1 091
Підписники
+324 години
+257 днів
+1730 день
Архів дописів
የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኙ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ኢንተርፕራይዞች ፍትሃዊ መንግስታዊ ድጋፎች ተጠቃሚ በማድረግ የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አድርገዋል።
ኮሌጆቹ ድጋፍ በመስጠት በአስተዳደሩ ጉልህ ስራዎችን እየሰሩ ሲሆን በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችንና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንደስትሪዎችን የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ በማስቻል ድጋፍ እየሰጡ እንደሚገኙ ይታወቃል፤
የሁለቱ ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች በጋራ በመሆን ይህን መድረክ ያዘጋጁ ሲሆን ለባለድርሻ አካላትም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጽንሰ ሃሳብ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ለቀጣይ የመፍትሔ አማራጮች የ2016 ዓ.ም የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ውጤት አምጪ ተግባራት ላይ ትኩረት ይደረጋል፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ተገኝተው የክትትልና ድጋፍን በማጠናከር፤ ከኢንተርፕራይዝ ልየታ ጀምሮ እስከ ምዘና እና ሀብት ልኬት እንዲሁም ደረጃ ሽግግር ድረስ ያሉት ተግባራት በጥብቅ ቅንጅት መከናወን እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 4/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ማሳሰቢያ
በድሬዳዋ አስተዳደር ለምትገኙ የግል እና የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ማሰልጠኛ ተቋማት በሙሉ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ12ኛ ክፍል አጠናቃቂ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ የስልጠና ተቋማት የሚያስገባቸውን መቁረጫ ነጥብ በይፋ መገለጹን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን፤
ይሁንና አንዳንድ ተቋማት ምዝገባ መጀመሩን የሚገልጹ ማስታወቂያዎችን የሚያስነግሩና የሚመዘግቡ እንዳሉ ለመመልከት ችለናል አግባቡ ግን ምዝገባ መጀመሩን የሚገልጽ ማስታወቂያ ማስነገርም ሆነ መመዝገብ የሚቻለው የመቁረጫ ነጥብ በይፋ ከተገለጸ በኋላ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም ሁሉም ተቋማት እንዲያሰለጥኑ እውቅና ባላገኙ እና ፈቃድ ባልተሰጣቸው ሙያዎች እንዲሁም የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ከመሆኑ በፊት የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያዎችንም ሆነ ምዝገባ ማድረግ የማይቻል መሆኑን አውቀው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እያሳሰብን ማሳሰቢያውን ተላልፈው በተገኙ ላይ ግን የእርምት እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬት የማሰልጠን ስነ-ዘዴ/ Training Methodology/ ላይ ስልጠና ላልወሰዱ ከለሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አሰልጣኞችና ከግል ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች ለሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ስልጠናን ለተከታታይ 8 ቀናት የሚቆይ ስልጠና መስጠት ጀመረ፤፤
በስልጠናውን መጀመር በንግግር የከፈቱት የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ውጤታማ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና አሰጣጥ ሥርዓትን በመተግበር ሙያው የሚጠይቀውን ዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት በበቂ ሁኔታ ለሰልጣኞች በማስረጽ በክህሎት የዳበሩና ስኬታማ የሆኑ ሰልጣኞችን ለስራ ገበያው ለማቅረብ የሚችሉ በአስተዳደራችን የሚገኙ ብቁ አሰልጣኞችን ማፍራት የቢሮው፤ የኤጀንሲው ብሎም የዳይሬክቶሬቱ ቁልፍ ተግባር መሆኑን በመግለፅ ሰልጣኞች በስልጠናው በሚቆዩባቸው ቀናት የሚጠበቅባቸውን የተግባር ስራዎች በማሟላት በስልጠናው ማጠናቀቂያ የሚኖረውን ምዘና ብቁ ለመሆን በንቃት ተሳታፊ እንዲሆኑ አሳስበዋል፤፤
ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አክለውም አሰልጣኞች በሙያቸው የሚጠበቅባቸውን የእውቀት፣ የክህሎትና የሙያ ስነምግባር በመላበስና በሙያቸው ብቃታቸውን ከማረጋገጥ ባሻገር፣ የማሰልጠን ስነ ዘዴ ስልጠና/Training Methodology/ በመሰልጠን አሰልጣኞች ሊኖራቸው የሚገባውን የሙያ ብቃት ማዕቀፍ/ Training Qualification Frame Work/ ስታንዳርድ ማሟላት እንዳለባቸው የዘርፉ ስትራቴጂ ማስቀመጡን አውስተው፤ የዘርፉ ስልጠና አሰጣጥ ስርአትም ውጤትን መሰረት ያደረገ/Out Come Based Training / መሆኑ፤ ይህንንም የሚያስተገብሩት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት እና ጥራት ያለው ስልጠና በመስጠት ብቁ የሆነ የሰው ሀይል የማፍራት ተልዕኮን በመወጣት ምንግዜም የማይተካ ሚና ያላቸው አሰልጣኝ መምህራን መሆናቸውን ገልጸዋል፤፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የተለያየ ዘርፍ ስር ለሚገኙ ኢንደስትሪዎችና ኢንተርፕራይዞች አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ተሰጠ።
በቢሮው የውጭ አገር ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የሰራተኛውን ደህንነትና ጤና የማስጠበቅ ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል አይደለም።
በዚህም በኢንደስትሪዎቹ እና በየኢንተርፕራዞቹ የሙያ ደህንነትና ጤንነት ኮሚቴ አንዲደራጅና እንዲቋቋም ድጋፍ በማድረግ ለተመሰረቱት ኮሚቴዎችም በቀጣይ ስለሚያከናውኗቸው ስራዎች በማስገንዘብ በተለይ የሙያ ደህንነቱና ጤናው የተጠበቀ የስራ አካባቢን በመፍጠር የኢንደስትሪውን ሰላም እና ደህንነት በማስጠበቁ ረገድ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑንና በተጨባጭም ውጤት የሚያስገኝ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ችግር ፈቺ በሆነ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለቢሮ ባለሙያዎች እና ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ተሰጠ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በዘርፉ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እና ባለሙያዎች እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል
በዚህም ከቢሮው ለተወጣጡ ባለሙያዎች እና ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ለተወጣጡ የአሰልጣኝ መምህራን በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዘጋጀት አቅም የሚገነቡበትን እድል ፈጥሯል፤ ይህም ስልጠና መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ከተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለው ልዩነት፤ የአጠናን ስነ-ዘዴን በማወቅ የተቋማዊ ችግሮች ልየታ፤ ምልከታ በማድረግ ለተግባራዊ ጥናትና ምርምር ማድረግ በሚያስችሉ ጽንሰ ሃሳባዊና ተግባራዊ ዝግጅት ማድረግ የሚያስችል ይሆናል፤
ስልጠናውም ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኝ የተሰጠ ሲሆን የስልጠናውም ዋና ዓላማ ባለሙያዎችና አሰልጣኝ መምህራኑ በስራ ቦታቸው ላይ ያሉ ችግሮችን ተግባራዊ ልየታ በማድረግ በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ እንዲፈቱ በሚያስችል አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ነው፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማት መካከል የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ አቅሞችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለ ድርሻ ተቋማት ጋር እካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የጥ/ቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አገልግሎት አቅዶ ከሚሰራባቸው ግቦች መካከል በዘርፉ ላይ የሚታዩ ውስነቶችን በሚያሻሽል መልኩ የጥናትና ምርምር፣ የፈጠራ ስራዎች፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር የSTEM እውቀቶች እንዲሁም የማህበረሰብ አገልሎትቶችን የማሳደግ ስራዎች የሚገኙበት ሲሆን እነዚህን ስራዎች ውጤታም ለማድረግ ከባለድርሻ ተቋማት ጋር አጋርነትና ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ የተዘጋጅ የውይይት መድረክ ነው::
