uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 068
Підписники
+224 години
Немає даних7 днів
+230 день
Архів дописів
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው ዓመተ-ሒጂራ የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ታላቁ የረመዳን የፆም ወር በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ወቅት ነው፡፡ በዚህ የፆም ወቅት ሕዝበ-ሙስሊሙ ራሱን ከክፉ ነገሮች በመቆጠብና ፈጣሪውን በዱአ በመለመን ፣ እንዲሁም ያለው ከሌለው ወገኑ ጋር ተካፍሎ በመብላትና ሰደቃ በማድረግ መልካምነትን የሚያሳይበት ጊዜ ነው፡፡ በተለይም በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ ወንድምና እህቶች በፆሙ ወቅት በተለያዩ ሥፍራዎች በተካሄዱ የኢፍጣር ሥነ ሥርዓቶች ላይ በመሳተፍ ለሙስሊም እህት ወንድሞቹ ያለዉን አጋርነት በተግባር ያሳየ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡም እርስ በርስ የመደጋገፍ የኖረበት ባሕሉን በተጠናከረ መልክ ያስቀጠለበት እና የተቸገሩ ወገኖችንም በማገዝ በኩል ያሳየው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነበር። ቢሮው በዚሁ አጋጣሚ የተለያየ ድጋፍ የሚያደርግላቸውን ኢንተርፕራይዞች ከበዓላት ጋር በተያያዘ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ መጨመር እንዳይፈጠርና በሚኖሩ የበዓል ገበያዎች የሚያቀርቧቸውን ምርትና አገልግሎቶች በጥራት በማዘጋጀት ህብረተሰቡን ተደራሽ እንዲያደርጉ በቂ ግንዛቤ የፈጠረ መሆኑን ለማስታወስ እወዳለሁ። ይህንንም ሁሉ አቀፍ አድርገን በሌሎች ስራዎቻችን መልካም ዕሴቶቻችንን ጠብቀን በጎነትን እንድናሳይ ጥሪዬን እያቀረብኩ በ2017 ዓ.ም የሚከበረው የኢድ-አልፈጥር በዓል የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በዓል  እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ መልካም በዓል! ኢድ ሙባረክ!             የድሬዳዋ አስተዳደር           ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ               አቶ ሮቤል ጌታቸው

photo content
+1

የክህሎት ኢትዮጵያ 1ኛ ዙር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን በመወከል የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያና ከሰል ማሽን የሰሩ፡፡ ይህ ማሽን semiautomate charcoal and animal feed production machine ይባላል። ማሽኑ ፕሮሶፊስ ጁሊ ፍሎራ እየተባለ የሚጠራውና በአፋርና በሶማሌ ክልሎች የሚገኘውን አረም ለመቀነስ የተሰራ ነው። አረሙ የሚታረስ መሬትን በመሻማት የሚታወቅ እና ከፍተኛ የከርሰ ምድር ውሃን የሚመጥ በመሆኑ አረሙን ለማጥፋት በማሰብ የተሰራ ነው። በዚህም ግንዱን ወደ ከሰልነት ፍሬውን ደግሞ ከሌሎች ሰብሎች ጋር በመቀላቀል ለእንስሳት መኖነት ለመቀየር የሚያስችል ማሽን ነው። ማሽኑ ለየት የሚያደርገው ኤሌክትሪክ ካርበናይዘር የተባለው ክፍሉ ጭስ አልባ መሆኑ ነው። ማሽኑ 16 ሰዓት መስራት ይችላል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች የኢፍጣር መርሀ-ግብር አካሄዱ፤      መርሃ-ግብሩ በተለይም የቢሮው እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችን አብሮነት እና አንድነት በመፍጠርና በማጠናከሩ ረገድ ሚናው ላቅ ያለ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረው የዛሬውን የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።     በዚህ የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላይ የቢሮው አመራሮች፣ የኮሌጆች ዲኖች እንዲሁም የአንድ ማዕከላት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

photo content
+9

ከሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ገበያ እና ግብይትን በተመለከተ በንድፈ ሃሳብና በተግባር አቅማቸውን እንዲገነቡ የሚያስችል መድረክ ተዘጋጀ፤ በዚህም ሞዴል ኢንተርፕራይዞቹ የሚፈጠርላቸውን የገበያ እድሎች እንዴት እንደሚጠቀሙ በተለይም ከተቋማትና ከደንበኞቻቸው ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነት በሚያሻሽሉበትና በሚያሳድጉበት አግባብ ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል፡፡ በተያያዘ በቀጣይ ለሚዘጋጀው ባዛር ያላቸውን አገልግሎትና ምርት ለህብረተሰቡ በማቅረብ እራሳቸውን የሚያስተዋውቁበትና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት እንዲሆን ለዚህም በቂ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከላት ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ አሳስበዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

