cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ድምፅ ማጉያ🎤A𝖒𝖕𝖑𝖎𝖋𝖎𝖗𝖊🎧

🎤የተደበቁ እና ብዙ ሰዎች ሊሰሙት የሚገባቸውን ጉዳዮችን እያነሳን የምንወያይበት፣ 🎤አጀብ የሚያስብሉ ትዝብቶችንም የምንነጋገርበት፣ 🎤በሕይወታችን ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ድንቅ ምክሮችን የምንመካከርበት፣ 🎙ብቻ በጥቅሉ የሚፈይዱንን ነገሮች ብቻ የምናጎላበት ብቸኛ ሚዲያ #ድምፅ_ማጉያ

Більше
Рекламні дописи
196
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Repost from N/a
Фото недоступнеДивитись в Telegram
እኛን ሳያማክሩ! ጫማ መግዛት እንዳይሞክሩ!
Показати все...
አመስግን ! በጠዋት ተነስተህ ማማረር አትጀምር ነቅተሀል እኮ ስለዚህ ለተሰጠህ ትልቅ እድል ፈጣሪህን አመስግን ደስ ይበልህ ገና ከእንቅልፍህ ስትነቃ ይሄ ጎድሎኝ ያን አጥቼያለሁ አትበል ከሁሉም በላይ ህይወት አግኝተሀል እኮ ስለዚህ ደጋግመህ አመስግን ! ሁሌም ደስተኛ፣አመስጋኝ፣ለመሆን የጎደለህን ሳይሆን በዚህ ሰአት ያለህን ነገር አንድ በአንድ ከ እራስ ፀጉርህ እስከ እግር ጥፍርህ ያለዉን ቁጠር፣በ አከባቢህ ያለዉን መልካም ነገር ሁሉ ተመልከት።እጅግ ብዙ ነገር ተሰጥቶሃል ማመስገኛ።ሁሌም የምስጋና አይኖችን ክፈት። መልካም እለትእሁድን ቀን ተመኘሁ🙏
Показати все...
Repost from N/a
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Item             VICTORY    Perfume Brand           victory maxo perfum Item form    liquids Volume        100ml 🌍 ለክፍለ ሀገር ደንበኞች ያሉበት ድረስ እንልካለን       📍አድራሻ፦ አዲስ አበባ እና ናዝሬት                     https://t.me/eyufashion19 @eyufashion2022                           📱09-4848-6666
Показати все...
የሚከተሉትን 8 ፍሬ ሀሳቦች ዘወትር ልብ በል። #1 እኔ ምርጥ ነኝ ብለህ ራስህን ንገረው። #2 ያሰብከውን ነገር እሰራዋለሁ(አደርገዋለሁ) ብለህ እመን። #3 ምንጊዜም ፈጣሪዬ ከእኔ ጋር ነው ብለህ ራስህን አበርታው። #4 አሸናፊ እንደሆንክ ውስጥህን ንገረው #5 ጠዋት ስትነሳ "ዛሬ ቀኑ የእኔ ነው" ብለህ በመልካም መንፈስ ቀንህን ጀምረው። #6 መቼም ቢሆን ተስፋ አትቁረጥ ነገ ምን ይዞልህ እንደሚመጣ አታውቅምና። #7 ብቻህን ስትሆን ስለምታስበው ነገር ተጠንቀቅ። #8 ከሰው ጋር ስትሆን ስለምትናገረው ነገር ተጠንቀቅ። ምክንያቱም ንግግርህ እና አስተሳሰብህ ልክ እንደ ጦር መሳሪያ አደገኛ ሊሆን ይችላል። የሌሎችን ስሜት ከመጉዳት ተቆጠብ። መልካም እሁድን ተመኘንላችሁ🙏 👇👇#በቅንነትሼር👇👇 @everthingspossible
Показати все...
