Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙
Відкрити в Telegram
● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸
Показати більше213
Підписники
Немає даних24 години
-17 днів
-430 днів
Архів дописів
The Qur'an is the Speech of Allah Regardless of How it is Conveyed | Shaykh Saleh Sindi حفظه الله
Where Is The Grave of the Prophet ﷺ_ by Shaykh 'Alī Nāṣir Faqīhī رحمه الله
Cutting Off the Hand of the Thief by Shaykh 'Alī Nāṣir Faqīhī رحمه الله
«ኒቃብ ለብሳ መጥፎ የምትሠራ አውቃለሁ!» ካሉህ፤ «ሙናፊቅ ሆኖ ከነብዩ ﷺ ጀርባ ሶፈ-ል-አወል (የመጀመሪያው ሶፍ ላይ) የሚሰግድ ሰው አውቃለሁ!» በላቸው። ኒቃብ ስለለበሰች ወይም ፂሙን ስላሳደገ ብቻ ፍፁም እንዲሆኑ መጠበቅ አላዋቂነት ነው።
منقول
〽️ ወዳጅ
ያንተን ተድላ፣ ደስታና ስኬት ማየት የሚፈልጉ ፤ ያንተን ችግር መከራና ወድቀት ማየት የማይፈሉጉ ብዙ ሰዎች አሉ።
....ስለዚህ በህይወት ስትኖር ተጠንቅቀህና መልከም ሁነህ ኑር። ካልሆነ ግን ብዙዎችን ታሳዝናለህና‼️
● ብዙዎች ሊያስከፉን ይችላሉ፣ ሊጎዱን አሊያም ሊበድሉን ይችላሉ። ብዙዎች የሀዘናችን፣ የችግርና የመከራችን ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ።
ብዙዎች ወደኋላ ሊገፈትሩን፣ ከቆምንበት ሽቅብ ቁልቁለት ሊወረውሩንም ይችላሉ!
ብዙዎች « እናተ አትችሉም »፣ « አቅም የላችሁም » ሊሉን ይችላሉ። ሊያሳቅቁን፣ ሊያዋርዱንም ይችላሉ!
...ይህ ሁሉ እኛ ላይ ተከስቶም፣ እኛ በአላህ እምነት ካለን፣ ስህተት ካልሰራን (አላህን ካላመፅን)፣ አምፀንም ከሆነ ተፀፅተን ወደሱ ከተመለስን፤ እነዚህ ችግሮች ለኛ ተራ ነገር ይሆናሉ። ምክንያቱም ብዙ ችግር የሚፈጥሩብን ሰዎች እንዳሉ ሁሉ አላህ ደግሞ እኛን የሚደግፉን፣ ለአላህ ብለው የሚወዱን፣ የሚሳሱልን፣ ከስህተታችን የሚመልሱን ብዙዎችን ይሰጠናልና!
አዎ በኛ ደስታ የሚደሰቱ፣ በኛ ሀዘን የሚያዝኑ። የኛን ስቃይ መከራ መካፈል የሚፈልጉ የልብ ወዳጆችን ይሰጠናል! እነዚህ የልብ ወዳጆች የእኛን ተድላ፣ ደስታና ስኬት ማየት የሚፈልጉ ፤ የእኛን ችግር መከራና ወድቀት ማየት የማይፈሉጉ ናቸው።
ከኛ የሚጠበቀው ይህ ነው፤ እነዚህን ወዳጆች ለይተን ማወቅ።
...እነዚህን ወዳጆች ደግሞ ለይተን የምናውቃቸው ያኔ ነው እኛ ለአላህ ብለን በምላሹ ምንም ነገር ሳንፈልግ ለእኛ ጥሩ የሆኑትንም ሆነ መጥፎ የሆኑትን በንፁህ ልባችን ስንወድና ለነሱ ስንጨነቅ ነው።
አቅማችን በፈቀደው ልክ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ሰዎችን ሳንመርጥ ለአላህ ብለን ስንረዳ ነው! ይሄኔ ወዳጆቻችንን ለይተን እናውቃቸዋለን!
.... አንድም ወዳጅ ባይኖረን እንኳን ለአላህ ብለን የሰራነው መልካም ስራ ምርጥና ከሁሉም የተሻለ ወዳጅ ይሆነናል!
