5killo Jem'a official Channel
Відкрити в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Показати більше1 159
Підписники
-124 години
Немає даних7 днів
-130 днів
Архів дописів
+4
ወንድም ሙራድ ታደሰ --- ሴኩላሪዝምን እንደ ሽፋን ተጠቅሞ ሒጃብን በመመሪያ በከለከለ ማግስት ሴኩላሪዝምን የሚጥስ የበዓል መልዕክት ስላስተላለፈው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከላይ ያለውን ፅሁፍ አስፍሯል። የAAU ሙስሊም ተማሪዎች እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ብዙዎች ዝም ባሉበት ከተማሪዎቹ እኩል ከመጀመሪያው ጀምሮ ድምፁን ሲያስተጋባም ነበር። ሀላፊነቱን በአግባቡ በመወጣት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ስላስተጋባ፤ ፍትሕ ይመጣ ዘንድ ስለሞገተ እናመሠግናለን። አላህ ከመጥፎ ነገሮች ይጠብቀው! ጥረቶቹንም ለመልካም ለውጥ ሰበብ ያድርግ!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
We are about to start our online ders on aqidetu Altahawiya,
Please join the Qirat channel to follow the session on the live stream.
https://t.me/qirat_channel_5k
+4
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች በሚንበር ቲቪ ቢሮ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
------------------------------------------
ሚያዝያ 2 / 2018 ዓ.ል
------------------------------------------
በሁሉም ኢትዮጵያዊ የተገነቡ ሚዲያዎች ስለሙስሊሙ ድምፅ ሳይሆኑ ሲቀር፤ ከዚያም አልፈው በሙስሊሙ ላይ የተሳሳተ መረጃን ሲነዙ፤ በችግሩ እና በሚያስፈልገው ሰዓት ሽፋን ሳይሰጡ ሲቀሩ ስለሙስሊሞች የሚዘግቡ ድምፅ የሚሆኑና በቋሚነት የሚሰሩ ሚዲያዎች እንደተቋቋሙ እሙን ነው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎችም ይህንን ክፍተት ለመድፈን ከተቋቋሙት ሚዲያዎች ደጋግመው በመሄድ እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት ይዘግቡላቸው ዘንድ ጠይቀዋል።
በሚንበር ቲቪ ተገኝተውም እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት በማብራራት፤ መፍትሔ ለማምጣት የሄዱበትን ርቀት በመግለፅ፤ ዘላቂ መፍትሔ እስኪመጣ ድረስ እንደ ሚዲያ ማድረግ ያለባቸውን ሁሉ ያደርጉ ዘንድ ጠይቀዋል።
ይህ የሁሉም ሀላፊነት ነውና ኡስታዞቻችን፣ መሻይኾች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕናዎች በተለይም ደግሞ መጅሊስ መፍትሔ ለማምጣት መትጋት አለባቸው። ለሙስሊሙ ከተቋቋሙት ሚዲያዎች ጀምሮ በሀገር ሐብት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የተቋቋሙት ሁሉ ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ግድ ነው። የሚመለከታቸው ተቋማት እና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ሁሉም ስለፍትሕ ሲባል ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
ዘመቻ 5 _ በነቢል ዘይን የቲክቶክ ገፅ !
አጀንዳውን አጀንዳው አድርጎ ሀላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ከጀመረ ሰነባብቷል። ሳይደክም ሳይታክት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፁን አሰምቷል። እናመሠግናለን! አላህ ጥረቱን በኸይር ይተካ!! ለመልካም ለውጥም ሰበብ ያድርግ። ሁላችንም በተዋቀረ ሁኔታ ድምፃችንን ካሰማን የማናሳካው ጉዳይ አይኖርም። የበዳዮች ግፍ ቆሞም ፍትሕ ይሰፍናል።
በዘመቻችን፦ ቪድዮዎቹን ማየት ማዳመጥ ግዴታችን ነው። ኮሜንት በመጨመር ስለጉዳዩ አሳሳቢነት መግለፅ ስራችን ነው። ለሁሉም በማሰራጨት እውቀና መፍጠር ከሀላፊነታችን ነው።
ሊንኩ https://vm.tiktok.com/ZS9LNcd7Djvtm-d2Xmq ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ __ በዳዩ መመሪያ ተሻሽሎ መብታችን እስኪከበር ! ! !
