uk
Feedback
ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/

ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/

Відкрити в Telegram

በግንባታው ዘርፍ ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሳምንታዊ የባለሙያዎች የሬድዮ ፕሮግራም የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር ከአሀዱ ሬድዮ 94.3 ትብብር ዘወትር ሰኞ ምሽት ከ2፡00-3፡30 ሰዓት የሚተላለፍ ሳምንታዊ ፕሮግራም ነው።

Показати більше
4 255
Підписники
+124 години
+87 днів
+1130 день
Архів дописів
የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው። ዘነበ ንጉሴ የተባ
+2
የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው። ዘነበ ንጉሴ የተባለው ግለሠብ በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ የህንፃ መጠቀሚያ ባለሙያ ሲሆን፣ የግል ተበዳይ የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት 100 ሺህ ብር ተጠይቀው በድርድር 50 ሺህ ብር ይዘው እንዲመጡ ተስማምተዋል። የግል ተበዳይ የደረሰባቸውን በደል ለክፍለ ከተማው ፖሊስ የወንጀል መከላከል መምሪያ በሰጡት ጥቆማ ተጠርጣሪው በክትትል አባሎች ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል። ከጉዳዩ ጋር ተሳትፎ የነበረው በክፍለ ከተማው የግንባታ ፈቃድ የመጠቀሚያ ፈቃድ ባለሙያ የሆነው አድምቀው ውቤ የተባለው ግለሰብ የግል ተበዳይን ጉቦ ካልከፈልክ አገልግሎት እንደማይሰጠው በመንገርና ለአንድ ወር በማጉላላት 50 ሺህ ብሩን እንዲሰጥ በማድረግ የማግባባት ስራ ሲስራ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል። ህብረተሰቡ መብቱን በገንዘብ መግዛት እንደሌለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መሰል የወንጀል ድርጊት ሲፈጸም ጉዳዩን በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (citizen engagement application) በመጠቀም መረጃ መስጠት እንደቻልም የከተማው ፖሊስ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡ (የ.ፌ.ሥ.ሙ.ኮ)

https://www.facebook.com/share/v/18b3qfqhKT/ 👉 ኢትዮ ኮን ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም

👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ▪️▪️ልዩ ፕሮግራም▪️ 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ
👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ▪️▪️ልዩ ፕሮግራም▪️ 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም መሐንዲስ የነበሩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬን የምናስታውስበት ልዩ የሬድዮ ፕሮግራም ይዘን እንቀርባለን። 🔲 በፕሮግራሙ ውስጥ፦ ✔️ የህይወት እና የሙያ ጉዟቸው ✔️ ከቤተሰቦቻቸው የተሰሙ ትዝታዎች ✔️ ከስራ ባልደረቦቻቸው የተገኙ ምስክርነቶች ✔️ ለሀገር ያበረከቱት አሻራ 🗓 ቀን፡ [ ሰኔ 1 ቀን 2018 ] ⏰ ሰዓት፡ [ሰዓት 2፡20—3፡30] አይለፍዎ! ▶️ በወቅታዊነት የምናነሳው ነጥብ ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ መልክ ሌሎች የስራ መስኮች ላይ ሊሰማራ መሆኑን አስታውቋል። የራሱን ባለሙያዎች ጨምሮ የበላይ አካላትን እና የደንበኞቹን ሙያዊ ብቃትና የሥራ አፈጻጸም አቅም ለማሳየት የሚስያችል የሥልጠና ማዕከል በማደራጀት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። ስለማሰልጠኛ ተቋሙ ግንባታ ሂደት ሌሎቸም ጉዳዮች ጋር ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ጋር ቆይታ አድርገናል። 📞☎️📩 የምታነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ 👉 📞0974466655 ላይ አድርሱን፡፡ ⏰⏱️📻ከ2፡00 — 3፡30 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 ላይ በቀጥታ ስርጭት ፕሮግራሞቻችንን ትከታተሉ ዘንድ ከወዲሁ በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡                      መልካም ምሽት! https://t.me/ethioconradio

👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👩‍🔧👩‍💼👩‍🦰ልዩ ፕሮግራም 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘ
👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👩‍🔧👩‍💼👩‍🦰ልዩ ፕሮግራም 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም መሐንዲስ የነበሩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬን የምናስታውስበት ልዩ የሬድዮ ፕሮግራም ይዘን እንቀርባለን። በፕሮግራሙ ውስጥ፦ ✔️ የህይወት እና የሙያ ጉዟቸው ✔️ ከቤተሰቦቻቸው የተሰሙ ትዝታዎች ✔️ ከስራ ባልደረቦቻቸው የተገኙ ምስክርነቶች ✔️ ለሀገር ያበረከቱት አሻራ 🗓 ቀን፡ [ ሰኔ 1 ቀን 2018 ] ⏰ ሰዓት፡ [ሰዓት 2፡20—3፡30] አይለፍዎ! ▪️ በወቅታዊነት የምናነሳው ነጥብ ይኖረናል፡፡ ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ መልክ ሌሎች የስራ መስኮች ላይ ሊሰማራ መሆኑን አስታውቋል። የራሱን ባለሙያዎች ጨምሮ የበላይ አካላትን እና የደንበኞቹን ሙያዊ ብቃትና የሥራ አፈጻጸም አቅም ለማሳየት የሚስያችል የሥልጠና ማዕከል በማደራጀት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። ስለማሰልጠኛ ተቋሙ ግንባታ ሂደት ሌሎቸም ጉዳዮች ጋር ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ጋር ቆይታ አድርገናል። 📞☎️📩 የምታነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ 👉 📞0974466655 ላይ አድርሱን፡፡ ⏰⏱️📻ከ2፡00 — 3፡30 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 ላይ በቀጥታ ስርጭት ፕሮግራሞቻችንን ትከታተሉ ዘንድ ከወዲሁ በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡                      መልካም ምሽት! https://t.me/ethioconradio

👉 የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዋና ዋና ስኬቶች
👉 የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዋና ዋና ስኬቶች

🔲 AFRICA HALL GUIDED TOUR
🔲 AFRICA HALL GUIDED TOUR

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን  ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

🏗 የግንባታ ወጪን የሚቀንሱ 5 መንገዶች 1. የተሟላ ፕላን ከስራ መጀመርዎ በፊት ያዘጋጁ። 2. ቁሳቁስን በአግባቡ ያከማቹ፡፡ 3.የሰራተኞችን ስራ በየቀኑ ይቆጣጠሩ። 4. የቁሳቁስ ብክነትን ይቀንሱ፡፡ 5. የጥራት ቁጥጥርን ከመጀመሪያው ይተግብሩ። 👉 ከመጀመሪያው የተሰራ የጥራት ስራ ከኋላ ከሚደረግ እርማት ያነሰ ወጪ ይጠይቃል። ለተጨማሪ የግንባታ እውቀቶች ቻናላችንን ይከታተሉ! https://t.me/ethioconradio

🔵 በውል አስተዳደር (Contract Management) የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት 🔷  ውል ከተዋዋሉ ቀን ጀምሮ የተሸናፊና አሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) እንዲመለስ ይደረጋል፣ የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) ጊዜውን እየጠበቀ የማራዘሚየ ደብዳቤ እያዘጋጀ እንዲራዘም ይደረጋል፡፡ 🔷  የውል ማስከበሪያ (Performance Bond) ይቀበላል፣ ይይዛል፣ያስተዳድራል፣ 🔷  በአገር ውስጥ ጨረታ ጊዜ ዕቃውን ከተረከበ በኋላ ከ5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን የክፍያ ሁኔታ ያመቻቻል ወይም እንዲመቻች ያደርጋል፡፡ 🔷  በአለም አቀፍ ጨረታ የሚፈፀም ግዥ (ICB) ከሆነ ሌተር ኦፍ ክሬዲት (l/C) ይከፍታል፣ወይም በተጠቃሚ መ/ቤቶች እንዲከፈቱ አስፈላጊውን ነገር ሁሉ ያመቻቻል፣ ሂደቱንና ዕቃውን ከተጫነበት አንስቶ እስከ ርክክብ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መረጃዎችን ለተጠቃሚው መ/ቤት ያቀብላል፡፡ 🔷 የትራንዚትና ክሊሪንግ ሥራዎችን ተከታትሎ ያስፈፅማል፣ ሰነዶችንም በአግባቡ ይይዛል፣ ያደራጃል፣ 🔷  ለመ/ቤቶች የተገዙትን ዕቃ በሚፈለገው ስፔሲፊኬሽን መሰረት መቅረቡን በባለሙያ አስፈላጊውን ምርመራ እንዲደረግ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፤ ከምርመራ በኋላ አስፈላጊውን የዕቃ ርክክብ እንዲፈፀም ያደርጋል፤ 🔷 በአገልግሎቱ የተገዙት ዕቃዎች (አገልግሎቶች) በውሉ መሰረት ለተጠቃሚዎች መድረሳቸውን ይከታተላል፣ ያረጋግጣል። https://t.me/ethioconradio