እናም ወዳጅ ብናጣ ራሱ *መልካም ስራችንን* ወዳጃችን እናድርገው። ለዚህ ደግሞ *መልካም የሆነ ስራ* ሊኖረን ይገባል አይደል!?
▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬
⭕️ We have to drift our ignorance!!
[[ባላዋቂነታችን እንዝመትበት!]]
✍️ በረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
════════════════
ለአስታያየት: t.me/ReshadMuzemil
ይ🀄ላ🀄ሉን👇👇 share👇
Telegram: t.me/SharpSwords1
Tiktok: tiktok.com/@sharpswords1
Instagram: Instagram.com/sharp_swords1
Ummalife: ummalife.com/ReshadMuzemil
LinkedIn: linkedin.com/in/reshad-muzemil-139b97320
እርግጥ ነው የነብዩ ውዴታ ‘መሐባ’ እና እሳቸውን ማላቅ በእጅጉ የሚያስፈልገን ነገር ነው። ሆኖም ውዴታቸውን የምንገልፀው መንገዳቸውን በመከተል፣ ሱናቸውን አጥብቀን በመያዝ እና ከአዳዲስ ፈጠራዎች በመራቅ መሆን አለበት። ‘የነብዩ ውዴታ’ በሸሪዓ መሰረት ያለው፤ ብሎም የኢማን መገለጫ መሆኑ አጠያያቂ ባይሆንም፤ ከተለያዩ የቢድዓ ተግባራት ጋር ተጣምሮና በቀን ተገድቦ ከተፈፀመ ግን በቢድዓነት ይፈረጃል።
መውሊድ ቢድዓ ከመሆኑ ባሻገር በየጊዜው እንግዳ ጥፋቶች እየታከሉበት እምነትን ከሚጎዱ ብዙ ተግባራት ጋር ከሁለቱ ኢዶች እኩል ወይም ከነሱ በደመቀ ሁኔታ በይፋ በመከበር ላይ ነው። በተለይም በአንዳንድ ቦታዎች ከተራ ወንጀሎች እስከ ቀብር አምልኮ የሚደርሱ ጥፋቶች ይሰራሉ። በተለይ ደግሞ ዓዋቂ የሚባሉ ሰዎች ሲሳተፉበት የቢድዓ አራማጆችም ተራ ሙግቶችን በጥሩ ገለፃዎች ከሽነው በስፋት ሲያሰራጩ ብዙሀኑን ህዝብ መደናገር ውስጥ ይከታሉና ሐቁን መግለፅ የሁሉም አዋቂዎች ግዴታ መሆኑን እናስታውሳለን።
አላህ እውነተኛ የነብዩ ወዳጆችና ተከታዮች ያድርገን። ሀሰትን ተከትሎ መንገድ ከመሳት ይጠብቀን።
ወል ሐምዱ ሊላሂ ረቢል ዓለሚን!
https://tewhidfirst.blogspot.com/2019/11/blog-post.html?m=1
አልሚቅሪዚይ "አልመዋኢዝ ወል-ኢዕቲባር" በተሰኘው ድርሳናቸው ቅፅ 2 ገፅ 436 ላይ እንዲህ ብለዋል፦ የፋጢሚያ (ዑበይዲዮች) ነገሥታት አመቱን ሙሉ የተለያዩ በአላት ነበሯቸው። ለምሳሌ፤ የአመቱ መግቢያ፣ የመጀመሪያው አመት፣ የዓሹራ ቀን፣ የነብዩ ﷺ መውሊድ ይገኙበታል። በተመሳሳይ መልኩ አቡ ሻማህ–አል-ባዒስ አላ ኢንካሪል-ቢደዕ ወልሀዋዲስ ገፅ 23 ላይ እንዲህ ብለዋል፤ በኛ ጊዜ ከሚፈፀሙ ተመሳሳይ መጤ (ሙህደስ) ተግባራት መካከል፤ በኢርበል ከተማ በየዓመቱ የሚፈፀመው የሰደቃ፣ የበጎ አድራጎትንና ደስታን ለመግለፅ ተውቦና ደምቆ በመዋል (የሚከበረው) የነቢዩ ﷺ የልደት ቀን አንዱ ነው።
ኢብኑ ነሓስ – ተንቢሁል ጋፊሊን ገፅ 331 ላይ እንዲሁም ኢብኑል ሀጅ – አልመድኸል ቅፅ 2 ገፅ 2 ተመሳሳይ መልዕክቶችን አስፍረዋል።
