cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ETHIO SPORT ሙሌ ስፖርት በየሰኮንዶች

✅ ሙሌ ስፖርት በየሰኮንዶች እሚወጡ ስፖርታ መረጃዎች ከእሁድ እስከ እሁድ ያገኙበታል ____________________________ ➠| የሃገር ቤት መረጃዎች ➠| የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች መረጃ ➠| ቀጥታ ስርጭቶች ➠| የዝውውር ዜናዎች 👉 | ለማስታወቂያ ስራ ☞ @Mulusporta 👉 | ስልክ ቁጥር +251925410302

Більше
Рекламні дописи
387
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Фото недоступне
አፄዎቹ ድል ቀንቷቸዋል ! √ የ 2015 ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር የመጀመሪያ ሳምንት መርሀ ግብር የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ እየተካሄዱ ሲሆን ፋሲል ከነማ ከ አዳማ ከተማ በባህር ዳር ስታዲየም ተጫውተዋል። √ ፋሲል ከነማ አዳማ ከተማን 2 ለ 1 በማሸነፍ ሶስት ነጥቦችን አሳክተዋል። √ የፋሲል ከነማን ሁለቱንም ጎሎች ፍቃዱ አለሙ ሲያስቆጥር አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገች ጎል አሜ መሀመድ አስቆጥሯል። √ በጨዋታው ላይ በአዳማ ከተማ በኩል ዊሊያም ሰለሞን በፋሲል ከነማ ደሞ ሽመክት ጉግሳ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል። √ አፄዎቹ በሁለተኛ ሳምንት መርሀ ግብር ከ ወላይታ ድቻ ጋር ሲጫወቱ አዳማ ከተማ ደሞ ከመቻል ጋር ይጫወታሉ። @Teme_Ayu @MULESPORT
Показати все...
Фото недоступне
ፊል ፎደን በአዲስ ኮንትራት ! እንግሊዛዊዉ የማንችስተር ሲቲ ኮከብ ፊል ፎደን ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ሊፈራረም ተቃርቧል። እንደ ዴቪድ ኦሬንስታይን ዘገባ ማንችስተር ሲቲ ከረጅም ጊዜ ድርድር በኋላ በዚህ ሳምንት ከ ፎደን ጋር አዲስ ኮንትራት እንደሚፈራረሙ ገልጿል። ለክለቡ ባለው ፋላጎት የተነሳ እንግሊዛዊው አጥቂ ክለቡን ለመልቀቅ ፈልጎ አያውቅም ነገርግን በአመራር ለውጥ ምክንያት ንግሮች እንዲዘገዩ ምክንያት ሆነዋል። ስምምነቱ አሁን ላይ ለመጠናቀቅ ተቃርቧል ክለቡ የ22 አመቱን ወጣት አዲስ ውል የመጨረሻ ዝርዝሮች አጠናቀዋል። ፎደን እስከ 2027 ድረስ በኢትሃድ የሚያቆየውን አዲስ ውል ይፈርማል ተብሎ ይጠበቃል። SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
  • Фото недоступне
  • Фото недоступне
  • Фото недоступне
እማታቁት ግብና ጉድ እዩ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/habeshabetting11 https://t.me/habeshabetting11 https://t.me/habeshabetting11 https://t.me/habeshabetting11
Показати все...