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ዘመቻ 4 _ በመርየም ልጅ የቲክቶክ ፔጅ ! ! !
ፔጁ ከ1 ሚልዮን በላይ ተከታይ አለው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው በደል ቆሞ ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ከላይ ያለውን ቪድዮ አጋርቷል። ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ስለተወጡ እናመሰግናለን። በአላህ ፈቃድ በአንድነት በሕብረት ድምፃችንን ከዳር እስከ ዳር በማሰማት የሚፈለገው ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ እንተጋለን።
በዘመቻችን፦ ቪድዮውን መመልከት፤ ስለፍትሕ ኮሜንት መስጠት ብሎም ለሁሉም ማሰራጨት ቀላሉ ሀላፊነታችን ነው።
ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSHx27Uks/
ነው።
ወደ ተግባር ! ! !
ፍትሕ እስኪሰፍን በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ ጥያቄ አለን እንላለን ! ! !
@aaumsu
🌙 ONLINE QIRA'AT DARS
Seeking Clarity in Your ‘Aqeedah
Are you looking to strengthen your understanding of Islamic belief in a clear, authentic, and structured way?
Here is a beautiful opportunity to learn a foundational text with guidance and clarity.
📚 Study: Al-Aqidah al-Tahawiyyah
(A Foundational Text in Islamic Belief)
👤 Instructor: Ustaz Zanjabil
🗓 Start Date: Saturday, April 11
📅 Schedule: Every Saturday & Sunday
⏰ Time: After Fajr (12:00 AM)
✨ What you will gain:
• Clear and structured explanation of core beliefs
• Interactive Q&A sessions
• Strengthening your understanding with authentic texts
• Certificate awarded upon consistent qira’at attendance and passing the final examination.
💫 Special gifts for top 3 students✨
🎓 Open to all students from any department and campus
⚠️ Only 1 day left — don’t miss this opportunity!
📝 Register now using the Google Form below👇👇👇
https://forms.gle/mR3hBMJ42hoP4V996
📢 Join the 5K Qira’at channel where the qira’at sessions are delivered
🤝 Take this step to build a strong foundation in your din and grow in beneficial knowledge.
@fivekjemaa
Hadith
وعنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول: "الدنيا ملعونة ملعون ما فيها إلا ذكر الله تعالى، وما والاه، وعالمًا أو متعلمًا" ((رواه الترمذي وقال: حديث حسن. )). (2)
Abu Hurairah (May Allah be pleased with him) reported:
The Messenger of Allah (ﷺ) said, "The world, with all that it contains, is accursed except for the remembrance of Allah that which pleases Allah; and the religious scholars and seekers of knowledge."
[At- Tirmidhi].
Riyad as-Salihin, 1384
Hadith
وعنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول: "الدنيا ملعونة ملعون ما فيها إلا ذكر الله تعالى، وما والاه، وعالمًا أو متعلمًا" ((رواه الترمذي وقال: حديث حسن. )). (2)
Abu Hurairah (May Allah be pleased with him) reported:
The Messenger of Allah (ﷺ) said, "The world, with all that it contains, is accursed except for the remembrance of Allah that which pleases Allah; and the religious scholars and seekers of knowledge."
[At- Tirmidhi].
Riyad as-Salihin, 1384
Repost from AAU - Muslim Students Union
ዘመቻ 3 _ በSeid Kemal Official !
በቲክቶክ 291 ሺህ ተከታይ አሉት። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ከላይ የሚታየውን ቪድዮ ሰርቶ 362 ሺህ እይታ፤ 74 ሺህ ላይክ እንዲሁም ከ50 ሺህ በላይ ሼር ያገኘ ሲሆን ድምፃችንን በሚገባው አስተጋብቷል። ሀላፊነቱን በሚገባ በመወጣት ስላሳየው አጋርነት በጥልቁ እናመሠግናለን።
በዘመቻችን፦ ቪድዮውን ማየት፤ ላልሰሙት ማሰማት፤ እየደረሰ ስላለው በደል በኮሜንት ገብቶ ድምፅ መሆን የእኛ ሀላፊነት ነው።
ሊንኩ https://vt.tiktok.com/ZSHxg2FWQ/ ነው።
ወደ ተግባር ! ! !