በአስተዳደሩ የገጠር አራቱም ወረዳዎች ስር የሚገኙና በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ ምልከታና ልየታ ቀጥሎ በአሰሊሶ ወረዳ ተካሄደ። በዛሬው ዕለትም በአሰሊሶ ወረዳ የተለዩ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምልከታ የተደረገ ሲሆን ቀሪ የአስተዳደሩ ገጠር ወረዳዎች ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች በተመሳሳይ ምልከታ እና ልየታ የሚደረግ ሲሆን ከዚህ በፊት ይነሳ የነበረውን የተደራሽነት ጥያቄዎች ለመመለስ የቢሮው አቅጣጫ አካል መሆኑም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም አስታውቀዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ በክህሎት የዳበረ ዜጋ የማፍራት ተገባርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ:: የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሳይንስ ትምህርቶችና ፈጠራ ላይ ዝንባሌ ያላቸው የ STEM ክበብ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ጉብኝት በኮሌጁ አካሄዱ:: ኮሌጁ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ የፈጠረውን ግንዛቤ በተጠናከረ መልኩ ውጤታማ ለማድረግ በት/ቤቶች ላይ የቴክኒክና ሙያ ክበብ እንዲቋቋም የተደረገ ሲሆን በዚህም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎች የቴክኒክና ሙያ ክበቡን እንዲቀላቀሉ ማድረግ መቻሉም ተገልፇል:: ለተማሪዎቹ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልእክታቸውም በቅድሚያ በቀጣይ የክህሎት ባለቤት ወደ ምትሆኑበት ኮሌጃችሁ እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ኮሌጁ ት/ቤቶች ላይ በስፋት ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውሰው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ የሚንቀሳቀሱ ተማሪዎችን በዘላቂነት በክህሎት ለማብቃት ታሳቢ በማድረግ ይህን የቴክኒክና ሙያ ክበብ በየት/ቤቶች እንዲቋቋም አድርገናልያሉ ሲሆን ተማሪዎች በቀጣይም በኮሌጁ የሚኖራችሁን ቆይታ በምትፈልጉት ሙያ መስክ ራሳችሁን ለማብቃት ልትጠቀሙበት ይገባልም ብለዋል:: ተማሪዎች ኮሌጁ ያለውን የማሰልጠን አቅም ተዘዋውረው ከጎበኙ በኃላም በቀጣይ ለክበብ አባላቱ የህይወት ክህሎትና STEMን መሰረት የደረጉ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም የSTEM አባላቱ ከመደበኛ ትምህታቸው ጎን ለጎን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጠርላቸዋልም ብለዋል:: በተጨማሪም ተማሪዎቹ በኮሌጁ ቆይታቸው የጥናት፣ ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ አስተባባሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት ስለ STEM power ፅንሰ ሀሳብ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን በተጨማሪም በክፍሉ አስተባባሪነት በኮሌጁ የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተማሪዎቹ እስጎብኝተዋል:: የSTEM ክበብ አባላት በተቋሙ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በየዲፖርትመንቶቹ ስለሚገኙ የሙያ ስልጠናዎች በተመለከተም በአሰልጣኝ መምህራ ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: በቀጥይ የቴክኒክንይ ሙያ STEM ክበብ አባላት በኮሌጁ በሚዘጋጅላቸ የሙያ ስልጠናዎችን የሚወስዱ ሲሆን ይህም የ2ኛ ደረጃ ትምህታቸውን ከማጠናቀቃቸው አስቀድሞ ቢያንስ የአንድ ሙያ ባለቤት እንዲሆኑም የሚያስችላቸው እንደሚሆን ተግልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 19/2017 ዓ.ም

