uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 069
Підписники
+224 години
Немає даних7 днів
+230 день
Архів дописів
#ዜና| በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለምረጥ የታለመ የክህሎት ውድድር ማከናወን ጀመረ፡፡ በዘንድሮ በጀት ዓመት ለ4
+8
#ዜና| በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለምረጥ የታለመ የክህሎት ውድድር ማከናወን ጀመረ፡፡ በዘንድሮ በጀት ዓመት ለ4ኛ ጊዜ ‹‹ ብሩህ አዕምሮዎች ፣በክህሎት የበቁ እጆች!››በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ ያለመ ከኮሌጅ ጀምሮ እስከ ክልል ድረስ የሚሄድ የተለያዩ የምዘና ስራዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተሰሩ ሲሆን በዚህም በICT ፣በTextile and Garment በElectrical Electronics፣በ Automotive ፣በManufacturing ፣በHotel Truism ትምህርት ክፍሎች ለበርካታ ሰልጣኝ ተማሪዎች ምዘናዎች ተደርገዋል፡፡ ይህ የክህሎት ውድድር ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ወደ ተግባር በመለወጥ ሂደት የበቁ ዜጎችን ለመፍጠር የሚያስችልና የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደ መሬት አውርደው ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ውድድር እንደሆነ በውድድሩ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ በትናንትናው እለት የተጀመረው ይህ ውድድር በኮሌጅ ደረጃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ በክላስተር ደረጃ የተለያዩ ውድድሮች የሚደረጉ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፈጠራቸውን ገለጹ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት 8 ወራት ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፍጠር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፈጠራቸውን ገለጹ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት 8 ወራት ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፍጠር መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ባለፉት 8 ወራት በተመዘገበ መረጃ በሀገር ውስጥ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። ከ300 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸው፤ ከ45 ሺህ በላይ ዜጎች በሪሞት ጆብ ወይም በዲጂታል መንገድ ስራ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ የግብርናው ዘርፍ 40 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ 20 በመቶ፣ ሰርቪስ 38 በመቶ የስራ ዕድሎች የተገኙባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ከሴክተሮች በተጨማሪ በኮሪደር ስራዎች እና ልዩ ልዩ ኢኒሼቲቮች በርካታ የስራ ዕድሎችን ፈጥረናል ብለዋል፡፡ ካለው አምራች ሀይል አንፃር አሁን ያለው የስራ ዕድል በቂ አለመሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ያለውን የስራ ፍላጎት በሚመጥን መልኩ ዜጎችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ አመላክተዋል፡፡ FBC

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው? ***** የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል . በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ታጥቀው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው? . የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ፤ በትግራይ ዳግም ጦርነት እንዳይነሳስ ምን እየተሠራ ነው? . የፍትሕ ተደራሽነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት መንግሥት በቀጣይ ምን ለመስራት አስቧል? . በሰላም እጦት ሳቢያ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሕዝብ ላይ የሚደርሰውን እንግልት ከመሰረቱ ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው? . በአምራች ዘርፉ ያለውን የጥሬ ዕቃ እና የሌሎች የአቅርቦት ችግሮ ለመፍታት መንግሥት ምን እየሠራ ይገኛል? . የ10 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ ማሳካት መቻላችንን የሚያመላክቱ መስፈሪያዎች ምንድን ናቸው? ፤ ሴክተሮችስ ከዚህ ዕቅድ ጋር ምን ያህል ተናበው እየሰሩ ነው? . መንግሥት በድጎማ የሚያቀርበው ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይሸጥ ምን አይነት ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው? . በአሁኑ ሰዓት የመንግሥት ሠራተኛን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በኑሮ ውድነት እየተቸገሩ ባሉበት ሁኔታ እንዴት የዋጋ ግሽበት ቀንሷል ሊባል ይችላል? . የቁጥጥር ተቋማት ነጻ ሆነው በትክክል ኃላፊታቸውን እንዲወጡ ምን አይነት ሥራዎች እየተሰሩ ነው? . የባሕር በር ለማግኘት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ስምምነቶች በምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ? . ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ያላቸውን የቤት ፍላጎት እና አቅርቦት ለማጣጣም ምን እየተሰራ ነው? . የኮሪደር ልማትን ተከትሎ የሚነሱ የአፈጻጸም ችግሮችን እና ቅሬታዎችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ ርምጃዎች ምን ይመስላሉ? . የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ መዘግየት እንዳይፈጠር ምን እየተሰራ ነው? . የመሬት አቀማመጣቸው ወጣ ገባ በሆኑ እና ለሜካናይዜሽን በማይመቹ አካባቢዎች ምርታማነት ለማሳደግ ምን እየተሠራ ነው? . እስካሁን የተፈጠረው የሥራ ዕድል ካለው ፍላጎት ጋር ምን ያክል የተመጣጠነ ነው?