Фото недоступне
ካሉም ዊልሰን ውሉን አራዝሟል ! ካልም ዊልሰን ከኒውካስል ጋር ያለውን ውል ለተጨማራ ሁለት አመታት አራዝሟል። የአጥቂው አዲስ የሁለት አመት ውል በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ ተመስርቶ ከዛ በላይ የመራዘም አማራጭም ይዟል። ዊልሰን በዚህ ሲዝን በአራት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ሶስት ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን በክለቡ ባሳለፈባቸው በሁለቱም አመታት የክለቡ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪያቸው ሆኗል። በክለቡ ባደረጋቸው 48 የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች 23 ግቦችን አስቆጥሮ አምስት አሲስት ማድረግ ችሏል። SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
Фото недоступне
"ከተቀናቃኞቻችን ጋር መጫወት ያስደስተናል" የማንችስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ማንቸስተር ዩናይትድን 6-3 ካሸነፉ በኋላ ለጋዜጠኞች እንዲህ ብሏል፦ "የመጀመሪያው አጋማሽ በጣም ጥሩ ነበር። አራት ጎሎችን አስቆጥረናል ግን ብዙ ማስቆጠር እንችል ነበር። በሁለተኛው አጋማሽ ጠንከር ያለ ስራ ነበረን።" "ታላቅ ድል እና ታላቅ ግጥሚያ ነበር። በስታዲየም ውስጥ ያሉት ሁሉ ተደስተው ነበር እና ከተቀናቃኞቻችን ጋር መጫወት ያስደስተናል። ለእኛ ጥሩ ከሰአት ነበር።" "በአጠቃላይ የእኛ የማጥቃት ደረጃ በጣም ጥሩ ነበር ነገር ግን በተፈጥሮው ብሩኖ ፈርናንዴዝ እና ክርስቲያን ኤሪክሰን ያለው ተጋጣሚ ጥራት ያለው ቡድን ነው። ቦታ ቦታዎችን እናውቀዋለን እና የፊት መስመር ተጫዋቾቻችን በመጀመሪያው አጋማሽ ልዩነት መፍጠር ችለዋል።" "እኛ ጥሩ አድርገናል; የተሻልን መሆን እንችላለን። በጣም ብዙ ተጫዋቾች የተሳሳቱ ቅብብሎች ነበሯቸው ይህም ጥሩ አይደለም። የበለጠ ወጥ መሆን አለብን። በአንዳንድ አካባቢዎች ጥሩ አልነበርንም።" ፊል ፎደን? "እሱ በእያንዳንዱ ግጥሚያ ላይ መጫወት ይገባዋል እና ጥራት አለው. እውነታው ግን ገና ወጣት ተጫዋች ነው።" ስለ ኤርሊንግ ሀላንድ? "እሱ የራሱ ቁጥሮች ለራሱ ይናገራሉ. እሱ አስቀድሞ እዚህ (ሃት ትሪክ) ሰርቶ ነበር። ሁልጊዜ እሱን ለመርዳት እንሞክራለን. እሱ ሁል ጊዜ በጣም የተጠማ እና ተወዳዳሪ ነው። ቁጥሮቹ በጣም አስፈሪ ነው።" SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
❓የየትኛው ክለብ ደጋፊ ናችሁ የክለባችሁን ቻናል በመምረጥ ተቀላቀሉ ❗️❗️
Показати все...
Фото недоступне
ለኮከቡ አቡበከር አድናቂዎች የተከፈተ ቻናል ጆይን ያድርጉ👇👌
Показати все...
Фото недоступне
ክሪስቶፈር ንኩንኩ ወደ ቼልሲ ! ክሪስቶፈር ንኩንኩ በ2023 ክረምት ወደ ቼልሲ ለመግባት ቅድመ ኮንትራት ፈርሟል። ቼልሲዎች ለዚህ የ24 አመቱ ተጫዋች ከ60 ሚሊየን ፓውንድ በላይ ለመክፈል ቃል ገብተዋል። (ምንጭ David Orenstein) SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
Фото недоступне
🇪🇹 የመጀመሪያ ሳምንት ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ                ⏰ 24'   ፋሲል ከነማ 1-1 አዳማ ከተማ ፍቃዱ አለሙ 8'⚽️ አሜ መሐመድ 14'⚽️ SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
Фото недоступне
"በወደፊቱ ህይወቴ የሚታየኝ ሪያል ማድሪድ ነው" የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቴ ከክለቡ የወደፊት ቆይታ ጋር በተያያዘ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንዲህ ብለዋል፦ "በእኔ በወደፊቱ ህይወቴ የሚታየኝ ሪያል ማድሪድ ነው. በዚህ የውድድር ዘመን እና በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ሪያል ማድሪድ. ከዚያም እንደገና ሪያል ማድሪድ እና አንድ ጊዜ ሪያል ማድሪድ! ከዚያ ሚፈጠረውን እናያለን "ሲል አንቾሎቲ ተናግሯል። SHARE"  @MULESPORT
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.