5killo Jem'a official Channel
Відкрити в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Показати більше1 160
Підписники
-124 години
+27 днів
-130 днів
Архів дописів
السلام عليكم ورحمت الله وبركاته
ነገ የሸዋል ፆም ይጀመራል። የሸዋል ፆም ማለት ለፈርድ ሰላት ሱና እንደምንሰግደው ከፈርድ ፆም በኋላ ያለ ሱና ፆም ነው።
❇️የሸዋልን ፆም መፆም የፈለገ መጀመሪያ የረመዷን ቀዷዕን መጨረስ አለበት።(ይወደዳል)
💥 ምክንያቱም ሀዲሱ የሚለው من صام رمضان ثم اتبع ست من شوال(ረመዷንን የፆመ ከዛ የሸዋልን 6 ቀን የፆመ) ነው የሚለው
🌐ስለዚህ ቀዷ ያለበት ሰው ረመዷንን ስላልፆመ ቀዷን ይጨርስ
💠 ምንዳው ደግሞ ረመዷንን ፁሞ የሸዋልን 6 ቀን ያስከተለ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው። ምክንያቱም ይህ ሰው 36 ቀን ፁሟል 1 ሀሰና ደግሞ በ10 ነው ሚባዛው ስለዚህ 360 ቀን እንደፆመ ይቆጠራል።
❇️ ሰውየው 6ቀን ፆም ከፈለገ አከታትሎ ከፈለገ ለያይቶ በሸዋል ወር ብቻ ይፁመው ፤ ነገር ግን በላጩ አከታትሎ ከኢድ በኋላ ቢፆመው በላጭ ነው።
⚜️ ከዛ በተረፈ ፆሙን ሁሉም ነው የሚፆመው አንዳንድ ቦታ 40 አመት ካልሞላ አይፆምም የሚባለው መሰረተ ቢስ ወሬ ነው።
❇️ ከዛ በተረፈ ሸወሊድ(የሸዋል ኢድ) ወይም ትንሹ ኢድ የሚባል ቅራቅንቦ እስልምናን አይወክልም።
(ኢብን አቢ ዱንያ ፡ ሸዋል 1/1447)
Repost from AAU - Muslim Students Union
+3
ካደጉበት ማህበረሰብ ሲኖሩ ሲማሩ ሲሰሩ ማንነታቸው እንደተጠበቀ፣ ክብራቸው ከቦታው እንደሆነ ብሎም እምነት ባህላቸው እንደተከበረ ነው። ሆኖም ትልቅ ሕልምን ሰንቀው ከዩኒቨርሲቱ ደጅ ሲደርሱ "እምነታችሁን፣ ባህላችሁን እና ማንነታችሁን ካላወለቃችሁ ከዩኒቨርሲቱ አትገቡም።" የሚል መመሪያ ሊጠብቃቸው ተሰናድቷል። "ጥያቄ አለን!" እያልን ያለነውም ይህንን ሕልም አምካኝ መመሪያ ነው። የልጆቻችን ውጥን በእነርሱ ኢ- ሕገመንግስታዊ መመሪያ ሊበላሽ አይገባም። ከታች ጀምረን ሁሉን ተረድተው የተሻለን ነገር ይጠይቁ ዘንድ ማስተማር ግዴታችን ነው። እኛ ባለፍንበት እነርሱ እንዳያልፉ መትጋት ግዴታችን ቢሆንም የተሻለን ያውቁ ዘንድ ያለፍንበትን እያወቁ ይጓዙ ዘንድ ግዴታ ሆኗል።
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥያቄ አለን _ ስለ ሰብዓዊ መብቶቻችን __ ስለ ሒጃባችን ጥያቄ አለን !!!
ምስል፦ ከማዕከላዊ ኢትዮጲያዋ ወለኔ
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
በ1966 ሚያዚያ ወር ውስጥ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች "የአንድነት መሠረቱ እኩልነት ነው። እኩልነት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ!" የሚልን መፈክር ይዘው "ኢትዮጵያ የሁላችን
እኩል ይሁን መብታችን
እንድንሰራ ላገራችን!"