photo content
+2

የትኩረት አቅጣጫ በሆኑ የሙያ ዘርፎች ላይ የሴት ሰልጣኞችን ተሳፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ሴቶችን ተፈላጊ በሆኑ የሙያ ዘርፎች ለማሳተፍ በሚደረግ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ ከዲፓርትመቶች ከተወጣጡ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የሴቶችና ህፃናት ክፍል ተጠሪ ወ/ሮ ራሄል እሸቱ ሲሆኑ በንግግራቸውም ሴት ሰልጣኞች በአብዛኛው Soft Skill የሚባሉ ሙያዎች ላይ ጥገኛ እንደሚሆኑ አስታውሰው በዛው መጠንም ተምረው ሲጨርሱ ስራ የማግኘት እድላቸው በጣም አናሳ እንደሆነ ይስተዋላል ያሉ ሲሆን ሴቶች ኢንዱስትሪው በሚፈልገውና ብዙ እድሎች ያሉባቸው ዘርፎች ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይገባልም ብለዋል:: በፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መድረኩ ላይ ለሰልጣኞች ግንዛቤ የሰጡት የEASE ፕሮጀክት የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን አስተባባሪ ኢንጂነር ህይወት እሸቱ ሲሆኑ በመልእክታቸውም ሴቶች የኢንጂነሪንግ ዘርፎች ላይ ደፈር ብለው ተሳታፊ ቢሆኑ ተጠቃሚ የሚያደርጏቸው ብዙ እድሎች እንዳሉ አስታውሰው ይህ በኮሌጁ የሚዘጋጀው ጥናትም የችግሩን መንስኤ ከስር መሰረቱ በመለይትና ለሴቶች እስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ወቅቱ በሚጠይቀው የሙያ ዘርፍ ላይ በሚፈለገው ደረጃ እንዲሳተፉ ለማድረግ እንደሆነም ገልፀዋል:: በመድረኩ ሴት ሰልጣኞቹን በቡድን ተክፍለው የሚስተዋሉ ክፍተቶች ላይ እንዲወያዩ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በዚህም ሴቶች Hard Skill የሚባሉ የሙያ ዘርፎችን ደፍረው እንዳይቀላቅሉ ምክንያት ናቸው ያሏቸውን መንስኤዎች በዝርዝር አንስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል:: በቀጣይም ከመድረኩ በተገኙ ግብዓቶች እንዲሁም ተጨማሪ በሚደረጉ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቶች መሰረት የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት ወደ ትግበራ እንደሚገባም ተገልፇል:: በEASE ፕሮጀክት በአለም ባንክ በሚደርግ ድጋፍ ለቀጣይ 5አመት በሚቆየው ፕሮጀክት ውስጥ የትኩረት ዘርፍ ተብለው በተመረጡ 3 የሙያ መስኮች (Manufacturing, Electrical/Electronics, Automotive) ላይ በትኩረት የሚሰራ ሲሆን ሴቶች በነዚህ ዘርፎች ላይ ተሳትፎ ቢያደርጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸውም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 10/2017 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ አመራር ኮሚቴ በዛሬው እለት በካሄደው ስብ ሰባ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ የውሳኔ ሃሳብ ያስተላለፈ ሲሆን በተለይም በቀጣይ እንደ ቢሮ በትኩረት የሚፈጸሙ አቅጣጫዎችን ከዚህ እንደሚከተለው አስቀምጧል፡- 1.  መለየት፡- የአካባቢን ጸጋ በአግባቡ መለየት፤ የሥራ ፈላጊዎችና ኢንተርፕራይዞችን መለየት፤ ከልምድ የተገኘ ክህሎት ያላቸውን መለየት፤ በኢ መደበኛ የተቀመጡ ኢንተርፕራይዞችን መለየት፤ 2.  ማዘጋጀት፤- አመራሩ በሚናው ዙሪያ ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ፤ አቅም የሚፈጥሩ ኢንዱስትሪዎችን ለይቶ ማዘጋጀት፤ ሥራ ፈላጊዎችና ኢንተርፕራይዞች በቂ እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው ማዘጋጀት፤ 3.  መደገፍ፡- ተቋማትን መለየት ማዘጋጀትና መደገፍ፤ ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን መስራት፤ 4.  ማሸጋገር፡- ከሥራ አጥነት ወደ ተወዳዳሪ ዜጋ ማሸጋገር፤ የተመዘገቡ ሥራ አጦችን ከLMIS ላይ በተጨባጭ መውሰድና ማሸጋገር፤ ኢንተርፕራይዞችን ማሸጋገር፤ ከኢ መደበኛ ወደ መደበኛ ማሸጋገር፤ ኢ መደበኛ አንቀሳቃሾችን በአንድ ቦታ በማደራጀት ማሸጋገር፤ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