ፍትሕ እስኪመጣ በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄ አለን እንላለን ! ! !
@aaumsu
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉
إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﷺ
🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
"ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።"
ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው።
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ-ለዲን ሲሉ እየታገሉ ላሉም እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!!
በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️
اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
ዘመቻ 2 _ በAbdii Sabaa Media !
ሚዲያው ዶክመንተሪ አዘጋጅቷል። በዶክመንተሪው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች ሲደርስባቸው ስለነበረው በደል በዝርዝር አስቀምጠዋል። ዩኒቨርስቲው እየመለሰበት ስላለው መንገድም አብራርተዋል። አሰሰቸኳይ መፍትሔ መጥቶ ሁሉም ተጠያቂ ይሆን ዘንድ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዘመቻችን፦ ቪድዮውን በመመልከት መልዕክቱን እንውሰድ። ከሁሉም ይደርስ ዘንድም በሁሉም መንገድ እናሰራጭ። ዩኒቨርስቲው የሰራውን ግፍ ሁሉም ያውቅ ዘንድ። ስለተቋማቶቻችን ዝምታ ሁሉም ይረዳ ዘንድ። ስለመፍትሔው ሁሉም ይመክር ዘንድ።
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው! ይህ ለኡመር ልጆች ምንም ነው። ይህ ለሱመያ ምትኮች ምንም ነው። ይህ ለአሽረፈልኸልቅ ኡማ ቀላል ነው።
ሊንኩ https://youtu.be/-oev1Tkye8M ነው።
ወደ ተግባር!
ፍትህ እስኪሰፍን በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄ አለን እንላለን።
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በመገኘት ዩኒቨርስቲው እየፈፀመባቸው ስላለው በደል አቤቱታ አቀረቡ !!!
----------------------------------
ሚያዚያ 1 / 2018 ዓ.ል
----------------------------------
በዳዮች የሕዝብን እንባ ማፍሰሳቸው በታሪክ የታዬ ዛሬም የቀጠለ ነው። ሆኖም ግን በዳይን በዳይ ሲወርሰው ስለመብቱ የሚሞግትንም ለነፃነቱ የሚታገል ትውልድ ይወርሰዋል። በዚህም ፍትሕ እየሰፈነ ሕይዎት ይቀጥላል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶችም በዩኒቨርስቲው ግፍ እየተፈፀመባቸው መሆኑ የአደባባይ ሐቅ ነው። የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በስሙ ልክ ሆኖ የፈሰሰው እንባቸው ይታበስ ዘንድ ሰበብ እንዲሆን በማለት ከቢሮው በመገኘት አቤቱታቸውን አቅርበዋል። እየደረሰባቸው ያለውን በደል አብራርተው፤ የሄዱበትን ርቀት አስረድተው፤ በዳዮች የመለሱበት መንገድ ገልፀው ስለፍትሕ ሲባል መደረግ ስላለበት አስቀምጠዋል።
ታሪክ እየፃፈ ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች መብት ማን እንደታገለ፤ ማን ከትክክለኛው ቦታ እንደቆመ ታሪክ እየመዘገበ ነው። ያለፈው ትውልድ ትግል እና መስዋዕትነት እንደተከተበ ሁሉ የአሁኑም ትውልድ ንቅንቄ እየተመዘገበ ነው።
በአላህ ፈቃድ ለጥያቄው ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ድረስ ጉዞው ይቀጥላል። ሳንደክም ሳናፍር ሳንፈራ በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄያችንን እናነሳለን።
ጥያቄ አለን እንላለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ዘመቻ 1 _ በሙባረክ ፖድካስት !