በዕለቱ በነበረው መድረክ በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ርዕሰ መምህራን፣ ምክትል ርዕሰ መምህራን እንዲሁም የቴክኖሎጂ ክበብ ተጠሪዎች በውይይት መድረኩ የተካፈሉበትም ነበር::
በመድረኩ ለተካፈሉ ባለ ድርሻ ተቋማትም በቴ/ሙ/ት/ስ ስትራቴጂ ላይ ሰፊ ገለጻ በማድረግ በSTEM እና INNOVATION እንዲሁም ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ግንዛቤ በመፍጠር እና የ2016 ረቂቅ ሰነድ ላይ በመወያየት የጋራ ስምምነት ላይ መድረስም ተችሏል፡፡
በመጨረሻም ግንዛቤ ከመፍጠሩ ባሻገር በቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ ኮሌጁ ውስጥ ያለው አቅምን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ከኮሌጁ ጋር በትብብር ለመስራት ይበልጥ ፍላጎት እንዳሳደረባቸው ጨምረው ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 30/2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ ድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ስለሆነም ሰልጣኞች ኮሌጃችንን ተመራጭ አድርገው እንዲመጡ የተለያዩ የቅስቀሳ መድረኮች ተዘጋጅተዋል ከነዚህም ውስጥ በነገው እለት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የኮሌጁ የጤና ቡድን ከድሬዳዋ አብያተ ክርስቲያን የጤና ቡድን ጋር በሳቢያን ሜዳ የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል በዚህም በአካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች ስለኮሌጃችን ቅስቀሳ የምንሰራ ይሆናል ስለሆነም በእለቱ በመገኘት ለቡድኑ ድጋፍ እንድታደርጉ በዛውም ኮሌጃችሁን እንድታስተዋውቁ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን
Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የግዢና ፋይናንስ ስራ ሂደት አዲስ በተገነባው ቢሮው በዛሬው እለት ስራውን ጀምሯል::
ኮሌጁ በሪፎርም ስራዎች እየሰራባቸው ከሚገኙ ስራዎች ውስጥ የስራ ቦታን ለሰራተኛው ምቹ የማድረግ ስራ የሚገኝበት ሲሆን ዛሬ ተመርቆ ስራ የጀመረው የኮሌጁ የግዢና ፋይናንስ ስራ ሂደት ቢሮም የዚህ ማሳያ ነው::
ይህ የስራ ክፍሎችን የማዘመና ምቹ የማድረግ ስራ በሌሎች የስራ ክፍሎችም ጭምር ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ወደተቋሙ የሚመጡ ተገልጋዮችን ምቹ በሆነና በተቀላጠፈ መንገድ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ታቅዶ እየተሰራ የሚገኝ ተግባር ነው::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 26/2016 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ የጤና ቡድን ከለገሃሬ የጤና ቡድን ጋር የወዳጅንት ጨዋታ በትናንትናው ዕለት በለገሃሬ ሜዳ ላይ አደረገ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘንድሮ አመት ከ2000 በላይ አዳዲስ ሰልጣኞችን በቀንና በማታ ተቀብሎ ለማሰልጠን በዝግጅት ላይ እንዳለ የሚታወቅ ሲሆን ይህንን ተግባሩን ደግሞ ሊደግፍ የሚችል አሰራሮችን በመቀየስ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡ስለሆነም ለቅስቀሳ እንዲሁም ኮሌጁን ለማስተዋወቅ ከሚጠቀምባቸው መንገዶች መካከል በኮሌጁ የሚገኘውን የጤና እግር ኳስ ቡድንን ከሌሎች ተጽእኖ ፈጣሪ የጤና ቡድኖች ጋር በማጫወት ኮሌጁን የማስተዋወቅና የ12ኛ ክፍል አጠናቃቂዎች የመንግስት ፖሊ ቴክኒኮችን ተመራጭ እንዲያደርጉ የቅስቀሳ ስራን ማከናወን ነው፡፡ በዘህም ስራ ላይ በትናንትናው እለት የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክት የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ፣ የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክተር እንዲሁም የኮሌጁ ዲንና ም/ዲን በተገኙበት በለገሃሬ ሜዳ የቅስቀሳ ስራውን አከናውኗል፡፡