"ብሩህ አዕምሮዎች፣በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር መካሄድ ጀመረ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት የሚካሄደው 4ኛው የክህሎት ውድድር ጋር ተያይዞ በተቋም ደረጃ የሚደረገውን ውድድር በዛሬው እለት አስጀምሯል:: በተቋም ደረጃ በዛሬው እለት በተካሄደው ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎችን ያሳተፈ ውድድር ሲሆን በመጀመርያው ቀን የውድድሩ ውሎም.... በAuto mechanics በAutomotive body repair & painting wor በBuilding Electrical Installation በIndustrial Electrical/Electronic control technology በFinishing Construction work በPlumping installation በStructural construction work በWood work technology.... የሙያ ዘርፎች ውድድሮች ተካሂደዋል:: ይህ በተቋም ደረጃ የተጀመረው ውድድር በቀጣይ ቀናትም በቀሩት የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድሩ የሚደረግም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 10/2017 ዓ.ም

ኮሌጁን ዘመናዊና ለስራ ምቹ እንዲሆን የኮንስትራክሽን ትምህርት ክፍል እንደሚሰራ ገለጸ፡፡ የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ አሰልጣኝ መምህር ተሾመ ሸለመ በዛሬው እለት እንደገለጹት ኮሌጁ ለስራ ምቹ እንዲሆንና
+4
ኮሌጁን ዘመናዊና ለስራ ምቹ እንዲሆን የኮንስትራክሽን ትምህርት ክፍል እንደሚሰራ ገለጸ፡፡ የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ አሰልጣኝ መምህር ተሾመ ሸለመ በዛሬው እለት እንደገለጹት ኮሌጁ ለስራ ምቹ እንዲሆንና ዘመናዊ ይዘት እንዲኖረው ትምህርት ክፍሉ እየሰራ እንዳለ የገለጹ ሲሆን ያይዘውም ለኮሌጁ የተለያዩ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን ከመደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት በዘለለ ምርቶችን ለማምረትና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ብሎም ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማቅረብ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንዳለ አስረድተዋል፡፡ ይህንንም ምርት ለማምረት የቦታ መረጣ፣ለማሽነሪዎች ምቹ ቦታ በመምረጥ የማስቀመጥ ስራዎች እንዲሁም ለምርት የሚያገለግሉ የተለያዩ ማሽነሪዎች ጥገና ስራ አከናውነናል ብለዋል፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ መሳካት ሁሉም የትምህርት ክፍል አባላቶች በስራው ላይ አመርቂ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢንጅነሪንግ ኮሌጅ የተወጣጣ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሌጅ የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ አካሄደ:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታም አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ እና ያለበትን ደረጃ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፊ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን እንዲሁም በቀጣይ ሁለቱ ተቋማት በትብብር ሊሰሩ በሚችሉበት አግባብ ላይ የሁለትዮሽ ውይይት ተካሂዷል:: በነበረው የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ ልዑካን ቡድኑ ከተደረገላቸው ገለፃ በተጨማሪ በቀጣይ በምን ዘርፍ በትብብር ለመስራት ያስችላል ሚለውን ለመለየት ኮሌጁ ያለውን ፋሲሊቲ እና ማሰልጠኛ ወርክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን ኮሌጁ በዚህ መልኩ ራሱን በማራጀራጀቱም አድናቆታቸውን ለግሰዋል:: በቀጣይም ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ ባገኙት የተሞክሮ ልምድ ልውውጥ መሰረት ሁለቱ ተቋማት በተለያዩ ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር እንደሚገቡም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 6/2017 ዓ.ም

