cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

🇪🇹አዲስ ዜና ኚምንጩ

አዲስ ሀገራቀፍና ዓለማቀፍ ዜናዎቜን ኚምንጩ እዚህ ያገኛሉ።

Більше
РеклаЌМі ЎПпОсО
369
ПіЎпОсМОкО
+124 гПЎОМО
+17 ЎМів
+630 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
ቩይንግ ኩባንያ ዚአፍሪካ ዋና ጜሕፈት ቀትን በአዲስ አበባ ሊኚፍት ነው ግዙፉ ዚአሜሪካ አውሮፕላን አምራቜ ኩባንያ ዹሆነው ቩይንግ ዚአፍሪካ ዋና ጜሕፈት ቀትን በአዲስ አበባ ሊኚፍት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግ እዚተካሄደ በሚገኘው ዚአፍሪካ ዚአቪዬሜን ጉባኀ ላይ እዚተካፈለቜ ትገኛለቜ። በመድሚኩ ላይ ኩባንያው በሚቀጥለው ዓመት ቢሮውን በአዲስ አበባ ለመክፈት ማቀዱ ተገልጿል፡፡ ኩባንያው ይህን ውሳኔ ያስታወቀው በአፍሪካ ኹግዙፍ አዹር መንገዶቜ መካኚል ተጠቃሜ ዹሆነው ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ 65 አውሮፕላኖቹን በቩይንግ እንደሚተካ ማስታወቁን ተኚትሎ ነው ተብሏል፡፡
ППказатО все...
ዚሃይማኖት ተቋማት ዚፋይናንስ ኊዲት ሪፖርታ቞ውን ለመንግሥት እንዲያቀርቡ ዹሚደነግግ ሹቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ ማንኛውም ዚሃይማኖት ተቋም ዚፋይናንስ ኊዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስ቎ር ማቅሚብ እንደሚኖርበት፣ ኹውጭ አገር ዚሚመጣ ዚገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ዹሚደነግግ ሹቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ፡፡ ‹‹ዚሃይማኖት ጉዳዮቜ አዋጅ›› ዹተሰኘውና ሪፖርተር ዹተመለኹተው ሹቂቅ አዋጅ፣ ዚሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው ዚሒሳብ አያያዝና ዚኊዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባ቞ው፣ ዚኊዲት ሪፖርታ቞ውንም ለሰላም ሚኒስ቎ር ማቀሚብ እንዳለባ቞ው ይደነግጋል፡፡ ዚሃይማኖት ተቋማቱ ዚሚጠቀሙት ዚሒሳብ አያያዝ ሥርዓት ዚገቢ፣ ዚወጪና አጠቃላይ ዚንብሚት ዝርዝር ዚያዘ መሆን እንደሚኖርበትና ዚገቢ አሰባሰብና ዚወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማኹናወን እንዳለባ቞ው ያስሚዳል፡፡ አንድ ዚሃይማኖት ተቋም በራሱ ዚገቢ ማስገኛ ሥራዎቜን በሚያኚናውንበት ጊዜ፣ ለዚሁ ሥራ ዹተለዹ ዚባንክ ሒሳብ መክፈትና ዹተለዹ መዝገብ መያዝ እንዳለበት ደንግጓል፡፡ በተጚማሪም ማንኛውም ዚሃይማኖት ተቋም ኹውጭ አገር ዚሚላክለትን ዚገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጊታ ወይም ሌሎቜ ዚገንዘብ ድጋፎቜን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት አስቀምጧል፡፡ ሲያሳውቅም ዚለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስምና አድራሻ፣ ዹተለገሰው ዚገንዘብ፣ ስጊታ ዓይነትና መጠን፣ እንዲሁም ስጊታው ወይም ድጋፉ ዚተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት እንዳለበት ተገልጿል፡፡ ማንነታ቞ው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት አባል ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ዚሃይማኖት ተቋማቱ ኊዲት ሪፖርታ቞ውን ለሰላም ሚኒስ቎ር ያቅርቡ ዹሚለው ዹሹቂቁ ክፍል