፃናትን እንዲህ እያስተማረ ነው።
በእንጅባራ ከተማ ኮሶበር ሥላሴ ያለው የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርት ቤት ያሉ ደቀ መዛሙርት ከወንበር ጎን ለጎን ሕፃናትን በማስተማር ላይ ናቸው።
ከኮሶበር ሥላሴ ሰበካ ጋራ አንድ በመሆን በትውልድ ግንባታ ላይ እየሠሯቸው ያሉ ሥራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው።
ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤትም ባጭር ጊዜ ከዚህ ደርሶ እየሰጠ ያለው አገልግሎት እጅግ በጣም አስደሳች ነው።የበለጠ ጉባኤን ብናሳድገው የበለጠ ያገለግለናል።
ጉባኤ ቤት የሚያድገው ጥሩ መምህር ሲኖር ነው።ለዚህደግሞ መምህር ሠናይ ክንዴ ያለ ዕረፍት ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤትን የትውልድ ማስተማሪያ ማዕከል አድርገው እየሠሩት ያለው የመምህርነት እና የአስተባባሪነት ሥራ ቀላል አይደለም።
ለአብነት ትምህርት መስፋፋት ሌት ከቀን እየደከመ ያለው ሰበካ ጉባኤ፣የእንጅባራ ማዕከል ማህበረ ቅዱሳን መመስገን ይገባችኋል።
የኮሶበር ሥላሴ ሰበካ ጉባኤ አባላት ሩቅ አሳቢ በመሆናቸው ባጭር ጊዜ ውስጥ ጉባኤ ቤቱን ከዚህ አድርሰው አሳይተውናል።
የበለጠ የትውልድ ማስተማሪያ ማዕከል እንዲሆን ሁሉም የድርሻውን ይወጣ።
1 997
አክሱም ላሊበላን የገነባው አእምሮ፤
ያነፀው ዐዋቂ ዛሬ ቢኖር ኖሮ፤
ይወቀስ፣ ይሰደብ፣ ይወገዝ ነበረ፤
እንኳን እሱ ሞቶ ሥራው ብቻ ቀረ፡፡
ነፍስ ይማር አባቴ!
ወደ ኋላ
1 997
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
ዓቃብያነ ሃይማኖት
የሆኑ ሰዎች በምድር ላይ እድሜያቸው አጭር ነው ታሪካቸው ግን ብዙ ነው።
ከዕቅበተ እምነት ህሊና የራቀ ሰው የምድር እድሜው ሊረዝም ይችላል ሐዋርያዊት እውነትን በምሥክርነት ስለማይናገር የሚጣለው ላይኖር ይችላል።
ቅዱስ እስጢፋኖስ ደፍሮ ከመመሥከሩ የተነሣ እድሜው አጭር ነው።የሰማዕትነት ታሪኩ ግን ብዙ ነው።
ለዘለዓለሙም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይነገርለታል።ሰማዕትነት ከላይ ክርስቶስን ከታች እስጢፋኖስን ትመለከታለች።
እንደ እስጢፋኖስ እውነተኛ ክርስቲያን ስሆን እድሜያችን አጭር ተግባራችን ግን ብዙ ይሆናል።ግብ.ሐዋ.፯፥፶፩።
ቤተ ክርስቲያንን ከተጋረጠባት የህልውና መከራ ለመታደግ ሰማዕታት ያስፈልጋሉ።
አሁን መናገር እንችላለን ነገ ግን እንኳን መናገር መኖር ሁሉ አንችላልም።
ዕቅዱ እንደዚያ ነው።
የቤተ ክህነት መዋቅርን ተስፋ የሚያደርግ ሰው ግን ጉም አፋሽ ወፈ ነዳሽ ነው። እንኳን ለምእመኑ አለኝታ ሊሆን ለራሱም አይሆን።
መፍትሄው እኛ እና እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ነገ የማሸተው ሰው ህሊናው ያመረምራል ማለት አይቻልም።እስቲ ከዛሬ ይልቅ ነገን በህሊና አሽቱት??
1 997
"እጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ-የአንበሳ ደቦል ሆይ ተኛህ አንቀላፋህ በትንሣኤህ አንሣኝ"
እንኳን አደረሳችሁ በዓለ ትንሣኤው የመነሣታችን መንሥኤ ይሁንልን።
ከወለሕ ጉባኤ ቤት