ዳን አድማሱ ❤️ከፍቶሽ እንዳላይ❤️ ከፋኝ ያንቺን እምባ ካይንሽ ሳየው አዝኗል ለካ ልብሽ ደስታም የለው እንኳን አዝነሽለት ይህን አለም ስቆም የሚሞላ ከቶ አይደለም ለሀዘን ፊት አትስጭው ጭራሽ ህይወት ላትኖሪያት ደግመሽ ለኔ ደስታዬ ነው ብታይ ምንም አይኔ ከፍቶሽ ባላይ ጸሀይ ባትወጣ ቢያም ደመናው ቢከብድሽ እንኳን እሾህ ጋሬጣው ለቀን አለቃም ቀን አለውና አሮጌው በአዲስ ይተካ ገና ቀኑም ቢጨልም ሰማዩም ቢመሽ ጠዋት ይሆናል ይነጋል አይዞሽ ነገን ለሚያስብ ተስፋ ላዘለ ሲያድር ከዛሬ ሌላ ቀን አለ ╔═══════ ೋღ❤ღೋ ═══════╗ ೋ ❤I LOVE YOU SO MUCH❤ ೋ ╚═══════ ೋღ❤ღೋ ═══════╝
Показати все...
ወደ ግብህ ከመድረስ በፊት ካቆመክ ወኔ ቢስ ነህ ማለት ነው ወኔ ቢስ አያሸንፍም! አሸናፊ ደግሞ ወደ ኋላ አይመለስም። መልካም ቅዳሜ ተመኘንላችሁ🙏 👇👇#በቅንነትሼር👇👇 @everthingspossible
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
🌹♥️🌹የሴት ጓደኛ ለመያዝ አስበህ ታውቃለህ ምን ልበላት ብለህ ቃላትስ አተህ ታውቃለህ🌹🌹 እንግዲያውስ የፍቅር ቃላት ፍለጋ አበቃ በቀላሉ ማግኘት ትችላለህ🥰🌹👇🌹👇🌹
Показати все...
🖤💜የፍቅር ቃላቶች ለማግኘት💜🖤
🖤💜የፍቅር ታሪኮችና ግጥሞች 💜🖤
💜JOIN💜
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ ጥንታዊት፣ታሪካዊት፣ብሔራዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በህግና በሥርዓት የምትመራ፣የአገራችን ሕዝቦች ሁሉ የመልካም ሥነ ምግባር ባለቤቶች በመሆን የመከባበርና የመደማመጥ ባህል በአገራችን እንዲዳብር ዘርና ቀለም፣ቋንቋ ሳትለይ ሁሉንም ያስተማረች፣የሥነ ምግባርና የባህል መሰረት መሆኗ የማይካድ ሀቅ ነው። ቤተ ክርስቲያናችን ፈተናዎች በሚገጥሟት ጊዜ ሁሉ በትዕግስትና በጥበብ፣በሰላማዊ መንገድ ብቻ የመፍታት ልምድና ተሞክሮ ያላት ተቋም ስትሆን ሕዝበ ክርስቲያኑም አባቶቹ የሚሉትን የሚያዳምጥ ከጠብና ግርግር ራሱን በማራቅ ጸሎትና ትዕግስትን የሚያስቀድም በዚሁ መንገድ ብቻ ፈተናዎችን በድል አድራጊነት የሚወጣ መንፈሰ ጠንካራና ሃይማኖተ ጽኑዕ ሕዝብ ነው። በአሁኑ ወቅት ሃይማኖቷን፣ ክብርና ልዕልናዋን በሚፈታተን ደረጃ የገጠማት ችግርም በህግና በህግ አግባብ ብቻ የሚፈታ በመሆኑ የ ቤተ ክርስቲያናችን ጉዳዩን የአገራችንን ህግጋት መሰረት በማድረግ መፍትሔ እንዲያገኝ ለማድረግ ህጋዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ትገኛለች። ይሁን እንጂ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያናችን ልጆች ችግሩን ባልተገባ መንገድ መፍታት እንደሚቻል በማመን ከቤተ ክርስቲያናችን አሠራርና ዓላማ ውጪ በሆነ መንገድ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘዋወሩ መልዕክቶች ምስክር ናቸው።