Mezmur mesikel
198
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
፳፱_ሆሣዕና_መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp37.99 MB
፴.ሕማማት (መጋቤ ስብሐት አለሙ አጋ).mp310.69 MB
፴፩_ከቶ_አይቀርም_ሞቱመጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp37.26 MB
፴፪_ሞቱ_አይቀርም_መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp31.72 MB
፴፫_ዕፁብ_ድንቅ_እንጂ_ነውመጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp35.80 MB
፴፬_ዳግም_ምጽአት_ቁ_፩_መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp35.77 MB
1310
#መጻጒዕ
ሰው የለኝም ያለ በሰው የተረሳ
የዳነው መጻጒዕ ያዳነውን እረሳ
በአምስቱ እርከኖች በአዕማደ ሚስጥራት
ቤተ ሳይዳ ላለች ከመቅደስ ላኖርካት
በበደል ለምናዝን ምሕረትን ፍለጋ
በንሰሐ ማረፍ ካራተ ዝንጋኤ ከኃጢአት አልጋ
አዝ.....................
በጠበሉ ደጃፍ ለጸኑት የሚላክ
ለቀድሶተ ማይ የሚወርደው መላአክ
በመንገድ ጠብቆ ሞትን የሚያሳልፍ
ዛሬም ይድረስልን ቀድመው ከገቡት ጋር ነፍሳችን እንድታርፍ
አዝ.....................
አልጋው ተሸክሞት ደክሞ ለሚጨነቅ
አልጋን አሸክመህ ሕመም የምታርቅ
ደዌያችንን ነስተህ ቆስለህ የምትፈውስ
የመጻጒዕ ረዳት የነፍሳት መጠጊያ መድኃኒት ክርስቶስ
አዝ.....................
የባሰ እንዳያየው ቃሉን ያልጠበቀ
እጁን ሰዶ ጸፍቶ ከደዌው ታረቀ
ሰንበት የሻረ ከሚሉት እንዳንውል
ለትንሣኤው ደስታ የሰንበትን ጌታ አርብ እንከተል
መጻጉዕ_ዘማሪ_ዲያቆን_ቀዳሜጸጋ_ዮሐንስ.mp34.09 MB
3000
ጌታ ሆይ
ጌታ ሆይ አይሁድ ዓማፅያን ሰቀሉህ ወይ
የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ወይ(፪)
የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመገደል
የሔዋን ስሕተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት (፪)
ንጹህ ክርስቶስ ሆንክ በደለኛ ብለህ ስለኛ
መስቀል አሸክመው አሥረው ገረፉህ እያዳፉህ (፪)
እጅና እግርህ በብረት ተመታ የዓለም ጌታ
የሾህ አክሊል ደፍተህ ጎንህም ተወጋ አልፋ ኦሜጋ (፪)
ግብዞች እንደ ራሳቸው መስሏቸው
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጐዱ (፪)
በመስቀል ላይ ቃልን አሰምተህ ተጠማሁ ስትል
ሐሞት እና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው (፪)
ይቅር ባይ የሰዎችን በደል ሁሉን ሳታይ
አንተ ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ (፪)
👉✍️ @DA121922
https://t.me/Abalibanos333
ጌታ ሆይ አይሁድ አማፅያን.m4a1.19 MB
በጌቴ ሴማኒ.m4a8.73 KB
zemari tnsae fikadu.mp35.31 MB
2000
✝️ማረኝ መመኪያዬ✝️
ማረኝ ማረኝ ማረኝ መመኪያዬ
አርጅቻለሁ እኔ(በኃጥያት ጎስቁዬ )/2/
ከፊቴ ናትና ኃጥያቴ ሁል ጊዜ
ተውጫለሁ እኔስ(በሀዘን በትካዜ)/2/
በፊትህ ክፋትን አድርጌያለሁ እኔ
ምንም ጽድቅ አልሠራው(በሕይወት ዘመኔ)/2/
#አዝ=====
ከፊትህ መቅበዝበዝ መሠደድ ፈለኩኝ
ኃጥያት ከሁዋላዬ(እያሳደደችኝ)/2/
ወዴት አሄዳለው መሸሸጊያም የለኝ
ምህረት መጠጊያ(ዋሻ ካልሆነችኝ)/2/
#አዝ=====
ከፊቴ ናትና ኃጥያቴ ሁል ጊዜ
ተውጫለሁ እኔስ(በሃዘን በትካዜ)/2/
በፊትህ ክፋትን አድርጊያለሁ እኔ
ምንም ጽድቅ አልሠራው(በሕይወት ዘመኔ)/2/
#አዝ=====