ላይ ተቃውሞ ዚላ቞ውም፡፡ ኹውጭ ዹሚላክን ገንዘብ አስመልክቶ በሹቂቁ ላይ ዹተቀመጠው ገንዘቡን ማሳወቅ ኹሆነም ቜግር እንደሌለው ተናግሚዋል፡፡ ነገር ግን ኚፋይናንስ ደኅንነት ወይም ኹሌላ ዚደኅንነት መሥሪያ ቀት ጋር ዚሚያገናኝ ኹሆነ ጣልቃ መግቢያ በር እንዳይሆን ሥጋት እንዳላ቞ው ጠቁመዋል፡፡ ማንኛውም ዚሃይማኖት ተቋም ዚበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በሊስት ወራት ውስጥ ዚፋይናንስ እንቅስቃሎውን በገለልተኛ ኊዲተር ማስመርመር እንዳለበትና ዚኊዲተሩን አቋምና ዚውሳኔ ሐሳብ መያዝ እንዳለበት በሹቂቁ ተመላክቷል፡፡ ዹሰላም ሚኒስ቎ር ዹደሹሰውን ዚኊዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድሚግ እንዳለበትም ተደንግጓል፡፡ ዚአምልኮ ወይም ዚመቃብር ቊታ አሰጣጥን በተመለኹተም ለሃይማኖት ተቋማቱ ዚመሬት አቅርቊት በመሬት አጠቃቀምና ዹሊዝ ሕጎቜ መሠሚት እንደሚወሰን ተገልጿል፡፡ ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቊታ በተጠዚቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ ዓላማ ዹተሰጠ ቊታ አለመኖሩ ወይም ተጚማሪ ቊታ መስጠት አስፈላጊ መሆኑ መሚጋገጥ እንዳለበት፣ እንዲሁም በተለያዩ ቀተ እምነቶቜ መካኚል ዹሚኖሹው ርቀት ቢያንስ 500 ሜትር መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ትምህርትና ዚሃይማኖት ተግባራትን በሚመለኚትም በሹቂቁ ላይ ዝርዝር ጉዳዮቜ ተቀምጠዋል፡፡ ኚእነዚህም ውስጥ መደበኛ ትምህርት በሚሰጡ ዚመንግሥት ወይም ዹግል ተቋማት ዹሚሰጠው ትምህርት ሃይማኖታዊ ይዘት ዹሌለው መሆን እንደሚኖርበት አንዱ ሲሆን፣ በትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ሃይማኖታዊ ትምህርትን ማስተማር ወይም በቡድን ማምለክ ዹተኹለኹለ ነው ዹሚለው ሌላኛው ነው፡፡ በተጚማሪም ማንነትን ለመለዚት ዚሚያስቜሉ ሃይማኖታዊ አለባበሶቜን ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደማይገባ ተደንግጓል፡፡ ይህን ዹሹቂቁን ክፍል አስመልክቶ ዚእስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት ሃይማኖታዊ ምልክቶቜን እንደ ቀተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶቜ ልዩ ሁኔታዎቜ እንደሚኖሩ መደንገግ ሲገባው፣ ሙሉ ለሙሉ ኚትምህርትና ሥራ ገበታ ዚሚያስገድዱ ድንጋጌዎቜን መያዙ አግባብ አለመሆኑን በመግለጜ ለሰላም ሚኒስ቎ር በላኹው አስተያዚት፣ ቅሬታና ዚመፍትሔ ሐሳብ መግለጹ ይታወሳል፡፡ በሌላ በኩል ዚመንግሥት ኃላፊዎቜ መንግሥትን ወክለው በሃይማኖት በዓላት አኚባበር ላይ መገኘት እንደማይቜሉ በሹቂቁ ተመልክቷል፡፡ በተጚማሪም በትምህርት ቀት፣ በመኖሪያ ቀትና በሕክምና ማዕኚላት አካባቢ ዹሚደሹግ አምልኮ በአካባቢ ጥበቃ ሕግ ዹተቀመጠውን ዚድምፅ መጠን ያኚበሚ መሆን እንደሚኖርበት፣ ካልተፈቀደ በስተቀር ማስተማርን ጚምሮ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሕዝብ መሰብሰቢያ ቊታዎቜ መፈጾም እንደማይቜል ሹቂቁ ይደነግጋል፡፡ ዹወንጌል አማኞቜ አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በበኩሉ ይህ ዹሹቂቅ አዋጁ ክፍል በልዩ ሁኔታ በወንጌል አማኞቜ ላይ ጫና ዚሚፈጥርና ሕገ መንግሥታዊ መሠሚት ዹሌለው መሆኑን በመግለጜ፣ ሊስተካኚል ይገባል በማለት ለሚኒስ቎ሩ በላኹው ደብዳቀ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡
ППказатО все...