"የአንድ ሙስሊም ተማሪ ዋጋ ስንት ነው?" - በሚል ሐሳብ ተነስቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው በደል ይዳስሳል። ከዩኒቨርሲቲው ጀምሮ፤ መጅሊስን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የሰጡትን ምላሽ በዝርዝር ያስቀምጣል። የመፍትሔ ሀሳቡንም በጥልቀት ይገልፃል።
ዘመቻችን፦ ቪድዮውን በመመልከት ሐሳቡን እንውሰድ። ከሁሉም ሰው ይደርስ ዘንድ። ዩኒቨርሲቲው እየፈፀመው ያለው በደል ይጋለጥ ዘንድ። ተቋማቶቻችን ሀላፊነታቸውን በኣግባቡ ይወጡ ዘንድ። ሁሉም ሰው ለፍትሕ ይተጋ ዘንድ።
ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው። አይደለም ወይ ያኡመተ ሙሐመድ?! ወደ ተግባር።
ሊንኩ፦ https://youtu.be/kRqk0MXuXvc?si=EJxv8KNF0yb1aFyZ ነው።
ፍትህ እስኪሰፍን በሁሉም ቦታ ለሁሉም ጥያቄ አለን እንላለን።
©aaumsu
@fivekjemaa
ከሐሙስ እስከ ማክሰኞ _ ዝግጁ ናችሁ ? !
ስለ መብታችሁ ለመጠየቅ ዝግጁ ናችሁ? አንተ የነቢ ኡማ! የእህቶችህን ክብር ለማስመለስ ጊዜ ለመስጠት ዝግጁ ነህ? አንተ የኡመር ልጅ! ስለዲንሽ ጊዜ ለመስጠት ዝግጁ ነሽ? አንቺ የኸዲጃ ምትክ!
ከሐሙስ እስከ ማክሰኞ በመጀመሪያ ዙር ሰፊ የሆነ የሚዲያ ዘመቻ ይኖረናል። ጊዜ ሰጥተን መሳተፍ እና ማስተባበር ደግሞ የእኛ ፈንታ ነው። ዝግጁ ናችሁ? ዝግጁ ነህ? ዝግጁ ነሽ? ያኡመተ ሙሐመድ _ ስለክብርህ! አንቺ የፋጢማ ምትክ _ ስለዲንሽ! አንተ የአልይ ልጅ _ ስለ እስልምናህ!
ከሆናችሁ 👍 አሳዩን! 100 እንደሞላ እንጀምራለን!!
©aaumsu
@fivekjemaa
"ምግቡ ምንም ቢሆን እንችለዋለን። በመጀመሪያ በእህቶቻችን ላይ እየፈፀማችሁት ያለውን በደል አቁሙ።" - በAAU Main Campus ያለ ተማሪ
በዛሬው እለት የሆነ ነው። የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ከተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ ተገኝተው "ምግቡ እንዴት ነው? ምን ይሻሻል?" - በማለት ይጠይቃሉ። በዚህም መሐል አንድ ተማሪ ምግቡ ምንም ይሁን እንችለዋለን። በመጀመሪያ በኒቃቢስት እህቶቻችን ላይ እየፈፀማችሁት ያለውን በደል አቁሙ።" - በማለት ጠይቋል። እየፈፀሙት ያለውን በደል ሸፋፍነው ለማለፍ ቢሞክሩም እስከ ጥግ ሞግቷቸው አልፏል። "በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ እንጠይቃለን።" - ስንል ለእስልምናው የሚቆምን ትውልድ ይዘን ነው። ከምግብ ይልቅ ስለዲኑ ለመጠየቅ የማያፍር የማይፈራ ትውልድ ይዘን ነው።
ፍትሐዊ መልስ እስኪጣም በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ ጥያቄ አለን ማለታችንን እንቀጥላለን።
©aaumsu
🌙 ONLINE SHORT COURSE
Seeking Clarity in Your ‘Aqeedah
Are you looking to strengthen your understanding of Islamic belief in a clear, authentic, and structured way?
Here is a beautiful opportunity to learn a foundational text with guidance and clarity.
📚 Study: Al-Aqidah al-Tahawiyyah
(A Foundational Text in Islamic Belief)
👤 Instructor: Ustaz Zanjabil
🗓 Start Date: Saturday, April 11
📅 Schedule: Every Saturday & Sunday
⏰ Time: After Fajr (12:00 AM)
✨ What you will gain:
• Clear and structured explanation of core beliefs
• Interactive Q&A sessions
• Strengthening your understanding with authentic texts
• Certificate awarded upon consistent qira’at attendance and passing the final examination.