በዚሁ አጋጣሚ መውሊድን ስለጀመሩት ሰዎች ማንነት አንዳንድ ነገሮችን ማንሳት ግድ ይለናል፤ "ዑበይዲዮች" ምንም እንኳ ራሳቸውን ወደ ፋጢማ ቢያስጠጉም፤ ሸሪዓዊ ትዕዛዛት እና ክልከላዎች የራቁ ትርጉሞችን በመስጠት ስርአት አልበኝነትን የሚከተለውን የባጢኒያ አመለካከት በማራመድ፣ የዲነልኢስላም ፋና እንዲጠፋ የቻሉትን ሁሉ በማድረግና ኡለማዎችን በመጨፍጨፍ የታወቁ ነበሩ። እነዚህ ሰዎች የኩፍር ንግግሮችን በመናገራቸዉ፣ አላህንና ነብያቶችን በግልፅ በመሳደባቸዉ፣ ክልክሎችን ሀላል በማድረጋቸዉ ወዘተ... ታላላቅ የኢስላም ሊቃዉንት ከኢስላም ምንም ድርሻ እንደሌላቸዉ ተናግረዋል። ሰላሀዲን አል-አዩቢይ አላህ ይዘንለትና ቁድስን ካስለቀቀ በኋላ ሙስሊሙን ከነዚህ ሰዎች ወረራ ለማላቀቅ ዘምቶባቸው ሙስሊሙን ህብረተሰብ እፎይ አሰኝቷል። ከፊሎቹ ደግሞ መውሊድን የጀመረው በ630 ዓ.ሒ የሞተው ንጉስ መሊክ ሙዞፈር ሲሆን እሱ ደግሞ ፍትሃዊ ንጉስ ነበር ይላሉ። በዘመኑ የነበረው የታሪክ እና የጂዖግራፊ ሊቅ ያቁተል ሀመዊ ሙዘፈርን ሲገልፀው “የሰው ንብረት ይዘርፋል ግን ለድሃዎች ያበላል፣ ስራዎቹ ሁሉ ግራ የሚያጋቡ ናቸው” ይላል። መውሊድን ማንም ቢጀመረው ከብዙ ክፍለ ዘመናት በኋላ በዲን ላይ የተጨመረ ለመሆኑ ምስክር ነው።
ከላይ በተዘረዘሩት መረጃዎች መሰረት መውሊድ የዲን አካል ያልነበረ የዑበይዲዮች ወይም የኢብኑ ሙዞፈር ፈጠራ እንደሆነ ግልፅ ነው።
مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ» متفق عليه
ረሱል ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በዲናችን ውስጥ ከእሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ነው” ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል
2) ዒባዳን በጊዜ መለየት (ተኽሲስ)፦
ጊዜያትን ለተለያዩ ዒባዳዎች መፈፀሚያ አድርጎ የወሰነልን አላህ ነው። በሸሪዓችን ረመዳን ለፆም ዙልሒጃ ለሐጅ እንደተለዩት በጊዜ የተገደቡ ዒባዳዎችን በመወሰን በዚህ ቀን ወይም ወር ይህ ይፈፀማል የሚል ድንጋጌ ማውጣት ለማንም አይፈቀድም።
መውሊድ የሚያከብሩ ወገኖች ግን በሸሪዓችን ያልተደነገገውን የረቢዕን ወር አስራ ሁለተኛ ቀን በተለያዩ የዒባዳ ተግባራት ለማሳለፍ በአል አድርገው መርጠውታል። አቡሁረይራህ ባስተላለፉት ሐዲሥ ረሱልﷺ እንዲህ ብለዋል፤
لَا تَخْتَصُّوا لَيْلَةَ الْجُمُعَةِ بِقِيَامٍ مِنْ بَيْنِ اللَّيَالِي، وَلَا تَخُصُّوا يَوْمَ الْجُمُعَةِ بِصِيَامٍ مِنْ بَيْنِ الْأَيَّامِ، إِلَّا أَنْ يَكُونَ فِي صَوْمٍ يَصُومُهُ أَحَدُكُمْ
“የጁምዓ ሌሊትን ከሌሎች ለሊቶች በመለየት በቂያም አትለዩ። ምን አልባት ከምትፆሙት ፆም ጋር ከገጠመ እንጂ የጁምዓ ቀንን ከሌሎች ቀናት በመለየት አትፁሙ» ሙስሊም ዘግበውታል
በዚህ ሐዲሥ የነቢዩ ንግግር ተኽሲስን ያመለከታል። ከጁምዓ ጋር አያይዘው ስለ ተከለከለ ወይም ስለ ታዘዘ ነገር ሲነግሩን ችግሩ በሸሪዓ ልዩ ያልተደረገን ጊዜ በተወሰኑ ኢባዳዎች መለየት ላይ መሆኑን እንረዳለን። አንድን ጊዜ ከሌሎች ጊዜያት በፆም በሶላት አትለዩት ተብሎ መከልከሉ ለሚሰራው ስራ መበላሸት መንስኤው በሸሪዓ ያልተገደበለትን ጊዜ መገደብ (ተኽሲስ) መሆኑን ያስረግጥልናል።