🔲 የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ዓላማዎች ምንድን ናቸው? ▶️ የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ዋና ዓላማ የመንግስት ወጪ ዘላቂ ልማትን እንዲደግፍ ማድረግ እና የመንግስት ገንዘብ ተመጣጣኝ ዋጋ (Value for Money) እንዲያገኝ ማስቻል ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌሎች ዝርዝር ዓላማዎች ይኖሩታል፡፡ እንዚህም የመንግስትን ሀብት በብቃት መጠቀምን ማበረታታት፣ አካባቢን መጠበቅ፣ ማህበራዊ ፍትሃዊነትን እና የሰብአዊ መብቶችን መደገፍ፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማበረታታት፣ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን ማጠናከር፣ ፈጠራን እና አረንጓዴ ቴክኖሎጂዎችን ማበረታታት፣ ሀገር በቀል ተቋማትን እና አነስተኛ ድርጅቶችን መደገፍ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ ▶️ ስለሆነም ይህ የግዥ ስርዓት የመንግስት ተቋማት የሚጠቀሙት ዕቃዎችን እና አገልግሎቶችን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ሰፋ ያሉ የብሔራዊ ልማት ግቦችንም ለማሳካት ጭምር እንደሆነ የሚያስገነዝብ ነው። በዋናነት የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ነው። ዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ሦስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ነው ሲባል ምን ማለት ነው? ▶️ ዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ከአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚታይ አይደለም፡፡ ማለትም ግዥውን ለመፈጸም ዝቅተኛ ዋጋን እንደ መስፈረት መውሰድ በቂ አይደለም፤ የእቃውን ጥራትም እንደ ግዥ መስፈርት ወስዶ ግዥውን መፈጸም በቂ አይደለም፡፡ ይልቁንም ግዥውን ለመፈጸም ከላይ ከገለጸናቸው መስፈርቶች በተጨማሪ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሚታ፣ በአካባቢ ላይ ተጽዕኖ የማያሳድር መሆኑ፣ ማህበራዊ አገልግሎት ላይ ያለው አስተዋጽዖ፣ አረንጓዴ ልማትን መድገፍ የሚያስችል መሆኑና ሌሎች መሰል መስፈርቶች ከግምት ውስጥ የሚገቡ ናቸው፡፡ በዝርዝር ለመመልከት ያህል፦ ▶️ የኢኮኖሚ ዘላቂነት (Economic sustainability)፦ የኢኮኖሚ ዘላቂነት በምርቶች እና በአገልግሎቶች የህይወት ዑደት ውስጥ ለተከፈለው ገንዘብ ተመጣጣኝ ዋጋ (Value for Money) ማረጋገጥ ላይ ያተኩራል። ይህም የወጪ ውጤታማነትን (Cost efficiency)፣ የጥራት ማሻሻያን (Quality improvement)፣ ዘላቂነትን (Durability)፣ የጥገና ወጪ መቀነስን  (Reduction of maintenance costs) እና የረጅም ጊዜ የፋይናንስ ቁጠባን (Long-term financial savings) መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ሂደት ውስጥ የግዥ ባለሙያዎች የመግዣ ዋጋ ላይ ብቻ  አያተኩሩም ይልቁንም ከመግዣ ዋጋው በተጨማሪ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችን፣ የጥገና ወጪዎችን እና የማስወገጃ ወጪዎችንም ግንዛቤው ውስጥ ያስገባሉ። ▶️ የአካባቢ ዘላቂነት (Environmental sustainability)፡- የአካባቢ ዘላቂነት የግዥ ሂደቶች ግዥው በአካባቢ ላይ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ መቀነስ ላይ ያተኩራል። ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው የሚገዙ ግዥዎች በአካባቢ ላይ ብክለትን የማያስከትሉ መሆናቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህን ስንል የሚገዙ ምርቶች ብክለትን የሚቀንሱ፣ ኃይልን የሚቆጥቡ፣ እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ ቁሳቁሶችን የሚጠቀሙ፣ የግሪን ሀውስ ጋዞችን የሚቀንሱ እና ታዳሽ ኃይልን የሚያበረታቱ መሆናቸው ግንዛቤ ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም የአካባቢ ተስማሚ ግዥ (Environmental Sustainability Procurement) የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ እና የተፈጥሮ ሀብቶችን ለመጠበቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ▶️ ማህበራዊ ዘላቂነት (Social Sustainability):-  ማህበራዊ ዘላቂነት የማህበራዊ ደህንነትን ለማሻሻል እና ሥነ-ምግባራዊ የንግድ አሠራሮች ማረጋገጥ ላይ የሚያተኩር ሲሆን ፍትሃዊ የሥራ ልምዶች፣ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ፣ የሥራ ቦታ ደህንነት፣ የፆታ እኩልነት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ለተጋላጭ ቡድኖች ድጋፍ መስጠትን የሚያበረታታ ነው፡፡ (መግባ) https://t.me/ethioconradio

* ዜና ዕረፍት * በደርግ ዘመነ መንግሥት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመምራት የሚታወቁት አቶ ካሳ ገብሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው። ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።  ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል። በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ  በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው  ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል። የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል። የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ። በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ። አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል። ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል። አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።   በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል። 👉 ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን። https://t.me/ethioconradio