የተሰባበረው አጥንቴ እንዲጠገን
በምህረት እና(በቸርነት ዳሠኝ)/2/
የቀና መንፈስን አድስ በልቤ ውስጥ
ነፍሴ በእሺታ(በደስታ ትለወጥ)/2/
#አዝ=====
ቅዱስ መንፈስህን ከኔ ላይ አትውሠድ
በንስሐ ድኜ(በተስፋ እንድላመድ)/2/
አቤቱ ንፁህ ልብ ፍጠርልኝና
በደስታ ልስከር(በፍቅርህ ልፅናና)/2/
@Abalibanos333
@Abalibanos333
@Abalibanos333
https://www.tiktij.com/@Abalibanos333
Yilma Hailu New Ethiopian Orthodox Mezmur 2015 Maregn.m4a9.71 KB
2610
Repost from ሄላንሳን
✍ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ✍
👆
👉የመጀመሪያው ሳምንት👈
ውድ ቤተሰቦቻችን እንደምን አላችሁ? እንደምንስ ለዛሬዋ ቀን ደረሳችሁ? አሜን በእኛ በደካሞቹ ላይ ኃይሉን የሚገልጥ ጥበቡን የሚያስተምር የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ የእኛም አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ለስም አጠራሩ ክብር ምሥጋና ይግባው። @helansane
የመጀመሪያው ጾም ምንቀበልበት ሰንበት ወይም ቅበላ የተባለው እሑድ ዘወረደ ወይም ሙሴኒ እንደሚባል ቅዱሳት መጽሐፍቶች ይናገራሉ።በዚህ ሳምንት በመዋዕለ ጾሙ ጠቅላላ የሚዘመረው የጾመ ድጓው መጀመሪያ "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ"ይህም ማለት ከላይ የወረደውን(አምላክ) አይሁድ ሰቀሉት በማለት በዚህ ሳምንት ይዜማል።በውስጡም የኢየሱስ ክርስቶስን የዕርገቱን የስቅለቱን የአዳኝነቱን መታሰቢያ የያዘ ነው።ዮሐ 1፥9-11 3፥13-21
? ዳግመኛም ይህ ሳምንት ሙሴኒ በመባል ይታወቃል።
የዚህም ምክንያት በዚህ ሳምንት መጀመሪያ የሰኞ ዕዝል ላይ ""ከመዝ ይቤ ሙሴ ፀዓቱ እምትእይንት"" ሙሴ ከከተማ መውጣቱ እንደዚህ ነው አለ ስለሚል አንድም "ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት ምድር ሰናይት" እያለ የሙሴን ታሪክ ስለሚያነሳ ሳምንቱ ሙሴኒ ተባለ። እነ ሙሴና ሌሎችም ነብያት አርባ አርባ ቀን ጾመው ከአለፋ በኃላ የሙሴ ሕግና ትንቢተ ነብያት ፈጻሚ የሆነው አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ እነሱ 40 ቀንና 40 ሌሊት መጾሙን የሚያስታውስ ነው።(ዘጸ 24፥18 1ኛ ነገ 19፥8 ማቴ 4፥1-4) ። በመጨረሻም በሳምንቱ ውስጥ በቅዳሴ ላይ የሚነበቡ የቅዱስ መጽሐፋችን ክፍሎች እና አስተምዕሮ በጥቂቱ ልናስቃኛችሁ ወደድን
👉በገባሬ ሰናዩ ዲያቆን ዕብ 13፥7-17 "የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሉዋቸው።" እያለ እስከ ፍፃሜው ያነባል። ለዋኖቻችሁ ታዘዙና ተገዙ።
👉በንፍቅ ዲያቆን ደግሞ ያዕ 4፥6-17 "ስለዚህ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል።እናንተ ኃጢአተኞ እጆቻችሁን አንሱ ሁለት ሃሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም ሳቃችሁ ወደ ኃዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ። በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኃል። ይህም የመጽሕፍ ቅዱስ ክፍልም እስከ ፍጻሜው ይነበባል።
🙏 በገባሬ ሰናዩ ዲያቆን መዝ 2፥11
ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት
ወተሐሰዩ ሎቱ በረዓድ
አንዕዋ ለጥበብ ከመ አይትመዐዕ እግዚአብሔር
ይህም ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ
በረዓድም ደስ ይበላችሁ።