3) ሙስሊም ካልሆኑ ጋር መመሳሰል (ተሸቡሕ)፦
መውሊድን ማክበር ክርስቲያኖች የእየሱስ ልደት (ገና) ብለው ከሚያከብሩት በአል ጋር በእጅጉ ተመሳሳይነት አለው።
አንዳንድ የቢድዓ ሰዎች ነቢዩን ለማላቅ በማሰብ መውሊድን ሲጀምሩት ክርስቲያኖች እንዴት "የነብያቸውን የውልደት ቀን በማውሳት ይቀድሙናል" ከሚል የፉክክር ስሜት ነው። ይህንኑ እውነታ በማረጋገጥ አሕባሽ በመባል የሚታወቀው ቡድን መስራች የሆነው ዐብዱላህ አልሐበሺ የ ‘ኢዝሀሩል አቂደቲሱኒያህ’ የድምፅ ማብራሪያ ካሴት ቁ.9 የመጀመሪያው ክፍል ላይ መውሊድን ለመጀመሪያ ጊዜ ያከበረው የኢርቢሉ ንጉስ ሙዘፈር እንደሆነ እና አጀማመሩም ክርስቲያኖች የመሲህን ልደት ሲያከብሩ አይቶ "ሙሀመድﷺ ወደዚህ አለም ብቅ በማለታቸው አላህን ላመስግን" በማለት እንደጀመረው ተናግሯል።
ቡኻሪ ከአቢ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዲየላሁ ዐንሁ እንደዘገቡት የአላህ መልዕክተኛﷺ እንዲህ አሉ፤
لَتَتَّبِعُنَّ سَنَنَ مَنْ قَبْلَكُمْ شِبْرًا بِشِبْرٍ، وَذِرَاعًا بِذِرَاعٍ، حَتَّى لَوْ سَلَكُوا جُحْرَ ضَبٍّ لَسَلَكْتُمُوهُ»، قُلْنَا يَا رَسُولَ اللَّهِ: اليَهُودَ، وَالنَّصَارَى قَالَ:«فَمَنْ»
"ከናንተ በስተፊት የነበሩትን (ህዝቦች) ፈለግ ስንዝር በስንዝር እርምጃ በእርምጃ ትከተላላችሁ። የተሳቢ እንስሳ ጉድጓድ እንኳ ቢገቡ ትከተሏቸዋላችሁ" የአላህ መልዕክተኛﷺ ሆይ አይሁዶችንና ነሳራዎችን ነው? ተብለው ሲጠየቁ፤ «ሌላ ማንን ነው!» (እነሱን ነው እንጂ) በማለት መለሱ።
ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት ሌላ ሐዲሥ “ሙሽሪኮችን ተፃረሯቸው” ብለዋል። ይህ ማለት በማንነታችሁ ላይ አትደራደሩ፣ በሀይማኖታዊ ጉዳዮች ሌሎችን ከመምሰል ተጠንቀቁ ነው።
በሌላ በኩል በመውሊድ በዓል ላይ በነቢያችን ﷺ ላይ ድንበር በማለፍ እና የአላህን ስልጣን በመስጠት የሚያወድሱ ግጥሞች ይነበባሉ። እርሳቸው ግን የዚህ አይነቱን ድንበር ማለፍ ከልክለዋል፤
لاَ تُطْرُونِي، كَمَا أَطْرَتْ النَّصَارَى ابْنَ مَرْيَمَ، فَإِنَّمَا أَنَا عَبْدُهُ، فَقُولُوا عَبْدُ اللَّهِ، وَرَسُولُهُ
«ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ እንዳጋነኑት እኔንም አታጋንኑኝ፤ እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ የአላህ ባሪያ እና መልዕክተኛ ብቻ በሉኝ» ሀዲሱን ቡኸሪ ዘግበውታል።
በመሆኑም መውሊድን የሚያከብሩ ሰዎች ሁለት የመመሳሰል (ተሸቡሕ) ጥፋቶችን ፈፅመዋል።
1ኛ:- ከኩፋሮች ጋር በበዓል መመሳሰል
2ኛ:- ድንበር ባለፈ የውዳሴ አካሄድ መመሳሰል
ሲጠቃለል፤
የመውሊድ በዓል የሸሪዓ አካል ስላልሆነ፣ ተቀባይነት የሌለው፣ መሰረታዊ የአምልኮ መርሆዎችን የሚጥስ የቢድዓ ተግባር ነው።
የመውሊድ በዓል በሚዛን ላይ
""""""""""""""""""""""""""
ነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol 2 ቁጥር 1
ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው ፡፡ ሰላት እና ሰላም ለዐለማት እዝነት በተላኩት በነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው እና እነርሱን በመልካም በተከተሉት ሁሉ ላይ እስከ እለተ ቂያማ (ትንሳኤ) ድረስ ይውረድ፡፡
ቁርዓን እና ሐዲስን እንዲሁም ዝርዝር የሸሪዓ ህግጋትን በትክክል መረዳት ለሁሉም ሙስሊም በእጅጉ አስፈላጊ ቢሆንም ቀላል ግን አይደለም።
አላህ ለዚህ ኡማ ታላቅ ውለታ በመዋል ኡለማዎችን ሰጥቶን ያላቸውን ታላቅ ክብር ገልፆልናል፡፡ የሙስሊሞችን እምነት፣ የአምልኮ ‘ዒባዳ’ አተገባበር እና የስነምግባር እሴቶችን ማረም የዑለሞች ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ ከሰሀቦችና እነሱን ከተከተሉ ታቢዒዮች መካከል ታላለቅ ዑለማዎች እና የፊቅህ ጠበብቶች ቁርዓንን በተገቢው መልኩ በመረዳት እና ዕድሜያቸውን ሙሉ በማስተማር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሰሃባዎች ከማንም በበለጠ በዕውቀት የበለፀጉ ከመሆናቸው ባሻገር የመልእክተኛውን ﷺ ንግግር እና ሱና በመተግበር ፋና ወጊዎች እንደነበሩ አያጠያይቅም።
አብደላህ ኢብን መስዑድ አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና በአንድ ወቅት ስለሰሃባዎች እንዲህ ብለው ነበር፤ "ከዚህ ከነቢዩ ዑመት ከማንም በበለጠ፤ ቅን ልቦና፣ የጠለቀ እውቀት፣ የተቃና ፈለግ እና ያማረ ስብዕና ባለቤት ነበሩ። እነሱ ማለት አላህ ለነብዩ ጓደኝነት የመረጣቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ክብራቸውን እወቁላቸው። ፋናቸውንም ተከተሉ። እነሱ ቀጥተኛው መንገድ ላይ ነበሩ።" ኢብኑ ዐብደል በር / ጃሚዑል በያኒል ዒልም በሚባለው ኪታባቸው ቅጽ 2/946-947
ሰሃባዎች በሐቅ ላይ አንድነታቸውን ለመጠበቅ የተለያዩ ሸሪዓዊ አጀንዳዎች ላይ ይመካከሩና ይተራረሙ ነበር፡፡ ያልደረሳቸውን መረጃ ሲያገኙም ወደ ሐቅ ከመመለስ የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም። ለሐቅ ተገዢ ስለነበሩ እርምት ለሰጣቸው አካል ምስጋና እና ክብራቸው ከመጨመሩ ባሻገር በመካከላቸው የነበረው ወዳጅነት አልጎዳም። ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ብለዋል "ሰሃባዎች፣ ታቢዒዮች እና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ዑለማዎች በመካከላቸው አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ የአላህን ትዕዛዝ ይከተሉ ነበር፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትሆኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡» ሱረቱ ኒሳዕ : 59
በተለያዩ የዲን አጀንዳዎች ላይ በምክክር መልክ ይወያያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የዒልምና እና የተግባር ጉዳዮች ላይ የአቋም ልዩነት ሲኖር መዋደድን፣ መተሳሰርን እና ኢስላማዊ ወንድማማችነትን በጠበቀ ሁኔታ ይተራረማሉ።" መጅሙዑል ፈታዋ 24/172