በዚህም ስራው በለገሃሬ አካባቢ የሚገኙ ወጣቶችን ተደራሽ ያደረገ የቅስቀሳ ስራ እንዲሁም ስለ ቴክኒክና ሙያ የገጽታ ግንባታ ስራ አከናውኗል፡፡በወዳጅንት ጨዋታውም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 3 እንዲሁም የለገሃሬ የጤና ቡድን 3 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 26/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
‹‹ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች የብልጽግና መሰረት ነው በሙያ እና ክህሎት የታጠቁ እና የበለፀጉ ተማሪዎች የሚሰበሰቡበት፣ በላባቸው እውቀት አምርተው ፣ በእጃቸው ሰርተው እራሳቸውን መጥቀም የሚችሉ ከዛም አልፎ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች የሚፈሩበት ተቋም ነው፡፡››
ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ
የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክትር
**********************
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች ጋር በጋራ በመስራት 12ኛ ክፍል አጠናቃቂዎችን ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በማምጣት ስልጠናዎችን በመስጠት ዙሪያ የመወያያ መድረክ በድሬዳዋ ፖሊ ቴሊቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡
በመድረኩ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክትር የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸም እንኳን ወደዚህ መድረክ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን በማስቀጠልም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የወደቁ ተማሪዎች የሚሰበሰቡበት ሳይሆን በላባቸው አምርተው በእጃቸው ሰርተው እራሳቸውን መጥቀም የሚችሉ ከዛም አልፎ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች የሚፈሩበት ተቋም ነው፡፡ስለዚህ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን ተመራጭ በማድረግ ረገድ አብረን በጋራ መስራት ይኖርብናል፡፡ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሀገር በቀል እቀውቀቶች ከዘመናዊው እውቀቶች ጋር በመሆን የሚዳብሩበት ተቋም እንደመሆናቸው መጠን ኮሌጆች እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤቶች በጋራ በመስራት የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ በማድረግ ወጣቶቻችን ከዚህ ትሩፋት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን በማስቀጠልም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚቀበሏቸው ሰልጣኞች በከተማና በገጠር ቀበሌዎች ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደመሆኑ መጠን የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን ተመራጭ ከማድረግ አንጻር በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡በጋራ ስንሰራ ደግሞ ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስልጠና ወስደው የሚጨርሱ ሰልጣኞች ለራሳቸው ብሎም ለሀገራችን መጥቀም የሚችሉ ትውልዶችን ማፍራት አንችላለን፡፡ በቀጣይ ደግሞ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አዳዲስ አሰራሮችን በመንደፍ እያመረቱ የሚያሰለጥኑ እያሰለጠኑ የሚያመርቱ ኮሌጆች እንደመሆናችን መጠን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚታዩ የግብአት ችግሮችን ለመፍታት በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ የጋራ ቤታችሁ ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ፡፡ኮሌጃችን ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር ለማስተሳሰር ስራዎችን በመቀመር ወደ ስራ ገብተናል፡፡ስለሆነም ዛሬ የምናደርገው የምክክር ተግባር በጋራ በመስራት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ላይ የሚስተዋለውን የሰልጣኞች መጠነ ምዝገባ ለመጨመር የሚያስችለን የምክክር