#ዜና| በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ግንባታ ሂደት ተጠናቆ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ፣ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተውጣጣ የSupervision team የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም ገመገሙ፡፡ በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የ EASTRIP ፕሮጀክት መሳካት በከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በኮሌጁ ማኔጅመንት ትልቅ ድጋፍና ክትትል እየተደረገበት አሁን ላለበት ደረጃ ደርሷል፡፡ ያሉት ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የግንባታውን ሂደት ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም ይህ የልህቀት ማእከል ግንባታው እንዲጠናቀቅና ለታለመለት አላማ መዋል እንዲችል አስተዋጽኦ ላበረከቱት ለከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮ፣ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት፣ለ EASTRIP ፕሮጀክት ሰራተኞች እንዲሁም ለኮሌጁ ሰራተኞች ከልብ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ ከሪፖርቱና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን ፕሮጀክቱ ውጤታማ የሆነ ደረጃ ላይ መድረሱን ያረጋገጡ ሲሆን በቀጣይ ወር በሃገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እንዲመረቅ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና|ድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ ፖሊ
+7
#ዜና|ድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፖሊስ አባላት በመሰረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ላይ ትኩረቱን አድርጎ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ፡፡ ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በትምህርትና ስልጠና ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ እየሰራን እንገኛለን ያሉት የኮሌጁ ም/ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ በሆኑት በአቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ሲሆን የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድግ የሚችሉ ከ42 በላይ የአጫጭር ስልጠናዎችን እንዲሁም ከ12 በላይ ትምህርት ክፍሎች የተለያዩ የሞያ ትምህርቶችን አዘጋጅቶ ስልጠናዎችን በመስጠት የስራ ባለቤት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ይህ በዛሬው እለት የተጠናቀቀው የ2ተኛ ዙር ስልጠናም በተለያዩ ዙሮች የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑት የፖሊስ አባላትም በስልጠናው ያገኙትን ችሎታ በስራ ቦታቸው ላይ ተግባራዊ እንደሚያደርጉትና በቀጣይም በኮሌጁ በሚሰጡ የተለያዩ ሞያዎችን እንደሚሰለጥኑ ተናግረዋል፡፡ስልጠናውም ላመቻቹት ለጠቅላይ መምሪያውና ለኮሌጁ እንዲሁም ስልጠናውን ለሰጧቸው መምህራን ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም በስልጠናው ላይ ተሳታፊ የሆኑት የፖሊስ አባላት በኮሌጁ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲሁም የተለያዩ ትምህርት ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በጉብኝቱ ላይም ስለኮሌጁ እንቅስቃሴ በICT ትምህርት ክፍል ተጠሪ አቶ ቴዎድሮስ አስፋው እና በሬጅስትራር ኃላፊ አቶ ፋሚ ኑረዲን ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የመጋቢት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራ ሃሳቦችን ወደ ተግባር በመቀየር በስፋት እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ ተገለ፡፡ በኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የሚመራ የኮሌጁ የቦርድ አባላት በተቋሙ የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችና ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በቦርድ አባላቱ የተጎበኙት የፈጠራ ውጤቶችና ፕሮጀክቶች በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ከፍተኛ ጥረትና በኮሌጁ ያልተቋረጠ ድጋፍ የተሰሩ ሲሆን የማህበረሰቡን ችግር በከፍተኛ ደረጃ እንደሚፈቱ ታምኖባቸው የተሰሩ እንደሆነም ተገልፇል:: በኮሌጁ ችግር ፈቺ ተብለው ከተሰሩ የፈጠራ ስራዎችና ፕሮጀክቶች መካከልም...... 1.በአንድ በሬ ማረስ የሚያስችል የእርሻ ማረሻ ፈጠራ፣ 2. የዘር ብክነትን የሚያስቀር ዘር መዝርያ ማሽን፣ 3. በአንድ ጊዜ 500 እቁላሎችን ማስፈልፈል የሚችል ማሽን፣ 4. እፅዋትን ጨምሮ ከተለያዩ ግብአቶች የተመረተ የነዳጅ ዘይት፣ 5. ዘመናዊ የመንገድ ዳር ቁሻሻ ማጠራቀሚያ፣ 6. ለኮሪደር ልማቱ ተጨማሪ ውበት የሚያጎናፅፍ ዘመናዊ አገልግሎት መስጫ ሼድ፣ 7. የመንገደኞች ማረፊያ አግዳሚ ወንበር... የሚገኙበት ሲሆን በቀጣይ በስፋት ተመርተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ እንደሚደረግም ተገልፇል:: ኮሌጁ የፈጠራ ሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከል እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች መፍለቂያ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ እንደሆነ ተመልክተናል ያሉት የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ አክለውም በቀጣይ የተጀመሩ ስራዎችን በፍጥነትና በጥራት በማከናወን የማህበረሰቡን ችግር በዘላቂነት ከመፍታት በተጨማሪ ተቋሙም የራሱን ገቢ ማሳደግ ያስችለዋልም ብለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 19/2017 ዓ.ም