ተግሣጹን ተቀበሉ ጌታ እንዳይቆጣ
@helansane
ውድ ቤተሰቦቻን ሳምንቱን የፍቅር የሰላም የጤና እንዲሁም የመተሳሰብ ያደርግልን ዘንድ በጸሎት እንትጋ። ቸር ያገናኘን።
2000
Repost from ዩቶጵያ UTOPIA
#ምድር_አበራች
ከመልአኩ ክብር የተነሳ ምድር አበራች
አበራች ፀጋውና ክብሩ ሆኗት የምስራች
ሃያል ሃያል ከመላእክት ክብሩ የገነነ
ሊረዳኝ የመጣው ቅዱስ ሚካኤል ነው
ሲደግፈኝ ክንዱ በዘመኔ
ምልጃው ሲጠብቀኝ እያለፈ ቀኔ
እየመራኝ በብርሃኑ ፋና
ሚካኤል መንገዴን አቀና
ዐይኑ ዘርግብ ዐይኑ
ኦ ሚካኤል ታየ በብርሃኑ
ሲማልድ ሲማጸን በፊቱ
እግዚአብሔር አየን በምህረቱ
ከመልአኩ ክብር የተነሳ ምድር አበራች
አበራች ፀጋውና ክብሩ ሆኗት የምስራች
ሃያል ሃያል ከመላእክት ክብሩ የገነነ
ሊረዳኝ የመጣው ቅዱስ ሚካኤል ነው
እያጽናናኝ ፍጹም ከድካሜ
ስጠራው ተፈወስኩ ዳንኩኝ ከህመሜ
ሊመግበኝ ለተራብኩት መና
ደረሰልኝ ሚካኤል ገናና
ዐይኑ ዘርግብ ዐይኑ
ኦ ሚካኤል ታየ በብርሃኑ
ሲማልድ ሲማጸን በፊቱ
እግዚአብሔር አየን በምህረቱ
ከመልአኩ ክብር የተነሳ ምድር አበራች
አበራች ፀጋውና ክብሩ ሆኗት የምስራች
ሃያል ሃያል ከመላእክት ክብሩ የገነነ
ሊረዳኝ የመጣው ቅዱስ ሚካኤል ነው
ያሻገረኝ መልአክ ሚካኤል ነው
በምልጃው ይደርሳል ቀርቦ ለለመነው
ለነፍሴ ከለላ ሆኖላት
አተረፈኝ ከዕደ ረበናት
ዐይኑ ዘርግብ ዐይኑ
ኦ ሚካኤል ታየ በብርሃኑ
ሲማልድ ሲማጸን በፊቱ
እግዚአብሔር አየን በምህረቱ
ከመልአኩ ክብር የተነሳ ምድር አበራች
አበራች ፀጋውና ክብሩ ሆኗት የምስራች
ሃያል ሃያል ከመላእክት ክብሩ የገነነ
ሊረዳኝ የመጣው ቅዱስ ሚካኤል ነው
ዘማሪ : ዲያቆን ኪሮስ ይኄይስ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 💚 @uto_pia1 💚 ✥
✥ 💛 @uto_pia1 💛 ✥
✥ ❤️ @uto_pia1 ❤️ ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╯
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
2000
✨በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!✨
ሳምንታዊ የኪነጥበብ መርሐግብር
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
አንድ ፓትርያርክ አንድ ሲኖዶስ
አንድ ሃይማኖት አንድ አርቶዶክስ
ጥምቀትን አክብረን በደስታ ቦርቀን
በደስታ ዘምረን በሐሴት ተሞልተን ስንል ሸር ብትን
ወዲያው በማግስቱ እኩይ መርዶ አረዱን
ደስታችን ቸልሰው ሐዘንን ሞሉብን
ትሕትና ቀረ ሰው እራሱን ሾመ
ሰይጣንን ደስ አለው ጠላት ተደመመ
በደላችን በዝቶ ከቁናው ፈሰሰ
ከራሳችን አልፎ ለጠላት ደረሰ
ለምድራዊ ስልጣን ቀኖና ተጣሰ
ሿሚ እና ተሿሚ ማንን ሊጠብቁ
ዶግማ ቀኖናዋን ሥርዓቷን ሳያውቁ
ፍቃደ እግዚአብሔርን በዕንባ ሳይጠይቁ
ማንን ለመምራት ነዉ ለሹመት የበቁ
ይገርማል ይደንቃል እጅግ ያስደምማል
ሰዉ ሰዉ ሆኖ እያለ እንዴት ይዋረዳል
ከፍ ብሎ እያለ እንዴት ውድቀት ይሻል
በሌለ ስልጣኑ ሹመትን ይሾማል
ሰነፍ እረኝነት መንጋውን የማያውቅ
በትጉህ እረኞች እሚስቅ እሚሳለቅ
ጠቦት ግልገሎችን በተኩላ 'ሚያስነጥቅ
ትሕትና የሌለው ጌታውን የሚያስንቅ
ከሕይወት መጽሐፍ ላይ ፍጹም እንዳይፋቅ
እግዚአብሔርን በዕንባ በጸሎት ይጠይቅ
በቅዱሳን ጸሎት ፍጹም እናምናለን
በእመ ብርሃን ምልጃ ፍጹም እናምናለን
በአንተ ፈራጅነት ፍጹም እናምናለን
እውነተኛ እረኛ አንተ ምረጥልን
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
✞አሜን✞
✨ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!! ✨
✞ ይቆየን ✞
4.34 KB
2510
Оберіть інший тариф
На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.