መድረክ ነው ብለዋል፡፡ በማስቀጠልም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በክህሎትና በአመለካከት ሰልጣኞችን በማዳበር ኢንዱስትሪውን ማንቀሳቀስ የሚችሉ ባለሞያዎችን ማፍራት ይኖርብናል ለዚህም እንደ ግብአት ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ማግኘት ይኖርብናል ስለሆነም መልካም መደላድሎችን በመፍጠር ለተማሪዎቹ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምዝገባ ስራን መስራት የሚችል ቴክኖሎጂን በማበልጸግ ወደ ስራ አስገብተናል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ተመራጭ አድርገው ትምህርትና ስልጠናቸውን እንዲወስዱ በማድረግ ረገድ በጋራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ኃላፊ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የቢሮው ዳይሬክተሮች ፣የኮሌጁ ኃላፊዎች፣ የEASTRIP ፕሮጀክት ባለሞያዎች፣የአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ዳይሬክተሮችና ም/ዳይሬክተሮች ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የSIFA ፕሮጀክት ተጠቃሚ አፍሪካ ሀገራት አጠቃላይ ቡድን መሪ የሆኑት M/R ካርተን አስሌት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የተውጣጡ የSIFA ተወካዮችና የስራ ሀላፊዎች በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ ውይይት ተካሄደ፡፡
በግምገማና ውይይት ሂደቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንዳብራሩት እንኳን ወደ በረሀዋ ንግስትና የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ ይህ በጀርምን መንግስት ድጋፍ የሚተገበረው የSIFA ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን ደግሞ ዲጂታል አሰራሮች የሚያሳድግ ፕሮጀክት እንደሆነ እተማመናለሁ፡፡ በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የSIFA ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር ፕጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ በመመደብ ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በማስቀጠል ንግግር ያደረጉት ደግሞ የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ወደ ሆነው ኮሌጅና የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ይህ በጀርምን መንግስትና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ የሚተገበረው የSIFA ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ነው ፡፡ ወጣቶቻችንም የሙያና የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት ነው፡፡ ፕጀክቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደ ተግባር ሲገባ ደግሞ ከኢትየጵያ አልፎ ለምስራቅ አፍሪካ የሚጠቅም ስራዎችን መስራት የሚያስችለን ነው፡፡ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር እንዲሁም የኮሌጁ ማኔጅመንት ቁርጠኛ ሆኖ እንደሚሰራ እና ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ እንዲሁም ለሚያጋጥሙ ችግሮች ሁሉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በግምገማና ውይይቱ ሂደቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እስካሁን የሰራቸው ስራዎች እንዲሁም ከስልጠና ጋር የተገኛኙ ጉዳዮች በኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ት/ት ስልጠና ኃላፊ አቶ ሳለሃዲን አብዱልሃሚድ የቀረበ ሲሆን ፣ ኮሌጁ ከቴክኖሎጂ ማፍለቅና ለተጠቃሚዎች በማስተላለፍ ጉዳይ ላይ ደግሞ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ቀርቧል፡፡ እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በእቃ በግዢ ሂደቱ እና በአቅም ግንባታ እንዲሁም በህንጻ ግንባታው ሂደት ከSIFA ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እንዲሁም ከዋናው የ SIFA ፕሮጀክት ጽ/ቤት የመጣው ልኡክ ቡድን ከኮሌጁ አመራሮች እና ከፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ዩኒት ጋር ውይይት ከተደረገ በኃላ በቀጣይ የእቃ ግዚው፣የመምህራን የአቅም ግንባታውና የልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ ለማስጀመር ከስምምነት ላይ በመድረስ የግምገማ ሂደቱ ተጠናቋል፡፡