#ዜና| በድሬዳዋ አስተዳደር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በምግብ ዋስትና መርሀግብር በማቀፍ ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የሚሸጋገሩበትን እድል ለመፍጠር አስተዳደሩ ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ ትኩረት ሰጥቶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ። #Diretv አማርኛ መጋቢት 6/2017 የሁለተኛው ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮጀክት ተጠቃሚ የምረቃ ሥነስርዓት ተካሂዷል። የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራ ፕሮጀክት (upsnjp) ተጠቃሚ ቤተሰቦች የምረቃ እና የርክክብ ፕሮግራም ተካሂዷል ። የከተሞች ምግብ ዋስትና ፕሮግራም በኢትዮጵያ መንግስት በሚመደብ በጀትና እና ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ገንዘብ በሁለተኛው ምዕራፍ በሀገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ 88 ከተሞች እና ክልሎች ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን ከተማችን ድሬደዋ አንዷ ተጠቃሚ ናት። የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ተጠቃሚ ከሆኑ በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞች መካከል አንዱ ሲሆን በፕሮግራሙ የመጀመሪያው እና ሁለተኛው ምዕራፍ ብዙ ሺ ዜጎች ከድህነት እና ስራ አጥነት እንዲላቀቁ ምቹ እድል ተፈጥሮላቸዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት የምግብ ዋስትና ዳይሬክቶሬት ሲያስፈፅም የቆየዉ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት የስራ ፕሮጀክት በሁለተኛ ምእራፍ አንደኛ ዙር ተጠቃሚ ቤተሰቦች ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው የደሃ ደሃ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በስድስት የከተማ ወረዳዎች ማለትም በ04፣ 05፣ 06፣ 07፣ 08 እና 09 በድምሩ አንድ ሺህ ሰባት መቶ ሃያ አራት (1724) ቤተሰቦችን በአካባቢ ልማት ንኡስ ፕሮግራሞች በመታቀፍ ለሶስት አመታት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሲደረግ ቆይቷል። የፕሮግራሙ ተጠቃሚ የነበሩና የዛሬ ተመራቂዎችም ከዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ከሶስት አመት ቆይታ በኋላ ወደ መደበኛ ስራ እድል ፈጠራ የተሸጋገሩ ሲሆን ካሉበት የኑሮ ደረጃ  እንዲሻሻሉ ከማገዝ ባለፈ የከተማዋን ማጽዳትና ዉበት በማሻሻል ÷ የከተማ ግብርና እንዲጠናከር እንዲሁም የተለያዩ የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ይበልጥ እንዲስፋፋ የበኩላቸዉን ድርሻ የተወጡ መሆናቸዉን ከመድረኩ ተገልጿል ። በመድረኩ ተገኝተዉ ለተመራቂዎች መልዕክታቸዉን ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የዜጎች የኑሮ ደረጃ እንዲሻሻል በማድረግ የበለፀገች እና ለሁሉም የምትመች ሀገርን ዕዉን ለማድረግ መንግስታቸዉ ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፀዉ በድሬዳዋ አስተዳደርም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በምግብ ዋስትና ፕሮግራም በማቀፍ ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የሚሸጋገሩበትን እድል ለመፍጠር አስተዳደሩ ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ ትኩረት ሰጥቶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን አንስተዋል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ኢንጅነር ጀማል ኢብራሂም በበኩላቸዉ በፕሮጀክቱ ሶስት አመታት በ21 የስልጠና ርእስ የተከፋፈለ የገንዘብ አጠቃቀምና አያያዝ፣የህይወት ክህሎት፣ የንግድ ስራ አመራር፣ የንግድ ሥራ ዕቅድ የክህሎት ማሳደጊያ ሥልጠና እና ተከታታይነት ያለዉ የድጋፍና ምክር አግኝተዋል ብለዋል ። ወ/ሮ ብርቱካን አስራትና ወ/ሮ ጡርዬ በየነ የ08 እና 04 ወረዳ ነዋሪዎች ናቸው፤ በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ተጠቃሚ በመሆናቸው ከተረጂነት እራሳቸዉን ችለዉ የተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዲገኙ እንዳስቻላቸዉ ተናግረዋል ። በመጨረሻም የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች በቀጣይ በሚኖራቸው የቦታ፣የገንዘብ ይሁን የስራ ምችችት ማንኛውም ነገር በተመለከተ በስራና ክህሎት ቢሮ በኩል እንዲሆን የሰነድ ፊርማ ተፈራርመዋል ። ©️ ድሬ ቲቪ

photo content
+7