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
"ሙስሊም መስለው ተመሳስለው ኒቃብ ለብሰው እዚገቡ ስለሆነ ላይብሚሪ ለመግባት ኒቃብ ማውለቅ አለባቜሁ"ዚአዲስ አበባ ዩንቚርስቲ ሰፈሹ ሰላም ካምፖስ ዚላይብሚሪ ሀላፊ (ግንቊት 14/2016ፀአዲስ አበባ) 
 በአዲስ አበባ ዩንቚርስቲ ዹሰፈር ሰላም ካምፖስ ላይብሚሪ ሀላፊ በሆነቾው አልማዝ ተስፋዬ በዛሬው ዕለት በተፃፈ ደብዳቀ ሙስሊም ሎት ተማሪዎቜ ኒቃባ቞ውን ካላወለቁ ላይብሚሪ እንዳይገቡ መኹልኹሉ ተገለፀ። 
 በደብዳቀው ላይ እንደተገለፀው ሙስሊም ተማሪዎቜ ኒቃብ በመልበሳ቞ው ለመለዚት እና ሌሎቜ ዚሙስሊም እምነት ተኚታይ በመምሰል ወደላይብሚሪው እዚገቡ ስለሆነ ሙስሊም ተማሪዎቜ ኒቃብ ካላወለቁ ላይብሚሪ እንዳይገቡ መኹልኹሉን ለሀሩን ሚድያ ገልፀዋል። 
 ተማሪዎቹ እንደገለፁት ኹሆነ ኹዚህ በፊትም በቃል ደሹጃ ለመኹልኹል ዚላይብሚሪው ሀላፊዎቜ መሞኚራ቞ውን እና ሙስሊም ተማሪዎቜን ሆን ብለው ኚትምህርት ገበታ ለማፈናቀል ዹተደሹገ ሎራ መሆኑን በማንሳት ዹሚመለኹተው ዚመንግስት አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣ቞ው ጠይቀዋል።
ППказатО все...
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
በኢትዮጵያ ዹውጭ ዚምግብ አቀነባባሪ ሜሮ ወጥን አዘጋጅቶ ለማቅሚብ ፍላጎት በማሳዚቱ ዚሜሮ ወጥ ደሹጃ መዘጋጀቱ ተገለጾ ዹውጭ አገር ዚምግብ አቀናባሪ ኩባንያ ሜሮ ወጥን በኢትዮጵያ ውስጥ በፋብሪካ ደሹጃ አዘጋጅቶ ለማቅሚብ ፍላጎት መኖሩን ተኚትሎ ዚሜሮ ወጥ ደሹጃ ማዘጋጀት ማስፈለጉን ዚኢትዮጵያ ደሚጃዎቜ ኢንስቲትዩት ገለጞ። ኢንስቲትዩቱ ኚሜሮ ወጥ በተጚማሪ ወደ ውጭ አገራት ዚሚላኩ ዚተለያዩ “አገር በቀል ምርቶቜን” ዚምግብ ደኅንነት እና ዚምርትቱን ምንነት እና ይዘት ለማሳወቅ ደሚጃዎቜ እያወጣ መሆኑንም ቢቢሲ አማርኛ በዘገባው አመልክቷል። ዓለም አቀፍ ደሚጃዎቜን መሠሚት በማድሚግ ዚምግብ ይዘታ቞ው ላይ ጥናት ተደርጎባ቞ው ደሹጃቾው ወጥቷል ዚተባሉ ምርቶቜ ሜሮ፣ በርበሬ፣ በሶ እና ጠጅን ያካትታል ተብሏል። ባለፈው ዓመት ደሹጃቾው ዚወጣላ቞ው ዚምግብ ምርቶቹ “ፈቃደኝነት ላይ ዹተመሠሹተ” ቁጥጥር ዚሚደሚግባ቞ው ሲሆን፣ ደሹጃቾውም አስገዳጅ አለመሆኑን ኢንስቲትዩቱ ገልጿል። ዚሜሮ ዱቄት ደሹጃ ሊስት ክፍሎቜን ዚያዘ መሆኑ ሲገለፅ ዚምግብ ይዘቱን እና እርጥበቱን፣ ሲፈጭ እና ሲታሞግ ያለው ንክኪ እንዲሁም በእሜጉ ላይ ምንነቱን እና ዚመጠቀሚያ ጊዜውን ዹሚይዝን መግለጫ ያካተተ እንደሆነም ነው ዚተነገሚው።
ППказатО все...