የሚልን ግጥም በአንድነት እያሉ ስለ ሐይማኖት ነፃነት፤ ስለ ሐይማኖት እኩልነት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት በአደባባይ ጠይቀው ነበር። ትግላቸውም ፍሬ አፍርቶ ሴኩላር የሆነ ሕገ-መንግስት እንዲኖር አድርገዋል። ከደርግ መውደቅ ቡሃላ ሕዝበ ሙስሊሙ በነበረው ተሳትፎ "የሐይማኖት እኩልነት! የሐይማኖት ነፃነት!! ሴኩላሪዝም!!! የመማር መብት!!" የሚሉ ድንጋጌዎች ከሕገ- መንግስቱ ሲካተቱ ከሁሉ ቀድመው ከመድረክ ወጥው ደስታቸውን የገለፁት ከወደ ባሌ የመጡ ሸይኽ ነበሩ። ለምን ከተባለ ድንጋጌዎቹ ሙስሊሙ ተማሪ በነፃነት እንዲማር ሰራተኛውም በነፃነት እንዲሰራ ያስችላል ብለው ስላሰቡ ነው።
ጥያቄያችን የትላንቱ ትውልድ አደራ ነው ስንልም ለዚህ ነው። በምስሉ ላይ የሚታዩት የነገ ፍሬዎች "ጥያቄ አለን!" የሚልን መፈክር የያዙት የነገ ተስፋቸው እንዳይጨልም ነው። ጥያቄያችን የልጆቻችን እጣፋንታ ነው የምንለውም ለዚያ ነው።
የትላንቱን አደራ እና የነገውን ተስፋ ወደ ፍትሐዊ እውነታ የመቀየር ሀላፊነት ደግሞ የዚህ ትውልድ አደራ ነው። ድምፃችንን ከፍ አድርገን መልዕክታችንን ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ የማድረስ ግዴታ አለብን።
ምስል፦ ከኦሮምያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ የተላከ
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
የዒድ ስጦታ የሚያሸልም ጥያቄ!
ከላይ ያሉት ሁለት ምስሎች ትርጉም ምንድን ነው? የመጀመሪያው ፊትን መሸፈን ያለበት ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጀርባ መስጠት ያለበት ነው። በደንብ ለገለፀ ለተማሪ ጥሩ የሆነን ሽልማት ይሰጠዋል።
መልሳችሁን @Aaumuslimstudentsunion1 ላኩልን።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
የኢድ ድምቀቶቻችን !
ዩኒቨርሰቲያችን (AAU) መጪው ትውልድ ሒጃብ (ኒቃብ) ለብሶ እንዳይማር የሚያስችል መመሪያን አወጣ። እኛ ደግሞ መጪውን ትውልድ "ጥያቄ አለን!" እያለ እንዲያድግ አደረግን። ሆኖም ግን በአላህ ፈቃድ እነዚህ ሕፃናት ስለ ሒጃብ (ኒቃብ) አይጠይቁም። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄን የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ወስዷል። በአላህ ፈቃድ ፍትሕ በቅርቡ ይሰፍናል።
ኢዱኩም ሙባረክ !!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+3
ቻሌንጅ 3 _ ለቲክቫህ፣ ATC News እና ሌሎችም !
