uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 089
Підписники
+324 години
+257 днів
+1730 день
Архів дописів
photo content
+5

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድር ዋስትና ፈንድ ደንብ ዙሪያ ለኢንተርፕራይዞች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡ በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከዚህ ቀደም የነበረውን የብድር ዋስትና ፈንድ ደንብ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ተሻሽሎ በቀረበው ደንብ ላይ ለመወያየት ከድሬዳዋ ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡ ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም ለብድር ተጠቃሚዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከማግኘት አንጻር ያለው የድጋፍና ክትትል እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት የቅንጅት ክፍተት በሰፊው ተነስቷል፡፡ በማጠቃለያው በቢሮው የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማሪያም በበኩላቸው የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት በመስጠት በድሬዳዋ አስተዳደር ብቻ እየተሰጠ የሚገኘውን ይህን የብድር ዋስትና ፈንድ አገልግሎትን ደንቡንና አሰራሩን የማሻሻልና ተግባር ከሚመለከታቸው ጋር በቅንጅት እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 17/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን እና ለቀበሌ አንድ ማዕከል አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች በ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የተከናወኑ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዙሪያ ግምገማዊ የስልጠና መድረክ አዘጋጀ:: ዳይሬክቶሬቱ ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዕቅድ አፈጻጸም በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የቀረበ ሲሆን ኮሌጆቹ በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችንና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንደስትሪዎችን  የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ በማስቻል የተሰሩ ስራዎች ቀርበዋል፤ በአጠቃላይ አፈጻጸሙ ላይ ከሚመለከታችው ለሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን እና ለቀበሌ አንድ ማዕከል አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ጋር በመሆን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ማድረግ ተችሏል፤ በኤጀንሲው የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ለተመዘገበው መልካም አፈጻጸም ምስጋና አቅርበው ወደ ኋላ የቀሩ ተግባራትን ትኩረት በመስጠት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

የድሬዳዋ ወጣት ምሩቅ ሥራ ፈላጊዎች በድሬዳዋ ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል ለማሳየት ፍላጎትና ተነሳሽነታቸውን ከፍ የሚያደርግ በተከታታይ ለዩኒቨርስቲ እና ኮሌጅ ምሩቃን ሥራ ፈላጊዎች በመሰጠት ላይ የሚገኘው  የማይንድ ሴት ስልጠና ቀጥሎ ዛሬም ተሠጠ። ይህም ስልጠና የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች የተወጣጡ ስራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ስራ ፈጣሪ ለማድረግ አቅማቸውን ለመገንባት ታስቦ በተከታታይ በመሰጠት ላይ ይገኛል። ቢሮው በአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን ለሽራ የተዘጋጁ ለማድረግና የተጀመሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር  ተመራቂዎች ስራን ሳይንቁ ተደራጅተው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ በማገዝ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ተጠቃሚ እንደሚደረጉ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል ። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የግል ኮሌጆች ላይ ኢንስፔክሽን ማካሄዱን ቀጥሎ በሪፍት ቫሊ ዩንቨርሲቲ ኮሌጅ ላይ ምልከታ አካሄደ፤ በዚህም ኢንስፔክሽን ኮሌጁ የሚሰጠውን ትምህርትና ስልጠና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተሰጠ ስለመሆኑ በአካል በመመልከትና በማረጋገጥ የሚታዩ ክፍተቶችና ችግሮች ቢኖሩ በአጭር ጊዜ ለማስተካከል እዲያስችል ግብረመልስ የሚሰጠው ይሆናል። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ስለ ኢንስፔክሽኑ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ጥራትን ማረጋገጥ ዋና አላው አድርጎ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላትና ባለድርሻ አከላት ጋር በቅንጅት  ሴክተሮችን ባሳተፈ መልኩ እየተካሄደ መሆኑንና በሁሉም ኮሌጆች የሚቀጥል መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

"ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ድህነትን ድል መንሳትና የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው፡፡" ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር በዘርፉ የሪፎርም ሥራዎች ላይ ያተኮረ የሥልጠናና የምክክር መድረክ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎች እና ከፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች ጋር እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በመድረኩ የዘርፉን አዲስ እሳቤና በሚኒስቴር መ/ቤቱ እየተከናወኑ የሚገኙ የሪፎርም ሥራዎችን አስመልክተው ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለፃ አድርገዋል፡፡ ክብርት ሚኒስትር በሰጡት ማብራሪያ ዘርፉ ዜጎችን ከድህነት የሚያወጡ ሰው ተኮር ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸው ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነትም ድህነትን ድል መንሳትና የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡ ክህሎትን የማሰቢ መንገድ አድርጎ መውሰድ፣ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ የሚሰጡ ሥልጠናዎች ገበያ መር ማድረግ ፣ ሰልጣኞች የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ ፈጥረው እንዲወጡ ማስቻል ፣ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ ሥልጠናዎች በአንተርፕረነርሺ እሳቤ መቃኘት እና ተቋማቱ እራሳቸውን የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር የክህሎት ዘርፍ ዋነኛ የሪፎርም አጀንዳዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የሥራ ዕድል የሚፈጠርላቸው ዜጎች መሰረታዊ የሚባሉ ክህሎቶች የታጠቁ እንዲሆኑ መሥራት፣ ከፍተኛ የማደግ አለኝታ ያላቸው ኢንተርፕራይዞች በልዩ ሁኔታ መደገፍ እና የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ንግድ ማስፋፋት ከሥራ ዕድል ፈጠራ አኳያ ያሉ አንኳር እሳቤዎች ናቸው ብለዋል፡፡ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ከዚህ በፊት የነበረውን ትርክት ምርታማነትን ማዕከል ባደረገ የግንኙነት አግባብ መቀየር እና አዲስ የኢንዱስትሪ ባህል መገንባት ላይ ትኩረት ያደረገ አዲስ እሳቤን እንደሚከተልም ገልፀዋል፡፡ የዘርፉ ተልዕኮ የትናንትን ዕዳ፣ የዛሬን ዕድልና የነገን ተስፋ መሰረት ያደረገ ነው ያሉት ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት አገርና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ተልዕኮን በፍጥነትን ፣ በብዛትንና በጥራት መፈፀም ከእያንዳንዱ የዘርፉ አስፈፃሚ አካል የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት መሆኑን በአፅንኦት ተናግረዋል። ምንጭ:- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