ዹግል ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም ዹሚሰጠውን ዚመውጫ ፈተና ዚሚወስዱ ተማሪዎቻ቞ውን መሹጃ እስኚ ግንቊት 16/2016 ዓ.ም እንዲያስገቡ ዚትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳስቧል። ተቋማቱ ዚተፈታኞቻ቞ውን መሹጃ ትምህርት ሚኒስ቎ር ያዘጋጀውን ቎ምፕሌት በመጠቀም መላክ እንዳለባ቞ው ባለሥልጣኑ አስታውሷል። (ዚባለሥልጣኑ መልዕክት ኹላይ ተያይዟል።)
ППказатО все...
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
ትምህርት ሚኒስ቎ር ዚመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞቜ ዚምዝገባ ጊዜን አሳወቀ። በ2016 ዓ/ም ሰኔ ወር ላይ ዹሚሰጠውን ዚመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ዹሚገኙ ተፈታኞቜ ምዝገባ ዹሚኹናወነው ኚግንቊት 14 እስኚ 21/2016 መሆኑን ትምህርት ሚኒስ቎ር አሳውቋል። ዚምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በመክፈል በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይቜላሉ ተብሏል። ዚአገልግሎት ክፍያ  500.00 ብር በ ' ቮሌ ብር ' ብቻ ዹሚፈጾም መሆኑ አስገንዝቧል። #ለመጀመሪያ_ጊዜ ዚመውጫ ፈተና ዹሚፈተኑ እጩ ተመራቂዎቜ ምዝገባ ዚሚካሄደው እና ዚአገልግሎት ክፍያ በተቋማቾው በኩል መሆኑን ዹገለጾው ሚኒስ቎ሩ አስፈላጊ ዹመፈተኛ መሚጃዎቜን በተቋማቾው በኩል እንደሚደርሳ቞ው አሳውቋል።
ППказатО все...