ይህ አይነቱ ድርጊት ከቤተ ክርስቲያን ታላቅነትና ታጋሽነት ይልቁንም ከምታራምደው መንፈሳዊ አስተምህሮ ጋር የሚጋጭ ተግባር በመሆኑ በእንደዚህ አይነቱ ተግባር ላይ መሰማራት ቀርቶ ማሰቡ እንኳን ተገቢነት የለውም። ስለሆነም በተለይም ወጣት የቤተ ክርስቲያን ልጆቻችን ሁሉ ቤተ ክርስቲያን በተቋም ደረጃ የምታከናውነውን በህጋዊ መንገድ መብቷን የማስከበር ተግባር ከመደገፍ፣ ከመጸለይና ከአባቶች የሚተላለፉ መልዕክቶችን ብቻ ተቀብሎ ተግባራዊ ከማድረግ ወጪ በማንኛውም አይነት መልኩ ሁከትና ብጥብጥን ከሚፈጥሩ ተግባራት ፍጹም በመራቅ ህግ አክባሪና ለህግ ተገዢ በሥነ ምግባር የታነጻችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ልጆች መሆናችሁን በተግባር ማሳየት ይኖርባችኋል። በሚቀጠሉት ጥቂት ቀናትና ወራት የሚከበሩ በዓላት ማለትም በታኅሣሥ ፲፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል በዓል፣ ታኅሥሦ ፳፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሚከበረውን የልደት በዓልና ጥር ከጥር ፲- ፲፪ ቀን ፳፻፲፭ዓ.ም የሚከበሩት የከተራ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት አከባበር ዙሪያ ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ በአንድነትና በኅብረት በለሰላምና በስምምነት ራሳችሁን እንደ ሰላም አስከባሪ በማቁጠር፣ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበርና በጋራ በመሠራት ለበዓላቶቻችን በሰላም መከበር ዘብ በመቆም ኦርቶዶክሳዊ የልጅነት ድርሻችን ልትወጡ እንደሚገባ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችሁ መልዕክቷን ታስተላልፋለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ታኅሣሥ ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
Показати все...
እ .. ረ .. ስ .. ቸ .. ዋ .. ለ .. ሁ ..!! አንድ ምስኪን ሴት ወደ አንድ መንፈሳዊ አባት ዘንድ ቀርባ "እግዚአብሔር ሁሌም ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ሁኔታ ግራ የተጋቡት እኚህ አባትም በሁኔታው ተበሳጭተው ጥለዋት ይሄዳሉ። ከዚያን ቀን በኋላ እቺ ሴት እየደጋገመች በመምጣት "እግዚአብሔር ማታ ማታ እየመጣ ያናግረኛል" ትላቸዋለች። በሴትየዋ ጭቅጭቅ የተሰላቹት እኚህ አባትም እንደለመደችው አንድ ቀን መጥታ ስታናግራቸው እንዲህ አሏት "እውነት አንቺን እለት እለት እየመጣ ፈጣሪ የሚያናግርሽ ከሆነ አምንሽ ዘንድ አንድ የቤት ስራ ልስጥሽ" አሏት ትኩር ብለው እየተመለከቷት! ሴትዬይቱም የሚሏትን ሁሉ ለማድረግ ቃል ገባች! እኚህ አባትም ከዚች ሴት ጭቅጭቅ ይገላግለኛል ያሉትን ጥያቄ አቀረቡላት እንዲህ በማለት "እውነት አንቺን እግዚአብሔር የሚያናግርሽ ከሆነ እስቲ ዛሬ ማታ አንድ ጥያቄ ጠይቂልኝ" አሏት። ሴትየዋም በእርጋታ "ምን ልጠይቅልዎ አባቴ?" አለቻቸው። "ለረጅም አመት ልተወው ያልቻልኩት የዛሬ ወር ገደማ ግን ንስሐ ገብቼ የተውኩት አንድ ኃጢአት እሰራ ነበር። ያ በፊት እሰራው የነበረ አሁን ግን