photo content
+5

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፌደራል ማረሚያ ቤት ኮምሽን ድሬዳዋ ማረሚያ ቤት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራረሙ፡፡ በስምምነቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉትና የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በዋነኝንት ትምርተና ስልጠናዎችን ከመስጠት በዘለለ ማህበረሰባዊ ግዴታቸውንም መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ስለሆነም በዛሬው እለት ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮምሽን ድሬዳዋ ማረሚያ ቤት ጋር የምንፈራረመው ይህ የመግባባያ ስምምነት ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው የግል ፍላጎታቸው ላይ መሰረት ባደረጉ የትምህርትና ስልጠና አገልግሎቶችን በማመቻቸት አገልግሎቱ ስልጣን ባለዉ አካል በወጣ ስርአተ-ትምህርት መሰረት በማድረግ ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና አገልግሎት ታራሚዎች እንዲያገኙ በማድረግ ምርታማ ታራሚ እንዲሆኑና ከታረሙ በኋላም ሙያ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሆኑ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም ኮሌጃችን ትምህርትና ስልጠናዎችን ለታራሚዎች ከመስጠት በዘለለ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመስራት ለማረሚያ ቤቱ የሚያቀርብ ይሆናል ይህ ደግሞ ማረሚያ ቤቱ በሃገር በቀል ቴክኖሎጂዎች እንዲደራጅ እድል ይፈጥርለታል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ማረሚያ ቤቱን በመወከል የጋራ ስምምነቱን የፈረሙትና ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ማረሚያ ቤት ኮምሽን ኃላፊ የሆኑት ም/ኮምሽነር ወንድሙ በዛሬው እለት የምንፈራረመው ይህ የጋራ የመግባቢያ ስምምነት በማረሚያ ቤቱ ውስጥ የሚገኙ ታራሚዎቻችን የእውቀት ሽግግር እንዲኖርና የአመለካከት ለውጥ እንዲሁም የስብእና ግንባታ የሚረዳን የመግባቢያ ስምምነት ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም ይህ ስምነት ከማረሚያ ቤቶቻችን ታርመው የሚወጡ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ እውቀት፣ክህሎት ያለውና ስራ ፈጣሪ የሆነ ማህበረሰብን መፍጠር እንድንችል ያደርገናል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ይህ ስምምነት ከግብ እንዲደርስ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ሲከታተሉ ለነበሩት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱላሚድ እንዲሁም ለሌሎች የኮሌጁ ኃላፊዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ከስምምነት ፊርማው በኋል ማረሚያ ቤቱ የሚሰጣቸውን የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለማረሚያ ቤቱ እየሰራው ያለው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ግብኝ ተደርጓል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት በጾታዊ እኩልነት፣አካታች እቅድ እንዲሁም ሴቶችን በማብቃት ወደ አመራርነት እንዲመጡ ለማድረግ የታሰበ Gender Mainstream, Inclusive
+4
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት በጾታዊ እኩልነት፣አካታች እቅድ እንዲሁም ሴቶችን በማብቃት ወደ አመራርነት እንዲመጡ ለማድረግ የታሰበ Gender Mainstream, Inclusive Planning And Women Empowerment and Leadership በሚሉ ርእሶች ሲሰጥ ነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ፡፡ በስልጠናው መዝጊያ ላይ በመገኘት የመዝጊያ ንግግር ያደረጉትየኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም ላለፉት 3 ቀናት ሲሰጥ የነበረው ይህ ስልጠና በዋናነት የጾታ እኩልነትና ሴቶችን በማብቃት ወደ አመራርነት እንዲመጡ እንዲሁም አካታች እቅዶችን በማዘጋጀት የሴቶችን ተሳትፎ ከፍ ማድረግ ሲሆን ከዚህ ስልጠናም ሁላችሁም በዚህ ስልጠና የተካፈላችሁ በቂ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ እተማመናለሁ፡፡ በቀጣይም በስራ ክፍሎቻችሁ ይህን የስልጠና አላማ እንድታሳኩ ለማሳሰብ እወዳሉያሉ ሲሆን አያይዘውም ኮሌጃችን ለጾታዊ እኩልነት ተግቶ የሚሰራ ኮሌጅ እንደመሆኑ መጠን በቀጣይ በምንሰራቸው ስራዎች እንዲሁም እቅዶች ሁሉ ሴቶችን ያሳተፈ ስራዎችን የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በስልጠናው ላይ የኮሌጁ አመራሮች፣የማኔጅመንት አባላት፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ፣ኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እንዲሁም ከስራና ክህሎት ቢሮና በስሩ ከሚገኙ ተቋማት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሳትፈዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 13/2016 ዓ. ም ድሬዳዋ