ሚዲያ መልካም ላይ ከዋለ ለማህበረሰብ ለውጥ፣ ለመብት መከበር እና ለፍትሕ መስፈን አስተዋፅዖ አለው። ቲክቫህ ከዚህ በፊት ድምፃችንን ሲናሰማ ሲያስተጋባልን የነበረ ግዙፍ ሚዲያ ነው። ATC Newsም በትምህርት ዘርፉ መረጃ በመስጠት እና ለተማሪዎች ድምፅ በመሆን የሚታወቅ ሚዲያ ነው።
እኛም እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየደረሰብን ስላለብን የመብት ጥሰት፣ ሰብዓዊ መብታችንን ስለሚጥሰው መመሪያ እና እየታገልንለት ስላለው ፍትሕ ድምፅ እንዲሆኑን እንሻለን። ስለሆነም፦
ኒቃቢስቶች፦ ስለደረሰባችሁ የመብት ጥሰት በዝርዝር በመፃፍ ድምፅ እንዲሆኗችሁ ጠይቋቸው።
ተማሪዎች፦ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ እንዲሆኑ አስታውሷቸው።
ይህንን ቻሌንጅ የፍትሕ መታወቂያ በሆኑት ታላቁ ኡመር ሰይመናዋል። የኡመር ልጆች ሆይ፦ ድምፃችሁን አሰሙ።
ለATC New፦ @mujaabot ላኩላቸው።
ለቲክቫህ፦ @tikvahethiopiaDM ላኩላቸው።
የምንፈልገው ዩኒቨርሲቲው እየፈፀመው ስላለው በደል ድምፅ እንዲሆኑን ነው። የምንፈልገው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የውይይት በርን ዘግተው ተማሪዎችን መበደልን ለምን እንደመረጡ በግልፅ እንዲጠይቁልንና ምላሹን እንዲያሰሙን ነው።
እናድርገው _ በትብብር በቅንጅት በአንድነት!
ያሰፈራችሁትን መልዕክት screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
Repost from 6 Kilo Muslim Students' Jeme'ah Official Channel
+3
ቻሌንጅ 3 _ ለቲክቫህ፣ ATC News እና ሌሎችም !
ሚዲያ መልካም ላይ ከዋለ ለማህበረሰብ ለውጥ፣ ለመብት መከበር እና ለፍትሕ መስፈን አስተዋፅዖ አለው። ቲክቫህ ከዚህ በፊት ድምፃችንን ሲናሰማ ሲያስተጋባልን የነበረ ግዙፍ ሚዲያ ነው። ATC Newsም በትምህርት ዘርፉ መረጃ በመስጠት እና ለተማሪዎች ድምፅ በመሆን የሚታወቅ ሚዲያ ነው።
እኛም እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየደረሰብን ስላለብን የመብት ጥሰት፣ ሰብዓዊ መብታችንን ስለሚጥሰው መመሪያ እና እየታገልንለት ስላለው ፍትሕ ድምፅ እንዲሆኑን እንሻለን። ስለሆነም፦
ኒቃቢስቶች፦ ስለደረሰባችሁ የመብት ጥሰት በዝርዝር በመፃፍ ድምፅ እንዲሆኗችሁ ጠይቋቸው።
ተማሪዎች፦ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ እንዲሆኑ አስታውሷቸው።
ይህንን ቻሌንጅ የፍትሕ መታወቂያ በሆኑት ታላቁ ኡመር ሰይመናዋል። የኡመር ልጆች ሆይ፦ ድምፃችሁን አሰሙ።
ለATC New፦ @mujaabot ላኩላቸው።
ለቲክቫህ፦ @tikvahethiopiaDM ላኩላቸው።
የምንፈልገው ዩኒቨርሲቲው እየፈፀመው ስላለው በደል ድምፅ እንዲሆኑን ነው። የምንፈልገው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የውይይት በርን ዘግተው ተማሪዎችን መበደልን ለምን እንደመረጡ በግልፅ እንዲጠይቁልንና ምላሹን እንዲያሰሙን ነው።
እናድርገው _ በትብብር በቅንጅት በአንድነት!
ያሰፈራችሁትን መልዕክት screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
©aaumsu
@AAU6kilojemea
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
ዝግጁ !!!