ንሰሐ ገብቼ የተውኩት ኃጢአት ምን እንደነበረ ጠይቀሽ ንገሪኝ። እሱን ከነገረሽ እውነትም ላንቺ እግዚአብሔር  እንደሚናገር አምናለሁ" አሏት። ሴትዬይቱም ወደቤቷ ሄደች። ተመልሳ እንደማትመጣ ግን ገምተው ነበር አባ ነገር ግን በበነጋው ያቺ ሴት መጥታ አባን አስጠራቻቸው። አባም ሴትየዬቱን ሲያዩ በጣም ተገርመው ወደሷ በመሄድ በፌዝ መልክ "እህስ ልጄ እግዚአብሔርን ንስሀ ገብቼ ያቆምኩት ሀጢያት ምን እንደነበር ጠየቅሺው?" አሏት ሳቅ እያሉ "አዎን አባ" አለቻቸው ሴትየዋ አንገቷን እንዳቀረቀረች "እህሳ ምን አለሽ?" አሏት አባ በመጓጓት "እረስቸዋለሁ አለኝ" አለቻቸው፡፡ እኚህ መንፈሳዊ አባት ባልገመቱት የእግዚአብሔር ምላሽ ልባቸው ተነክቶ ስቅስቅ ብለው እያለቀሱ ወደደረታቸው አስጠግተው አቀፏት! እ .. ረ .. ስ .. ቸ .. ዋ .. ለ .. ሁ ..!! የሰው ልጅ ሙሉ ይቅርታ የለውም። ዛሬ ምን ፍሪዳ አርዶ ቢታረቅህ፣ ምን በልቅሶ ታጅበህ እየተንፈራፈርክ ይቅር በለኝ ብትለው "ይቅር ብየሀለሁ" ይልህና የሆነ ቀን ስታስቀይመው ይቅር ያለውን በደልህን እየቆጠረ ሲወቅስህ ይውላል እግዚአብሔር ግን ይቅር ካለህ በቃ ረሳው ፍቅር ነዋ፤ ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔርን በኛ መጠን መትረን ንስሐ በገባንበት ኃጢአት ዘወትር የምናለቅስ? ስንቶቻችን እንሆን እግዚአብሔር እንደኛ ቂመኛ መስሎን በፍቅር ሂፆጱ ያጠበውን ኃጢአታችንን እያስታወስን ዘወትር በፀፀት እሾህ ራሳችንን የምንገርፍ? ይቅርታ ከመለመን እኮ ይቅር ማለት ይከብዳል! ምሬሀለሁ ከማለት ማረኝ እያሉ እግር ስር መደፋት ቤት በቀለለ! በህይወታችን የገፋንና ያቆሰለንን ሰው በደል ከመርሳትኮ ሺህ ጊዜ ፍሪዳ እያረዱ "እንታረቅ" ማለቱ እጅግ ቀላል ነውኮ ...! ለዚያም ነው መሰል ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሎት አስተምረን ባሉት ጊዜ "እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል አንተም ይቅር በለን" ብላችሁ ፀልዩ ያለን፡፡  እግዚአብሔር አምላክ የይቅርታ ዘመን ያድርግልን የይቅርታ ልብ ይስጠን
Показати все...
አልጋህ ላይ ተኝተህ አጉል አትጨነቅ፡፡የመኝታ ሰዓት ካለቀ ተነስ፡፡መነሳትህ ካልቀረህ አነሳስህን የጀግና አድርገው፡፡አትንቀራፈፍ፡፡እግርህ ወለሉን ፈጥኖ  ይርገጥ፡፡ልብህ ለፈጣሪ ምስጋና ይስጥ፡፡ቀኑን ቀደም ብለህ በወኔ ጀምረው፡፡እስክትዘጋጅ አትጠብቅ፡፡"ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም!" አትበል፡፡ተነስና እስቲ አድርገው፡፡ "ከየት መጀመር እንዳለብኝ አላውቅም!" አትበል፡፡እስቲ ጀምረው፡፡ይጠቅመኛል የምትለውን ነገር በጠዋቱ  ጀምረው፡፡ያልጀመርከውን ነገር አትጨርሰውም፡፡ስለዚህ አሁን ጀምረው! በወኔ ጀምረው! በእምነት ጀምረው! ጀምርና መንገዱ  መንገዱን ይመራሃል፡፡አንዱ ደረጃ ወደ ቀጣዩ ያደርስሃል፡፡እምነት ካለህ? ሁሌም መንገድ አለ፡፡ግን በመጀመርያ ጀምረው፡፡ወዳጄ ተነስ! ንቃ! ጀምረው፡፡
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.