👉 ኢ/ር ካሳ ገብሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
👉 ኢ/ር ካሳ ገብሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

👉 የሚኒስትሮች ምክር ቤት የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ ✨​ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አ
+2
👉 የሚኒስትሮች ምክር ቤት የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ ✨​ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላልፏል። ✨​ ማሻሻያው ያስፈለገው ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ የመጡትን የኢኮኖሚ ለውጦች ተከትሎ፣ የታክስ ሥርዓቱን ከዘመናዊ ዓለም አቀፍ ልምዶች ጋር ለማጣጣም መሆኑ ተገልጿል። ✨ በተጨማሪም የታክስ አለመግባባቶችን በፍትሐዊነት፣ በሰላማዊ መንገድና በቅልጥፍና ለመፍታት፣ ተጠያቂነትና ግልጸኝነትን ለማስፈን እንዲሁም ሕጎችን በተጠናከረ መልኩ ለማስፈጸም ያለመ ነው። ​ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ፣ አስፈላጊ ግብአቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ ወስኗል። ✨ በዕለቱ ምክር ቤቱ በሌሎች በርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይም ውሳኔዎችን አሳልፏል።

👉 ወደቻይና የሚደረጉ ኤክስፖርቶችን በተመለከተ ፈቃድ መስጠት ከ1999 ጀምሮ የኢትየጵያ ንግድ ባንክ ስልጣን ሆኖ ቆይቷል። 🔘 ነገር ግን ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ግንቦት 18 2018 ጀምሮ ሁሉም ባንኮ
👉 ወደቻይና የሚደረጉ ኤክስፖርቶችን በተመለከተ ፈቃድ መስጠት ከ1999 ጀምሮ የኢትየጵያ ንግድ ባንክ ስልጣን ሆኖ ቆይቷል። 🔘 ነገር ግን ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ግንቦት 18 2018 ጀምሮ ሁሉም ባንኮች ወደቻይና የሚላኩ ኤክስፖርቶች ፈቃድ በሁሉሜም ባንኮች እንዲከናወን መፈቀዱን አሳውቋል። https://t.me/ethioconradio

ነገ መስቀል አደባባይ በሚደረገው ፕሮግራምን ምክንያት የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመሆኑም ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፦ 
ነገ መስቀል አደባባይ በሚደረገው ፕሮግራምን ምክንያት የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመሆኑም ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፦   ከመገናኛ በባንቢስ ሱፐር ማርኬት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ  ኡራኤል አደባባይ   ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ጥላሁን አደባባይ ወይም መሾለኪያ  ለከባድ ተሽከርካረዎች አጎና ሲኒማ   ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሃር መብራት   ከንግድ ባንክ ወደ አዲስ አበባ ስቴዲዩም ቴሌ መ/ቤት   ከፒያሳ በአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሀራምቤ ሆቴል   ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግስት   ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ለገሃር መብራት   በቦሌ መንገድ ወደ  መስቀል አደባባይ ኦሎፒምያ ወይም ደንበል  አደባባይ ጋር ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። መረጃ ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ በተጠቀሱ አካባቢ ለአጭርም ሆነ ለእረጅም ጊዜ ተሽከርከካሪ አቆሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ዋና መምሪያው ገልጾ መሰል ፕሮግሞች በሚዘጋጁበት ወቅት ሆነ በሌሎች የፀጥታ ስራዎች ህዝቡ እያደረገ ላለው ቀና ትብብር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና  ጠቅላይ መምሪያ  ምስጋናውን እያቀረበ አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እዳያጋጥማቸው አመራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

ነገ መስቀል አደባባይ በሚደረገው ፕሮግራምን ምክንያት የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመሆኑም ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፦   ከመገናኛ በባንቢስ ሱፐር ማርኬት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ  ኡራኤል አደባባይ   ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ጥላሁን አደባባይ ወይም መሾለኪያ  ለከባድ ተሽከርካረዎች አጎና ሲኒማ   ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሃር መብራት   ከንግድ ባንክ ወደ አዲስ አበባ ስቴዲዩም ቴሌ መ/ቤት   ከፒያሳ በአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሀራምቤ ሆቴል   ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግስት   ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ለገሃር መብራት   በቦሌ መንገድ ወደ  መስቀል አደባባይ ኦሎፒምያ ወይም ደንበል  አደባባ ጋር ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። መረጃ ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ በተጠቀሱ አካባቢ ለአጭርም ሆነ ለእረጅም ጊዜ ተሽከርከካሪ አቆሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ዋና መምሪያው ገልጾ መሰል ፕሮግሞች በሚዘጋጁበት ወቅት ሆነ በሌሎች የፀጥታ ስራዎች ህዝቡ እያደረገ ላለው ቀና ትብብር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና  ጠቅላይ መምሪያ  ምስጋናውን እያቀረበ አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እዳያጋጥማቸው አመራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