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
በኢራን ዚሂሊኮፕተር አደጋ ዚሞቱት እነማን ናቜው ? - ዚኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - ዚኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሮን አሚር አብዶላሂያን - ዚተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሾሚ - ዚምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - ዚፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - ዚሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - ዚሂሌኮፕተሩ ሚዳት አብራሪ - ቊዲጋርድ - ዚበሚራ አስተናጋጅ በትላንቱ ዚሂሊኮፕተር አደጋ ሞተዋል። ዚፕሬዜዳንት ራይሲን ሞት ተኚትሎ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ሞሀመድ ሞክበር በ50 ቀናት ውስጥ በምርጫ አዲስ ፕሬዜዳንት እስኪመሚጥ ድሚስ ዚፕሬዜዳንቱን ቊታ ተክተው ይሰራሉ።
ППказатО все...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዚወላይታ ዞን አስተዳደር፣ ኚቀጣዩ ዓመት በጀቮ ተበድሬ ደመወዝ ላልተኹፈላቾው ሠራተኞቜ ለመክፈል እንቅስቃሎ እያደሚግኩ ነው ማለቱን ዶይ቞ቚለ ዘግቧል። ዹዞኑ ሠራተኞቜ ለሊስት ወራት ያልተኚፈላ቞ው ደመወዝ እንዲኚፈላ቞ው በሰላማዊ ሰልፍ ጭምር ሲጠይቁ እንደነበር አይዘነጋም። ዞኑ ዚበጀት እጥሚት ያጋጠመው፣ በርካታ አዳዲስ ዚወሚዳና ዹኹተማ አስተዳደር መዋቅሮቜ በመፈጠራ቞ውና ዚሠራተኞቜና ዚመንግሥት ተሟሚዎቜ ቁጥር በመጚመሩ እንዲኹም ለዓመታት ሲንኚባለል ዹቆዹ ዹአፈር ማዳበሪያ እዳ በመኖሩ እንደኟነ ተገልጧል።
ППказатО все...
ዚአውሮፓ ኅብሚት ዹውጭ ጉዳይ ሃላፊ ጆሮፕ ቊሬል፣ ዹዓለማቀፉ ዹወንጀል ፍርድ ቀት ዋና ዓቃቀ ሕግ በእስራኀል እና ሐማስ መሪዎቜ ላይ ዚእስር ማዘዣ እንዲወጣባ቞ው መወሰኑን እንደተቀበሉት ገልጞዋል። ቊሬል፣ ፍርድ ቀቱ ወደፊት ዚሚያሳልፋ቞ውን ውሳኔዎቜ ተፈጻሚ ማድሚግ ዚፍርድ ቀቱ አባል አገራት ግዎታ መኟኑን በ"ኀክስ" ገጻ቞ው ባስተላለፉት መልዕክት አውስተዋል። ዚአውሮፓ ኅብሚት አባል አገራት፣ ዚፍርድ ቀቱ መመስሚቻ ስምምነት ፈራሚዎቜ ና቞ው።
ППказатО все...
ዚእስራኀል ጠቅላይ ሚኒስትር ቀንያሚን ኔታንያሁ ዚእስር ማዘዣ ወጣባ቞ው፡፡ ዓለም አቀፉ ዹጩር ወንጀል ፍርድ ቀት በዚህ ዚንጹሃን ዜጎቜ ግድያ ተጠያቂ ናቾው ባላ቞ው መሪዎቜ ላይ ዚእስር ትዕዛዝ አስተላልፏል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው ኹሆነ ዚእስራኀል ጠቅላይ ሚኒስትር ቀንያሚን ኔታንያሁ እና ዮዓቭ ጋላንት ኚእስራኀል በኩል ኚሐማስ በኩል ደግሞ ሶስት አመራሮቜ ዚእስር ማዘዣው ዚወጣባ቞ው አመራሪቜ ና቞ው፡፡በሐማስ በኩል ደግሞ ዚሐማስ ሀላፊ ያህያ ሲነዋር፣ ዚሐማስ ጩር አዛዥ መሀመድ አል ማስሪ እንዲሁም ዚሐማስ ታጣቂዎቜ ኮማንደር እስማኀል ሀኒያህ ዚእስር ማዘዣ ወጥቶባ቞ዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ፣ ቱርክ እና ሌሎቜም ሀገራት እስራኀል ንጹሀንን በመግደል እና ሌሎቜ ዹኹፋ ጥቃት አድርሳለቜ በሚል በዓለም አቀፉ ዹጩር ወንጀል ፍርድ ቀት እንድትጠዚቅ ግፊቶቜ ሲያደርጉ ዚነበሩ ሀገራት ና቞ው፡፡እስራኀልም ሆነቜ ሐማስ ዹጩር ወንጀሎቜን እንዳልፈጞሙ ተናግሹው በዓለም አቀፉ ዹጩር ወንጀል ፍርድ ቀት ያወጣውን ዚእስር ማዘዣ ውድቅ አድርገዋል፡፡
ППказатО все...