የ SIFA ፕሮጀክት በኢትዮጵያ በሚገኙ ሁለት ኮሌጆች የሚተገበር ሲሆን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የICT የልህቀት ማእከል እንዲሁም በሚዛን ቴፒ ኮሌጅ ደግሞ የግብርና የልህቀት ማእከልነት የሚተገበር ፕሮጀክት ነው፡፡ፕሮጀክቱ በዋናነት የእቃ ግዢ፣የመምህራን የአቅም ግንባታ እንዲሁም የህንጻ ግንባታን ያካትታል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 23/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ለግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችና ለአገልግሎት ተጠቃሚ ድርጅቶች አዲስ ተሸሽሎ የወጣውን አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አዋጁን መሰረት በማድረግ በወጣው መመሪያ ቁጥር 45/2013 ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ፤
በዋናነት ስልጠናው እንዲዘጋጅ የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ሕግና አሠራርን በመከተል ፍትሃዊ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የሥራ ስምሪት አገልግሎት በሀገር ውስጥ የሚሰጡበትን ሁኔታ መወሰን በማስፈለጉ፤ በኤጀንሲ አማካኝነት ለሥራ የተሰማራውን ሠራተኛ መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ኤጀንሲው እና የአገልግሎት ተጠቃሚው ድርጅት ሊኖራቸው የሚገባውን የጋራና የተናጠል ኃላፊነት ለይቶ የማመልከቱ ተገቢነት ስለታመነበት ነው፤
በተጨማሪም መንግሥት በሀገር ውስጥ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሚሰጠውን የሥራ ስምሪት አገልግሎት በብቃትና በተገቢው በመከታተል፣ በመቆጣጠርና በመደገፍ፣ በሥራ ላይ የሚሠማሩ ሠራተኞች መብት፣ ደህንነትና ጥቅም የሚጠበቅበትን ሁኔታ መፍጠር እና የኢንዱስትሪ ሠላምን ማስፈን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ በመንግሥት እና በግሉ ዘርፍ የሚሰጡ የሥራ ስምሪት አገልግሎቶች በተቀናጀ አግባብ የሚፈጸሙበትን ሁኔታ በመፍጠር ለሀገሪቱ የሥራ ገበያ እድገትና ውጤታማነት ተገቢውን አስተዋጽኦ የሚያበረክት ይሆናል፤
በዚህም የስልጠና መድረክ ይህንን መመሪያ ኤጀንሲዎቹ እንዲረዱ በማድረግ በቀጣይ እንደከዚህ ቀደሙ ህገወጥ የሆኑትን ለመከታተልና ለመቆጣጠር የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት ህጋዊነትን የሚያበረታታ ስራ እንደሚሰራ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
" እያመረትን እናሰለጥናለን እያሰለጠንን እናመርታለን " በሚል አዲስ ዕሳቤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ስር የሚገኙ ሁለቱን የመንግስት ኮሌጆች ከስልጠና በተጨማሪ አምራችነታቸውን የሚያጠናክር የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በዛሬው ዕለት ተካሄደ።
" እያመረትን እናሰለጥናለን እያሰለጠንን እናመርታለን " ስንል ምን ማለታችን ነው?
ማሰልጠንና ማምረት ፣ማምረትና ማሰልጠን በአንድ ቦታ ማለትም በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆቻችን በተመሳሳይ ወቅት በማከናወን የማምረቻና የማሰልጠኛ መሣሪያዎች፣ አምራችና አሰልጣኝ ባለሙያ ፣ቦታና ጊዜ ተቀናጅተው የሚገኙበት ሲሆን በዚህም ቁሳዊና ሰብዓዊ ሃብቶችን በማቀናጀት እሴት በመጨመር ሃብት ማፍራት ምንም የሚባክን ጊዜና ሃብት እንዳይኖር በማድረግ ድርብ ኃላፊነትን በማቀናጀት ምርት በማምረት/አገልግሎት በማቅረብ ገቢ ማግኘት የሚያስችል ነው፡፡
በዚህም መርሃ ግብር ላይ የየድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፤ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የአስተዳደሩና የቢሮው ከፍተኛ አመራሮች፤ የኮሌጅ ዲኖች፤ አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የተገኙ ሲሆን ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