ከዩኒቨርስቲ እና ከኮሌጅ ተመርቀው ሥራ በመፈለግ ላይ ለሚገኙ ወጣቶች የማይንድ ሴት ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከ
+6
ከዩኒቨርስቲ እና ከኮሌጅ ተመርቀው ሥራ  በመፈለግ ላይ ለሚገኙ ወጣቶች የማይንድ ሴት ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች የተወጣጡ ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ሥራ ፈጣሪ ለማድረግ አቅማቸውን ለመገንባት ታስቦ ተሰጥቷል። ቢሮው በአስተዳደሩ ትኩረት  የተሰጠውን የሥራ አጥ ቁጥር ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ የተጀመሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር  ተመራቂዎች ተደራጅተው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ብዙዎች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል። ተሳታፊ ምሩቃን ሥራ ፈላጊዎችም ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ይጠብቁ የነበሩበትን አመለካከት ከስልጠናው ባገኙት ግንዛቤ በግልም ሆነ ተደራጅቶ ለመስራት መነሳሳት እንደሚፈጥርባቸውና ይህን መሰል ስልጠናዎችንም ለወጣቶች ማዘጋጀት ወደ አስተዳደሩ እየመጡ ያሉ የሥራ እድሎችን ለመጠቀም ምቹ መደላድል መፍጠር ላይ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ  11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት በጾታዊ እኩልነት፣አካታች እቅድ እንዲሁም ሴቶችን በማብቃት ወደ አመራርነት እንዲመጡ ለማድረግ የታሰበ Gender Mainstream, Inclusive Planning And Women Empowerment and Leadership በሚሉ ርእሶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተጋበዙ አሰልጣኞች ለኮሌጁ አመራሮች እንዲሁም ኬዝ ቲም አስተባባዎች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡ በስልጠናው ላይ በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን እንደ ገለጹት እንደሚታወቀው ሃገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላለችብት እድገት እንዲሁም ቀጣይ ለምትደርስበት የእድገት ደረጃ ለመድረስ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነዉ። ስለዚህ ሴቶችን በማብቃትና አካታች እቅዶችን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም ደግሞ ኮሌጃችን ጠንከሮ እየሳራ ይገኛል በዚህም መሰረት ደግሞ በኮሌጁ የሚገኙ ትምህር ክፍሎችን ከ50 ፐርሰንት በላይ በሴቶች እንዲደራጅ አድርገናል፡፡ ለዚህ ደግሞ በትምህርት እንዲሁም በተለያዩ ስልጠናዎች የግንዛቤ ችግሮችን በመፍታት ሴቶችን የእቅዶች አካል በማድረግ ጠንክረን በመስራት ሴቶችን ወደ አመራር ለማምጣት እድል ልንሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም የጾታ እኩልነትና ሴቶችን በማብቃት ወደ አመራርነት እንዲመጡ እንዲሁም አካታች እቅዶችን በማዘጋጀት የሴቶችን ተሳትፎ ከፍ ማድረግ ይኖርብናል ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ኮሌጁ በሴቶች ተሳትፎ ለሌሎች ኮሌጆች አርአያ መሆን የሚችሉ በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በስልጠናው ላይ የኮሌጁ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት፣ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ፣ ኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እንዲሁም ከስራና ክህሎት ቢሮና በስሩ ከሚገኙ ተቋማት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው ለ3 ቀን የሚቆይ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 11/04/2016 ዓ. ም ድሬዳዋ

ማስታወቂያ የውጭ ሃገር ዜጎች ሆናችሁ የስራ ፍቃድ ወስዳችሁ በኢትዮጲያ ውስጥ በስራ ለተሰማራቹ እንዲሁም የውጭ ሃገር ዜጎችን ቀጥራችሁ ለምታሰሩ ተቋማት በሙሉ !! የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት፣ በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በመረጃ ጥራት ዙሪያ ያሉ የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት እንዲሁም ለዜጎችና በዘርፉ አገልግሎት ለሚሹ የውጭ ሃገር ዜጎች ቀልጣፋ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል የኢትዮጲያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት(E-LMIS) አካል የሆኑ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በውስጥ አቅም አልምቶ ተግባራዊ በማድረግ ለአገልግሎት እያበቃ ይገኛል። በኢትዮጲያ ውስጥ የውጭ ሃገር ዜጎችን ቀጥረው ለሚያሰሩ ድርጅቶች እንዲሁም የስራ ፍቃድ በመውሰድ በስራ ለተሰማሩ የውጪ ዜጎች ካሉበት ሆነው በዘመነ መንገድ የአዲስ የስራ ፍቃድ እና ዕድሳት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶችን  ማግኘት የሚያስችል “Expat Work Permit System” አልምቶ ተግባራዊ አድርጓል። ይሄ ስርዓት ቀደም በነበረው የአሰራር ስርዓት ከ1 ወር በላይ ይወሰድ የነበረውን አዲስ ፍቃድ እና ዕድሳት በ20 ደቂቃዎች አገልግሎቱን መስጠት የሚያስችል እንዲሁም በዘርፉ ያጋጥም የነበረ ወጥነት የጎደለው የአሰራር ስርዓትና ብልሹ አሰራርን የሚያስቀር ስርዓት ነው። በመሆኑም የውጭ ሃገር ዜጎች ሆናችሁ የስራ ፍቃድ ወስዳችሁ በኢትዮጲያ ውስጥ በስራ ለተሰማራቹ እንዲሁም የውጭ ሃገር ዜጎችን ቀጥራችሁ የምታሰሩ ተቋማት መረጃዎቻችሁን የE-LMIS ስርዓት አካል በሆነው በ ”Expat Work Permit” ሲስተም አድርሻ https://ewp.lmis.gov.et/  እንድታስገቡ  እና የዚህ ዘመናዊ አገልግሎት ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳስባለን። የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ኖዎት !

photo content