በየዓመቱ የረቢዐል አወል ወር በገባ ቁጥር የነቢያችንን የልደት በዓል መውሊድን የማክበር ጉዳይ ሰዎችን ሲያወዛግብና መነጋገሪያ ሲሆን ይታያል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን በመሰረታዊም ይሁን በቅርንጫፋዊ የዲን ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ቢፈጠሩ ጉዳያቸውን ወደ ቁርዓንና ሐዲስ በመመለስ መፍትሄ እንዲፈልጉ በሚከተለው የቁርዓን አንቀጽ አዟል፡፡
فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا ٤:٥٩
«በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው» ሱረቱ ኒሳዕ : 59
ከዚህ ቁርአናዊ መመሪያ በመነሳት ለአንባቢዎቻችን ነሲሓ ይሆን ዘንድ ትክክለኛውን አቋም እናመላክታለን። አላህ ሀቁን አይተው ከሚከተሉት ሰዎች ያድርገን።
ይህ በዓል በሸሪዓ መሰረት የሌለውና ሰዎች በዲን ውስጥ የጨመሩት አዲስ ነገር ከመሆኑ ባሻገር አላህና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ተግባር በቀን የተገደበ ወደ አላህ መቃረቢያ አምልኮ ማድረግ መሆኑ ዋነኞቹ የመውሊድ ችግሮች ሲሆኑ፤ በተጨማሪም ክርስቲያኖችን በመፎካከር የመጣ መሆኑ ከእነሱ ጋር መመሳሰል ነው። በተጨማሪ በዚህ በዓል ውስጥ በሸሪዓ የተወገዙ በርካታ ተግባራት ይፈፀማሉ። መውሊድ አንድን ስራ ቢድዓ የሚያሰኙ ምክንያቶች ሁሉ እንዳሉበት አያጠራጥርም። ይህም በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ይብራራል፤
1) አዲስ ነገር መፍጠር (ኢሕዳስ)፦
ካለ ሸሪዓዊ ማስረጃ፤ ማንኛውንም ቀን ወይም ወር ልዩ ሀይማኖታዊ ክንውን የሚፈፀምበት እንደሆነ በማሰብ በዋጂብነት ወይም ሱናነት ሰዎችን የምናበረታታበት ከሆነ በዲን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ነውና ሀራም ነው።
አላህ እንዲህ ብሏል:-
أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ
«ከሀይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?» ሱረቱ ሹራ ቁጥር 21
ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት የተረጋገጠ ሰሂህ ሐዲስ ነቢያችን ﷺ ብለዋል፤
مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ
«በዲናችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ይደረግበታል» ብለዋል።
ይህ ማለት በሸሪዓ ያልተደነገገን ነገር ፈጥሮ ቢፈፅም ተቀባይነት አያገኝም ማለት ነው።
እንደሚታወቀው፤ መውሊድን ረሱል ﷺ የተከበሩት ኸሊፋዎች እና ሌሎችም ሰሀባዎች አላከበሩትም። እንደዚሁ በተከበረው ዘመን ውስጥ የኖሩት ሰሀባዎችን በመልካም ሲከተሉ የነበሩ ታቢዒዮች አልሰሩትም። እነሱ ደግሞ ከማንም በላይ የሱና አዋቂዎችና ለነቢያችን የነበራቸው ውዴታም ከማንም በላይ እንደነበር እሙን ነው። የነብዩን ፈለግ በሚገባ በመከተልም የማይታሙ እንደ ነበሩ ለማንም ግልፅ ነው። ለኛ አርአያ መሆናቸውም ተነግሮናል። ምንም ሳንጨምር መንገዳቸውን አጥብቀን እንድንይዝ የአላህ መልዕክተኛ አደራ ብለውናል፤
عَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ
«የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል
መውሊድ በቀደምቶቹ ዘመን እንዳልነበረ እና ኃላ የተፈጠረ (ሙህደስ) ለመሆኑ መውሊድ አክባሪዎች ሁሉ የማይክዱት እውነታ ነው። መውሊድ ማክበርን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት ከአራተኛው ክ/ዘመን በኋላ እራሳቸውን ፋጢሚዮች ብለው ይጠሩ የነበሩት ኡበይዲዩች ግብፅን በ362 ዓመተ ሂጅራ የወራሩ ጊዜ ነበር።
SUPPRESSING ONE'S SOUL AND CONQUERING THE DEVIL
𝐓𝐡𝐞 𝐬𝐨𝐮𝐥 𝐚𝐧𝐝 𝐭𝐡𝐞 𝐝𝐞𝐯𝐢𝐥 𝐚𝐫𝐞 𝐭𝐡𝐞 𝐬𝐨𝐮𝐫𝐜𝐞 𝐨𝐟 𝐞𝐯𝐞𝐫𝐲 𝐬𝐢𝐧 𝐚𝐧𝐝 𝐭𝐡𝐞 𝐨𝐫𝐢𝐠𝐢𝐧 𝐨𝐟 𝐚𝐥𝐥 𝐞𝐯𝐢𝐥. If he distanced himself from sinfulness and wrongdoing to which his soul that calls to evil and the accursed devil incites him, then he would have successfully suppressed his own soul and subdued the devil. In doing so he has tasted the sweetness of true strength through the obedience of Allāh, pursuing His pleasure and avoiding whatever He is displeased with. 𝐈𝐭 𝐡𝐚𝐬 𝐛𝐞𝐞𝐧 𝐧𝐚𝐫𝐫𝐚𝐭𝐞𝐝 𝐢𝐧 𝐭𝐡𝐞 𝐬𝐮𝐩𝐩𝐥𝐢𝐜𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐰𝐡𝐢𝐜𝐡 𝐞𝐯𝐞𝐫𝐲 𝐌𝐮𝐬𝐥𝐢𝐦 𝐢𝐬 𝐞𝐧𝐜𝐨𝐮𝐫𝐚𝐠𝐞𝐝 𝐭𝐨 𝐬𝐚𝐲 𝐢𝐧 𝐭𝐡𝐞 𝐦𝐨𝐫𝐧𝐢𝐧𝐠, 𝐢𝐧 𝐭𝐡𝐞 𝐞𝐯𝐞𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐚𝐧𝐝 𝐰𝐡𝐞𝐧𝐞𝐯𝐞𝐫 𝐡𝐞 𝐠𝐨𝐞𝐬 𝐭𝐨 𝐛𝐞𝐝,
اللَّهُمَّ فَاطِرَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ عَالِمَ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ رَبَّ كُلِّ شَيْءٍ وَمَلِيكَهُ أَشْهَدُ أَنْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ أَنْتَ أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ نَفْسِي وَشَرِّ الشَّيْطَانِ وَشِرْكِهِ وَأَنْ أَقْتَرِفَ عَلَى نَفْسِي سُوءًا أَوْ أَجُرَّهُ إِلَى مُسْلِمٍ