💫 Special gifts for top 3 students✨
🎓 Open to all students from any department and campus
⚠️ Only a few days left — don’t miss this opportunity!
📝 Register now using the Google Form below👇👇👇
https://forms.gle/mR3hBMJ42hoP4V996
📢 Join the 5K Qira’at channel where the qira’at sessions are delivered
🤝 Take this step to build a strong foundation in your din and grow in beneficial knowledge.
@fivekjemaa
اَلسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
💥 የደርስ ማስታወሻ::::::::::::::::::
✅ ኢንሻአላህ የኡምደቱል አህካም ደርሳችን ዛሬም የሚቀጥል ይሆናል።ከመጝሪብ እስከ ኢሻ ባለው ስአት በ4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ እንገናኝ። 🕌
«በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ✨
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/479
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ📱
https://t.me/Qirat4k
⏰ :- ከመግሪብ - ኢሻ
🕌 4ኪሎ ተማሪዎች መስጅድ
©aau4kilomsj
ሸይኽ ሙቅቢል ብኑ ሃዲ አልዋዲዒይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ :-
"የዲን ወንድሞቼ ሆይ! እነዚህ የዶክትሬት፣ የፕሮፌሰርነትና መሰል ማእረጎች ሱንና፣ ዲንና አላህን መፍራት ካልተቆራኛቸው በስተቀር እኛ ዘንድ የሽንኩርት ያክል ዋጋ የላቸውም።
(يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُمْ مِنْ ذَكَرٍ وَأُنْثَىٰ وَجَعَلْنَاكُمْ شُعُوبًا وَقَبَائِلَ لِتَعَارَفُوا ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِنْدَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ)
"እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ብሔሮችና ጎሳዎች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ ይበልጥ አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን አዋቂ ውስጥንም አዋቂ ነው፡፡" [አልሑጁራት: 13]
[ኢጃበቱ አስ - ሳኢል: 140]
©
+1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በፌደራል መጅሊስ ቢሮ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ያለው በደል ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ እንዲሰራ ጠየቁ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 30 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
መጅሊስ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በሀገራቸው መብታቸው ሲጓደል ሊጠይቅ፤ የመብት ጥሰት ሲፈፀምባቸው መብታቸውን ሊያስከብር፤ በሁሉም መስክ ያለልዩነት እንደ ሀገር ነፃነታቸው ተከብሮ በእኩልነት እንዲኖሩ ለማስቻል የተቋቋመ የሙስሊሞች አባት ተቋም ነው። ስለሆነም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ያለውን የመብት ጥሰት በመዘርዘር፤ መጅሊሱ እስካሁን ድረስ መፍትሔ ሊያመጣ ያልቻለበትን ምክንያት በመጠየቅ፤ አፋጣኝ ምላሽ እና መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ባለመሰራቱ የደረሰባቸውን ቅሬታ በጥልቀት በማስረዳት ከመጅሊሱ ጋር የነበራቸው ውይይት አጠናቀዋል።
በሂደቱም መጅሊሱ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በጥልቀት እንዲያዳምጥ እና እንዲገመግም፤ የዩኒቨርስቲውን አመራሮች በሕግ አግባብ ተጠያቂ እንዲያደርግ እና ዘላቂ መፍትሔ እስኪመጣ ድረስ በቁርጠኝነት እንዲሰራ ጠይቀዋል።
የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ የሙስሊሙ ተቋማት፤ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ብሎም የሁሉም ፍትሕ ፈላጊ ሰው ሁሉ ጥያቄ ነው። ዘላቂ መፍትሔ በማምጣት ሁሉም ተማሪ በተመቻቸ ከባቢ ውስጥ ተምሮ ለሀገር የሚኖረው አበርክቶ እንዲያይል በማድረግ ረግድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስቸኳይ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ እንዲተጉ ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ _ የተበደሉት እስኪካሱ _ በዳዮች ተጠያቂ እስኪደረጉ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
