1 326
Підписники
+424 години
+187 днів
+9830 день
Архів дописів
🔖ማስታወሻ 🔖
✍ የክፍያ ማስታወቂያ✍
የየካቲት ወር ክፍያ ከየካቲት 1_ 14/06/2017ዓ.ም ድረስ ብቻ ያለቅጣት መክፈል እንደሚችሉ ልናስታዉስዋ እንወዳለን።
ማስታወሻ :-
_ እስካሁን ወቅቱን ጠብቃችሁ ክፍያ ያጠናቀቃችሁትን እያመሰገንን ያልከፈላችሁ ደግሞ በወቅቱ እንድትከፍሉ በድጋሚ እናሳውቃለን ::
እናመሰግናለን።
ውድ ወላጆች፣
የዳሰሳ መጠይቁን ሞልተው ላስገቡት እናመሰግናለን።
ዛሬ የመጨረሻው ቀን መሆኑን ለማሰታወስ እንወዳለን፣ ስለዚህ እባክዎን የዳሰሳ ጥናቱን ለማጠናቀቅ እድሉን ይጠቀሙ፡፡
ኮሚቴው
ለወላጆች
እሁድ 9/6/2017 ዓ.ም የአንደኛ መንፈቅ አመት ማጠቃለያ ውጤት ጠዋት ከ2:30 እስከ 5:30 ድረስ ት/ቤት መጥታችሁ እንድታዩ በትህትና እናሳውቃለን።
Assessment in Teaching-Learning, Ethical Development, and Student Safety for Maria Robato Catholic School Primary Division.
በ መማር-ማስተማር፣ በስነምግባር ክትትል እና በተማሪ ደህንነት ላይ ያተኮረ አጭር ጥናት ለ ማሪያ ሮባቶ የካቶሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
Maria Robatto Catholic Primary School is one of the larger divisions, currently serving over 900 students. The parent committee has been established with a clear scope of responsibilities, one of which is providing advisory services to both the school administration and parents. The purpose of this survey is to identify any gaps in the teaching and learning process, assess the ethical development of students, and evaluate the corrective measures in place to address student misbehaviour while at school. Additionally, it aims to examine the strengths and weaknesses in both teaching practices and ethical development procedures in the current academic year 2024/2025. The findings from this survey will help the committee support the school and parents in addressing these gaps and further strengthening the areas that are working well.
Language: English (preferable) or Amharic (optional). Using English letter for Amharic message will be rejected by the system.
Deadline: Tuesday 12/02/2025
Language used: English (preferred) or Amharic (optional). English alphabet cannot be used for Amharic message.
The questions can be filled out on your phone or computer and must be online
We kindly request parents to complete this survey thoughtfully and accurately.
The committee
06/02/2025
ማሪያ ሮባቶ የካቶሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአሁኑ ወቅት ከ900 በላይ ተማሪዎችን እያገለገለ ያለ አንዱ የት/ቤቱ አካል ነው። እንደሚታወቀው የወላጅ ኮሚቴው የተቋቋመው ግልጽ በሆነ የኃላፊነት እና ተግባር ነው። አንዱ ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫ የምክር አገልግሎት ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር እና ለወላጆች መስጠት ነው። የዚህ ዳሰሳ አላማ በ ያዝነው የት/ት ዘመን በ2017 አ.ም, በመማር ማስተማሩ ሂደት ላይ ያሉ ክፍተቶችን መለየት፣ የተማሪዎችን የስነምግባር እድገት መገምገም እና ተማሪዎችን በትምህርት ቤት ውስጥ እያሉ ሲያጠፉ ወይም ሲሳሳቱ እየተተገበሩ ያሉትን የማሰተካከያ እርምጃዎች በዚሁ መጠየቅ ጠንካራ እና መሰተካከል የሚገባቸውን ጉዳዩች በመለየት በቀጣይ በጠንካራ ጎኖች ላይ የበለጠ መሰራት እና በክፍተቶች ላይ ደግሞ የማሰተካከያ መንገዶቸን ለት/ቤቱ እና ለወላጆች ምክረሃሳብ ማቅረብ እና መደገፍ ነው፡፡
የሚጠቀሙት ቋንቋ፡ እንግሊዘኛ (ይመረጣል) ወይም አማርኛ (እንደ አማራጭ)። የእንግሊዘኛ ፊደል ለአማርኛ መልእክት መጠቀም አይቻልም።
ጥያቄዎቹ የሚሞሉት በሰልክዎ ወይም ኮምፒውተር ሲሆን ኢንተርኔት ኦንላይን መሆን አለበት፡፡
የመጨራሻ ቀን፡ ማክሰኞ 5/06/2017 ዓ.ም
ሰለሆነም ወላጆች ይህን መጠይቅ በጥንቃቄ እና በሃላፊነት እንዲሞሉልን በከፍተኛ አክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ኮሚቴው
29/5/2017
ማስታወሻ
ለወላጆች እና ለተማሪዎቻችን
👉የ1ኛው መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ሙከራ በሰላም ተጠናቋል።
👉 ሰኞ ጥር 26/2017 ጠዋት ለግማሽ ቀን ውጤት የምታዩበት ቀን ይሆናል:: ሁሉም ተማሪዎች ፈተና ውጤት ለመውሰድ ኢንፎርም ለብሰው መምጣት ይኖርባቸዋል ።
👉 የሴሚስተር ዕረፍት ቀናት :- ከጥር 26-30 ቀን 2017 ዓ.ም ይሆናል።
👉ሰኞ የካቲት 03 ቀን 2017 ዓ.ም የ2ኛ ሴሚስተር ት/ት የሚጀምር ይሆናል::
🤹♀መልካም የዕረፍት ሳምንት🤹♂
ማሪያ ሩባቶ ካቶሊክ ትምህርት ቤት
ለተማሪ እና ወላጆች
ተማሪዎች የፈተና ውጤት የሚያዩበት ቀን ሰኞ 26/05/2017 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን።
ለወላጆች
ነገ ሰኞ 5/5/2017 ትምህርት የሚሰጠው እስከ ምሳ ሠአት 6:30 ድረስ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን።
ከማክሰኞ 6/2017 እስከ ሐሙስ 8/207 ድረስ የሚሰጠው የ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ምዴል ፈተና መርሐ ግብር ነው።
እንኳን ደስ አለን ትላንት 24/04/2017 በቦሌ ክፍለ ከተማ ካሉ 11 ትምህርት ቤቶች በተካሄደው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ጥያቄ ና መልስ ውድድር ትምህርት ቤታችን አሸናፊ ሆኗል
እንኳን ደስ አለን ትናት 24/04/2017 በቦሌ ክፍለ ከተማ ካሉ ትምህርት ቤቶች በተካሄደው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ጥያቄ ና መልስ ውድድር ትምህርት ቤታችን አቸናፊ ሆኗል