❝𝐎 𝐀𝐥𝐥𝐚𝐡, 𝐭𝐡𝐞 𝐂𝐫𝐞𝐚𝐭𝐨𝐫 𝐨𝐟 𝐭𝐡𝐞 𝐡𝐞𝐚𝐯𝐞𝐧𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐞𝐚𝐫𝐭𝐡, 𝐭𝐡𝐞 𝐊𝐧𝐨𝐰𝐞𝐫 𝐨𝐟 𝐚𝐥𝐥 𝐭𝐡𝐢𝐧𝐠𝐬 𝐡𝐢𝐝𝐝𝐞𝐧 𝐚𝐧𝐝 𝐚𝐩𝐩𝐚𝐫𝐞𝐧𝐭, 𝐭𝐡𝐞 𝐋𝐨𝐫𝐝 𝐚𝐧𝐝 𝐒𝐨𝐯𝐞𝐫𝐞𝐢𝐠𝐧 𝐨𝐯𝐞𝐫 𝐚𝐥𝐥 𝐭𝐡𝐢𝐧𝐠𝐬; 𝐈 𝐛𝐞𝐚𝐫 𝐰𝐢𝐭𝐧𝐞𝐬𝐬 𝐭𝐡𝐚𝐭 𝐧𝐨𝐧𝐞 𝐡𝐚𝐬 𝐭𝐡𝐞 𝐫𝐢𝐠𝐡𝐭 𝐭𝐨 𝐛𝐞 𝐰𝐨𝐫𝐬𝐡𝐢𝐩𝐩𝐞𝐝 𝐞𝐱𝐜𝐞𝐩𝐭 𝐘𝐨𝐮. 𝐈 𝐬𝐞𝐞𝐤 𝐫𝐞𝐟𝐮𝐠𝐞 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐘𝐨𝐮 𝐟𝐫𝐨𝐦 𝐭𝐡𝐞 𝐞𝐯𝐢𝐥 𝐨𝐟 𝐦𝐲 𝐨𝐰𝐧 𝐬𝐨𝐮𝐥, 𝐟𝐫𝐨𝐦 𝐭𝐡𝐞 𝐞𝐯𝐢𝐥 𝐨𝐟 𝐭𝐡𝐞 𝐝𝐞𝐯𝐢𝐥 𝐚𝐧𝐝 𝐡𝐢𝐬 𝐬𝐡𝐢𝐫𝐤 𝐚𝐧𝐝 𝐟𝐫𝐨𝐦 𝐜𝐨𝐦𝐦𝐢𝐭𝐭𝐢𝐧𝐠 𝐞𝐯𝐢𝐥 𝐚𝐠𝐚𝐢𝐧𝐬𝐭 𝐦𝐲 𝐨𝐰𝐧 𝐬𝐨𝐮𝐥 𝐨𝐫 𝐛𝐫𝐢𝐧𝐠𝐢𝐧𝐠 𝐢𝐭 𝐭𝐨 𝐚𝐧𝐨𝐭𝐡𝐞𝐫 𝐌𝐮𝐬𝐥𝐢𝐦.❞*
This is an example of seeking refuge [with Allāh] from the two sources of evil and their consequences. Surely the two sources of evil are the soul and the devil. Therefore, it is required of you in this blessed supplication to seek refuge with Allah from the two sources of evil, which are the soul that incites to evil and the devil, three times: 𝐰𝐡𝐞𝐧 𝐲𝐨𝐮 𝐚𝐰𝐚𝐤𝐞, 𝐰𝐡𝐞𝐧 𝐲𝐨𝐮 𝐞𝐧𝐭𝐞𝐫 𝐭𝐡𝐞 𝐞𝐯𝐞𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐚𝐧𝐝 𝐰𝐡𝐞𝐧 𝐲𝐨𝐮 𝐫𝐞𝐭𝐢𝐫𝐞 𝐭𝐨 𝐛𝐞𝐝, 𝐟𝐫𝐨𝐦 𝐭𝐡𝐞 𝐭𝐰𝐨 𝐬𝐨𝐮𝐫𝐜𝐞𝐬 𝐨𝐟 𝐞𝐯𝐢𝐥.
It is also required of you to seek refuge with Allāh from the consequences of these things which is the perpetration of evil against yourself or to bring evil to someone else. If you are mindful of this and abandon disobedience, suppressing the soul that incites to evil, subduing your enemy the devil and seeking honor through obedience to Allāh (سُبْحَانَهُ وَتَعَالَى), then this is a treasure that is greater than any other.
*[PN] Sahih: Collected by al - Tirmidhī and others. Declared Sahīh by Shaykh Albanī Sahīh Sunan al-Tirmidhī (no.3529).
Book: HOW TO ESCAPE SINS
The Ways and Means to Refrain From The Disobedience of Allāh
Dr. Abdur-Razzāq Ibn ‘Abdul-Muhsin Al-Badr | Translated by Abul-Layth Qāsim Ibn Aggrey Mutiva | Hikmah Publications | P. 20, 21
ستسألون عن هذه الأجهزة يوم القيامة!
🎙️الشيخ عبدالرزاق البدر حفظه الله
You will be asked about these devices on the Day of Judgement!
🎙️Shaykh Abdurrazzaq al-Badr حفظه الله
Salvation vs Fire |Surah Ghafir سورة غافر| Yasser Al Dosari ياسرالدوسري #القران_الكريم #تلاوة_خاشعة
