uk
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Відкрити в Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Показати більше
1 160
Підписники
-124 години
+17 днів
+530 день
Архів дописів
ይህን ትውልድ በምንም መልኩ ማስፈራራት አይቻልም። አመራሮቹን በማዋከብ የሚታፈን ጥያቄ አይኖርም። ጥያቄው የመብት እና የፍትህ ነው። መንገዳችንም ሁልጊዜም ሰላማዊ ነው! የተማሪዎችን ሰላማዊ ጥያቄ በ
+3
ይህን ትውልድ በምንም መልኩ ማስፈራራት አይቻልም። አመራሮቹን በማዋከብ የሚታፈን ጥያቄ አይኖርም። ጥያቄው የመብት እና የፍትህ ነው። መንገዳችንም ሁልጊዜም ሰላማዊ ነው! የተማሪዎችን ሰላማዊ ጥያቄ በምንም መልኩ ማስቆም አይቻልም!! @aaumsu

You can follow 6kilo main channel live stream

በ 5ኛ በር የምትመጡ ልጆች በኤቲኤም በኩል መምጣት ትችላላችሁ !

Notice! ሰላማዊ ጥያቄ የያዘን ተማሪ አላስገባም ማለት ከአምባገንነትም አምባገንነት ነው! በአምስተኛ በር የተዘጋባችሁ ወንድም እና እህቶች በአንደኛ በር ግቡ! @aaumsu

ጥያቄያችን ግልጽ ነው! ጥያቄያችን የፍትህ የእኩልነት፤ የመብት ነው። ከማንም ውለታን አንፈልግም፤ የኛ የሆነውን መብታችንን ነው! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን! @aaumsu
+2
ጥያቄያችን ግልጽ ነው! ጥያቄያችን የፍትህ የእኩልነት፤ የመብት ነው። ከማንም ውለታን አንፈልግም፤ የኛ የሆነውን መብታችንን ነው! ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን! @aaumsu

ያልመጣችሁ ወንድም እህቶች ገና ስለሆነ አሁን ኑ።

መብቱን አሳልፎ የማይሰጥ ትውልድ! መብቱን ለማስከበር መሄድ ያለበትን ሁሉ የሚሄድ ትውልድ እንደሆነ አላወቁም! @aaumsu
+3
መብቱን አሳልፎ የማይሰጥ ትውልድ! መብቱን ለማስከበር መሄድ ያለበትን ሁሉ የሚሄድ ትውልድ እንደሆነ አላወቁም! @aaumsu

ፕሬዝዳንቱ ሳይመጡ የትም አንሄድም! ጥያቄያችን ምላሽ ሳያገኝ ወደኃላ ማለት የለም ያሉት የግቢያችን ሙስሊም ተማሪዎች በአሁን ሰዓት በፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት በገፍ ተሰባሰበዋል! @aaumsu
+7
ፕሬዝዳንቱ ሳይመጡ የትም አንሄድም! ጥያቄያችን ምላሽ ሳያገኝ ወደኃላ ማለት የለም ያሉት የግቢያችን ሙስሊም ተማሪዎች በአሁን ሰዓት በፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት በገፍ ተሰባሰበዋል! @aaumsu

አላሁ አክበር!!! አላሁ አክበር!!! ከ19 ወራት በላይ፤ ከ620 ቀናት በላይ ጥያቄ አለን! ሲሉ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለጥያቄ መልስ እንፈልጋለን! በማለት በአሁኑ ሰዓ
+3
አላሁ አክበር!!! አላሁ አክበር!!! ከ19 ወራት በላይ፤ ከ620 ቀናት በላይ ጥያቄ አለን! ሲሉ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለጥያቄ መልስ እንፈልጋለን! በማለት በአሁኑ ሰዓት ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤቱ ጋር ይገኛሉ!! @aaumsu

"አሁን አሸባሪ እንደዚህ ሆኖ ቢገባና ጉዳት ቢያደርስ ራሳችሁን አይጸጽታችሁም?" ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎችን ላይብረሪ አትገቡም ብሎ ከልክሎ ምክንያቱን ሲያብራራ ከተናገረው ነው። ሙስሊም ጠልነታቸው በዚህ ልክ አግጥጦ ነው የሚታየው። እነዚህን አካላት ደፍሮ ከመጠየቅ፣ ከመታገል እና በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ ውጪ አማራጭ የለንም። By any means necessary መብታችን ሊከበር ግድ ነው። በመመሪያ የከለከሉትን መብት በመመሪያ ከለላ እስኪሰጡት መጠየቅ ግድ ነው። መብታችንን የጣሱ አካላት ተጠያቂ ሊደረጉ ግድ ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

"ለእኛ አጀንዳ ሰጥተው ከትምህርት ያዘናጉን አካላት ቀጣዩን ትውልድ፤ የእኛን ልጆች፤ የእኛን ወንድም እህቶች በተመሳሳይ ጥያቄ ከትምህርት እንዲያዘናጓቸው አንፈልግም። እኛ እየተሳቀቅን የኖርንበትን፤ እኛ እየተሳቀቅን የተማርንበትን፤ ማንም አካል በክብራችን እየተረማመደ ያለበትን ሁኔታ በእኛ ልጆች ላይ እንዲደገም አንፈቅድም።" @aaumsu

የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው! ፍትህን ለማስፈንና መብቶቻችንን ለማስከበር በምናደርገው ጉዞ ውስጥ የሚገጥሙን መሰናክሎች የጥንካሬያችን መለኪያ እንጂ የውድቀታችን ምልክቶች አይደሉም። ጨለማው በጣም የሚበረታው ሊነጋ ሲል እንደሆነ ሁሉ፣ ፈተናውም የሚከብደው ድሉ ሊመጣ ሲቃረብ ነው። ታላቁ ጌታችን በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይለናል፦
"የአላህ እርዳታ መቼ ነው? ይሉ ዘንድ (ተጨነቁ)። ንቁ! የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው።" (አል-በቀራህ፡ 214)
ይህ የጽናት ጊዜ ነው። ይህ የተወኩል ወቅት ነው። የሐቅ መንገድ መቼም ቢሆን ቢጠነክር እንጂ አይበጠስም። በጌታችን በአላህ ቃል ኪዳን ላይ ሙሉ እምነት አለን፤ እርሱ ፍትሃዊ ነውና የተገፉትን አይጥልም፣ የደጋጎችንም ስራ አያጠፋም። 📌 ጥንካሬያችን የሚመነጨው ከልባችን እምነት እንጂ ከሁኔታዎች መለዋወጥ አይደለም። 📌 እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በዱዓ ተጠናክረን ወደፊት እንጓዛለን። 📌 ትዕግስት የድል ሁሉ ቁልፍ ናት። 📌 ለእውነት የቆመ ማንም ይሁን ማን፣ መጨረሻው ስኬት ነው። እውነትና ፍትህ አሸናፊ መሆናቸው የማይቀር ሃቅ ነው። ጌታችን ሆይ! በጽናት አጽናን፤ ድልህንም ቅርብ አድርግልን። @aaumsu

🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨ 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آ
🎉ዛሬ ጁምዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ            ሰለዋትን እናብዛ🎉✨✨ 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }    ✨✨   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  ✨✨ 🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል........ "أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً" ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ- እስልምናን ለማስከበር ለሚታገሉ እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!! اللَّهُمَّ اجعلهم مِنَ الَّذِينَ يَثْبُتُونَ عَلَى صِرَاطِكَ، وَثَبِّتْ قُلُوبَهُمْ عَلَى طَاعَتِكَ، وَانْصُرْهُمْ عَلَى أَنْفُسِهِمْ وَأَعْدَائِهِمْ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

🔊ከትላንቱ አቅሳ መስጂድ  "ረሂቀል መህቱም" የረሱሉ ﷺ ሲራ ደርስ የተወሰደ!! ✍️"የዚ ኡማ ፊራውን" የተባለው አቡ ጀህል ፤ ያ ፈርጣማ ሰውነት ያለው ግዙፉ የኢስላም ጠር፤ ረሱልን ﷺ ሲሳደብ፣ ሲዘልፍ፣ በል እንደውም ሲመታቸው የነበረው ያ የሙሽሪክ ቁንጮ የገደሉት 2 ለጋ ታዳጊ ልጆች ነበሩ። ሙሽሪኮች አለቃቸው እንዳይገደል ጥቅጥቅ እንዳለ ጫካ ዙሪያውን ከበው ቢጠብቁትም እነዚ ለግላጋ ታዳጊ ልጆች ካላቸው ወኔ እና ቆራጥነት የተነሳ ወድያው ፈትለክ ብለው ሰይፋቸውን አሳረፉበት። 👉ቢላል ረ.ዐ ለዛ ሁሉ ስቃይ የዳረገውን ፤ በዛ ምድረ-በዳ ትልቁን ቋጥኝ ጭኖበት ክፈር ሲሉት 'አሃድ አሃድ' በማለት ያስተጋባው ሀበሻዊው ቢላል ረ.ዐ ኡመያን ኢብኑ  ሀለፍ ከአብዱራህማን ኢብኑ አውፍ እጅ አስጥሎ ገደለው ፤ በተደጋጋሚም እንዲ ይል ነበር......"ዛሬ ወይ እኔ ወይ እሱ" 🪄ታዲያ እኛ ታዳጊ ለግላጋ የቢላል ልጆች መብታችን ተረግጦ ዝም ምንል ነን እንዴ? የሀበሻው ቢላል ረ.ዐ ምትኮች መሆን ያቅተን ይሁን!! ያ ኡመተ ሙሐመድ ንቁ !!!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቦርድ ሙስሊም ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው እያደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በመግለፅ መፍትሔ ያመጣ ዘንድ ለቦርዱ ደብዳቤ ይዘው የሄዱት ከወራት በፊት ነበር። ደብዳቤውን ለማስገባት
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቦርድ ሙስሊም ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው እያደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በመግለፅ መፍትሔ ያመጣ ዘንድ ለቦርዱ ደብዳቤ ይዘው የሄዱት ከወራት በፊት ነበር። ደብዳቤውን ለማስገባት ለሄዱት ተወካዮች "ቦርድ የዩኒቨርስቲው የመጨረሻ አካል ስለሆነ እስከዛሬ የሄዳችሁበትን መንገድ በደንብ በሚገልፅ መልኩ፤ ለተቋማት ሁሉ ያስገባችሗቸውን ደብዳቤ እንዲሁም የሰጡትን ምላሽ አጠናቅራችሁ አምጡ።" - የሚልን ምላሽ ሰጠ። መስፈርታቸውን በመቀበልም በብዙ ቀናት ዶክመንቶች ተዘጋጅተው ካለቁ ቡሃላ ተወካዮች ደብዳቤውን ከእነ ዶክመንቶቹ ለማስገባት ሲሄዱ "እኛ ከእናንተ ደብዳቤ አንቀበልም!" - በማለት መልሰዋል። የዩኒቨርስቲው አመራሮችየተማሪዎችን ጥያቄ በማፈን እና መብታቸውን በመጣስ የጀመሩት የቁልቁለት ጉዞ ከቦርድ መድረሱ በጣም የሚያሳዝን ነው። ጥያቄያችንን በደብዳቤ ስናስገባ መቀበል፤ ችግሮቻችንን በውይይት እንፈታ ዘንድ ስንጠይቅም ማስተናገድ ግዴታም ስልጣኔም ቢሆንም አሻፈረኝ እንዳሉ ነው። ያም ሆነ ይህ ግን መብቶቻችን መከበራቸው አይቀሬ ነው። በሁሉም መንገድ ጠይቀን የነጠቁንን መብት እናስከብራለን፤ በደል የፈፀሙብን አካላትም ተጠያቂ ይሆናሉ። "ንቁ! የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው (ተባሉም)፡፡" [2:214] @aaumsu

በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ባነዎ ኒቃቢስት ተማሪ ፎር ይሰራ የረፐረ የመብት ወትላለፍ በገገህኖ አነበት ዝ ይመስር!! ተጨራ እንዝር ዋብ ያስፈልግ!! ይንም ሰብ ይሰር ኸማም አስራጮዊ!! ጥያቄ ነረንደ_ ፍትሐዊ የኸረ መልስ ይቸን ዳረጋ!! @aaumsu

في جامعة أديس أبابا، تعرضت الطالبات المنتقبات لانتهاكات تمس حقوقهن. يجب أن يصل هذا الأمر للجميع، ويجب اتخاذ خطوات لتحقيق العدالة. استمعوا لرسالتهن وانشروها أمانةً لوجه الله، وسنستمر في طرح السؤال حتى نصل إلى إجابة عادلة. @aaumsu

"ዝምታው ይሰበር! ጭቆናው ይብቃ!" - ወንድም ሙራድ ታደሰ የሚከተለውን መልዕክትም አስተላልፏል፦ "መንግስት አለ» በምንልበት፣ የሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበ
"ዝምታው ይሰበር! ጭቆናው ይብቃ!" - ወንድም ሙራድ ታደሰ    የሚከተለውን መልዕክትም አስተላልፏል፦ "መንግስት አለ» በምንልበት፣ የሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ፣ 4 ኪሎ እና 6 ኪሎ (AAU) ላይ የሙስሊም እህቶቻችንን መብት ማስከበር ካልቻልን፤ የመንግስት አማጺ እና ጽንፈኛ በነገሰበት አክሱም ከተማ ላይ ሙስሊሙ መብት ያገኛል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው! ይህ በዋና ከተማችን፣ በመንግስት አፍንጫ ስር እየሆነ ያለ ግልጽ መዋቅራዊ ጭቆና ነው! በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ሴቶችን ክብር እና መብት ማስከበር ያቃተው ኡማ፣ አክሱም ላይ ሄዶ መብት አስከብራለሁ ቢል ቀልድ ነው።" ኢንሻአላህ _ መብቶቻችንን ለምነን ሳይሆን ታግለን እናስከብራለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! @aaumsu

በአዲስ አበበ ዩምበረስቲ  በኒቃቢስት ደረሳሶ ኢጄጅ ናረይ ምካት ተገግኒሙ ቲሰሙይ። አጥናቡይ! ለበለ ሰብ ኢጄጃምነኮ አሱይ ሱል አለነ_ ኣዲል ጀዋብ ኢመጫን ጃንጎ!!! @aaumsu

Sarbama mirgaafii cunqursa barattoota yuniversitii Finfinnee irra gahaa jiru, afaan niqaabistoota irraa. Dhaggeeffadhaa, hunduu akka dhagahuufis tamsaasaa. Gaaffii qabna_ deebiin haqaa hanga kennamutti ! @aaumsu