ዒድን በየአደባባዩ ወጥተን በጋራ እንሰግድ ዘንድ ለደነገገልን አላህ ምስጋና ይድረስ። አብረን ስንቆም ያለውን ውበት አሳየን፤ በዝተን ለጌታችን ስንሰግድ ያለውን ድምቀት መሰከርን፤ በጋራ "አላሁ አክበር!" ስንል ያለውን ተፅዕኖ ተረዳን። ያላንዳች ምክንያት በአደባባይ ወጥተን እንድንሰግድ አልተደነገገም። ስትሰሰቡ፣ ለጋራ አላማ _ በተመሳሳይ አቅጣጫ _ መስመራችሁን ጠብቃችሁ _ ድምፃችሁ ሲስተጋባ ውበትም ተፅዕኖም አለው ከሚታዩ ትርጉሞች መካከል ነው።
ስለ መብታችን መታገል ከጀመርን ሰነባበትን። ሕብረታችን አንድነታችን ትብብራችን ጉልበታችን ነው። በጋራ የምናሰማው ድምፅ ተፅዕኖ መፍጠሪያ መሳሪያችን ነው።
ስለ መብታችን ለመናገር አናፍርም አንፈራም፤ ስለ ነፃነታችን መሞገት የክብራችን መገለጫ ነው፤ የእኛ የሆነው ከእኛ እስኪሆን ድምፃችንን እናሰማለን። በቢሮ ውስጥም በአደባባይም፤ በሚዲያም በአካልም ጥያቄ አለን እንላለን።
ዝግጅ ነሽ እህቴ? ዝግጁ ነህ ወንድሜ? ዝግጁ ናችሁ ያኡመተ ሙሐመድ?
ኢዱኩም ሙባረክ !!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ጥያቄያችን ያለፈው ትውልድ ጥያቄ መሙያ፤ የዛሬው ትውልድ መብት መመለሻ ብሎም የነገው ትውልድ ነፃነት መረጋገጫ ነው። ለዚህም ነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጨቋኝ መመሪያ ያለፉት ትላልቆች፤ የዛሬ ወጣቶች እና የነገ ተስፋ ሕፃናት ጥያቄ የሆነው።
ለዚህም ነው ሕፃናት ጭምር የኢድ ፊኛቸው ላይ ጥያቄ አለን እያሉ ያሉት። ለዚህም ነው አዛውንቱ ጭምር ስለኛ የሚጠይቁት። ለዚህም ነው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ጥያቄ አለን የሚለው።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
ዒዱኩም ሙባረክ !!
ፎቶ፦ በዛሬ ኢድ ከአዲስ አበባ ሕፃናት የተላከልን
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
ቻሌንጅ 2 _ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ !
መብታችንን የሚጥስ መመሪያ ከማውጣት ጀምሮ በእህት ወንድሞቻችን ላይ ብዙ በደሎችን ፈፅሟል። መፍትሔ ይምጣ ተብሎ ለውይይት ሲጠየቅም እምቢኝ በማለት ጆሮ ዳባ ልበስ ካለ ከራርሟል። ፌስቡኩኑም ቢሮውንም ለሐሳብ ዝግ ቢያደርግም መንገዱን ፈልገን ድምፃችንን ማሰማት ታሪካዊ ሀላፊነታችን ነው።
የመጀመሪያው ምስል ላይ የዩኒቨርሲቲውን ሕንፃዎች ውበት የሚያሳይ ሲሆን ከአስተያየቶች መካከል " ካሜራው ትንሽ ዝቅ ቢል ለመብታቸው እየታገሉ ያሉ ብዙ ተማሪዎች አሉ። መብታችንን ባታከብሩ እንኳ ድምፃችንን ማፈን አትችሉም።" - የሚል ታሪካዊ መልዕክት ተቀምጧል።
ሁላችንም ወደዚያ በመግባት ድምፃችንን እናሰማ!
በደል የደረሰባችሁ ተማሪዎች በደላችሁን በዝርዝር አስቀምጡላቸው!!
ሁላችሁም ስለ ነፃነት፤ ፍትሕ እና እኩልነት በአንድነት ጠይቋቸው።
በ https://www.facebook.com/100064311447035/posts/1365127555640946/?app=fbl በመግባት ያሰፈራችሁትን መልዕክት screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+3
ቻሌንጅ 2 _ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ !
መብታችንን የሚጥስ መመሪያ ከማውጣት ጀምሮ በእህት ወንድሞቻችን ላይ ብዙ በደሎችን ፈፅሟል። መፍትሔ ይምጣ ተብሎ ለውይይት ሲጠየቅም እምቢኝ በማለት ጆሮ ዳባ ልበስ ካለ ከራርሟል። ፌስቡኩኑም ቢሮውንም ለሐሳብ ዝግ ቢያደርግም መንገዱን ፈልገን ድምፃችንን ማሰማት ታሪካዊ ሀላፊነታችን ነው።
የመጀመሪያው ምስል ላይ የዩኒቨርሲቲውን ሕንፃዎች ውበት የሚያሳይ ሲሆን ከአስተያየቶች መካከል " ካሜራው ትንሽ ዝቅ ቢል ለመብታቸው እየታገሉ ያሉ ብዙ ተማሪዎች አሉ። መብታችንን ባታከብሩ እንኳ ድምፃችንን ማፈን አትችሉም።" - የሚል ታሪካዊ መልዕክት ተቀምጧል።
ሁላችንም ወደዚያ በመግባት ድምፃችንን እናሰማ!
በደል የደረሰባችሁ ተማሪዎች በደላችሁን በዝርዝር አስቀምጡላቸው!!
ሁላችሁም ስለ ነፃነት፤ ፍትሕ እና እኩልነት በአንድነት ጠይቋቸው።
በ https://www.facebook.com/100064311447035/posts/1365127555640946/?app=fbl በመግባት ያሰፈራችሁትን መልዕክት screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ሳምንቱን የሗሊት _ ሐሙስ ምሽት !
የራበን ፍትሕ እንጂ ዳቦ አይደለም
የጠማን ነፃነት እንጂ ውሃ አይደለም
በፍትሕ እንጂ በቁራሽ ምግብ የሚገለፅ ክብር የለም
በማለት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ምሽት "ጥያቄ አለን!" በማለት ለሚዲያ ፍጆታ ከተዘጋጀ ኢፍጣር ተገኝተው ድምፃቸውን አሰምተው ነበር _ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ እንቁ ሴቶች።
በሰዓቱ ድምፃቸውን በአደባባይ በሕብረት በማሰማት ታሪክ ሰርተው አልፈዋል። አሁን ደግሞ ሀላፊነቱ ወደ ሁላችንም መጥቷል። በዲጂታሉ መድረክ "ጥያቄ አለን!" በማለት እየደረሰብን ያለውን የፍትሕ እጦት የምናሰማበት ጊዜ ነው። የተባበረ ስብስብ፤ የተቀናጀ ድምፅ፤ ለፍትሕ የቆመ ስብዕና፤ በአንድነት የሚስተጋባ ጩኸት ተፅዕኖ መፍጠሩ የማይታበል ነው።
እናድርገው _ በትብብር በቅንጅት በአንድነት!
ዝግጁ ናችሁ? ዝግጁ ነሽ? ዝግጁ ነህ?
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ለመላው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሂ የኢደል-ፊጥር አመት በዓል በሰላም አደረሳቹ!!
በበዓሉ ያጣናቸው መብቶች ይመለሱ ዘንድ፤ የሙስሊም ተማሪዎች የነፃነት ጥያቄዎች መፍትሔ ያገኙ ዘንድ ዱዓ አድርጉ። እርሰ በዕርስ መዘያየርን አብዙ። ከቤተሰብ ተነጥለው ብቻቸውን የሚያሳልፉ አሉና በአብሮነት በድምቀት ታሳልፉ ዘንድ አደራችን ነው።
───────⊱◈◈◈⊰────────
عِيدٌ مُبَارَكٌ💫
🎊تَقَبَّلَ اللَّهُ مِنَّا وَمِنۡكُمۡ صَالِحَ الأَعۡمَال🎉🎉
كل عام وأنتم بخير 🌙✨
───────⊱◈◈◈⊰────────
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+6
ቻሌንጅ 1 _ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር !
ሚኒስትሯ ሻሽ ለብሰው ሒጃብ (ኒቃብ) የለበሱ ሴቶች ባሉበት የኢፍጣር መርሐግብር እንደተዘጋጀ በፌስቡክ ገፃቸው አሳውቀዋል። ይህ የሄዱበትን ከማክበር ስለሆነ ክብር ቢገባቸውም በሒጃባችን ምክንያት በደል እየደረሰብን ነው በማለት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ደጅ ሲመላለሱ ለነበሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ምላሽ አለመስጠታቸው ተቃርኖ ይፈጥራል። ስለ ሙስሊም ሴቶች መብት ስለምን ዝም አሉ? በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ስለምን ዝም አሉ? ቢሮ ሄደን ምላሽ አልሰጡምና በአደባባይ መጠየቅ ገዴታ ሆኗል።
ስለደረሰባችሁ የመብት ጥሰት በዝርዝር ፃፉላቸው
እያሳለፋችሁት ስላለው መገፋት እና በደል ፃፉላቸው
እነርሱ ሲበድሉን ያላፈሩትን እኛ ስለመብታችን ለመጠየቅ፤ ለመናገር፤ ጠበቃ ለመሆን አናፍርም።
የተያያዘው ምስል ላይ ቀድመው የፃፉ ወንድም እህቶች መልዕክት አለ። የእናንተንም ፃፉና https://www.facebook.com/100069070785075/posts/1255792020066479/?app=fbl በዚህ ከላካችሁላቸው ቡሃላ screenshot አድርጋችሁ @Niqab_issueBot ላኩልን።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ዝግጁ ናችሁ ወይ? ስለ መብታችሁ ለመጠየቅ ... ስለ ነፃነታችሁ ለመሞገት ... የእናንተ ስለሆነው ለመናገር ዝግጁ ናችሁ ወይ? ከሆናችሁ 👍 ምልክት አሳዩንን ወደ ተግባር እንግባ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሐሳብ መስጫ ሳጥኑን ዘግቷል !!!
ስለ ሐሳብ ነፃነት ያስተማረን ግቢ የመብት እና ግዴታን ሀ ሁ የቆጠርንበት የልሕቀት ማዕከል
የሰብዓዊ መብት ምንነት ያስረዳን ካምፓስ
ለነፃነታችን መቆም፤ ሰለ እኩልነት መጠየቅ፤ ስለ አካታችነት መታገል እንዳለብን ያስተማረን ዩኒቨርሲቲ
ተማሪዎች ሐሳብ ይሰጣሉ በሚል ፍራቻ የሐሳብ መስጫ ሳጥኑን ዘግቷል። ይህ ለተቋማችን ትልቅ ስላቅ ነው። የፌስቡክ ኮሜንት box ስለተዘጋ የሚታፈን ድምፅ የለም።
አክብራችሁ "ለበዓልህ እንኳን አደረሰህ!" ያላችሁትን ተማሪ የእውነት የምታከብሩት ከሆነ ድምፁን ስሙ፤ ሐሳቡን አድምጡ፤ አወያዩት፤ ለጥያቄውም መልስ ስጡ፤ መብቱንም አክብሩ። ከማክበር መከበርን ብታገኙ እንጂ የምታጡት ነገር አይኖርም።
ጥያቄ አለን: ዛሬም ነገም!
ጥያቄ አለን: ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!!
ጥያቄ አለን: ቢሮ ውስጥም በአደባባይም!
@aaumsu
👋👋 አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ👋👋
👉የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከ አህለል ኸይራት ያገኙትን ለተማሪዎች የሚከፋፈል ተምር የሰጡን ሲሆን እንደ 5 ኪሎ ጀምዓ የደረሰንን ኮታ ኢንሻአላህ ዛሬ 4 ኪሎ መስጂድ እስከ 12:00 ባለው ወቅት ለተማሪዎች ስለሚሰጥ መገኘት የምትችሉ ተገኝታችሁ እንድትወስዱ ስንል ለማሳወቅ እንወዳለን።
👉ግቢ የሌላችሁ እና ያልተገኛችሁ ተማሪዎች ኢንሻአላህ ከኢድ በኅላ ሻዋል ላይ የምሰጥ ይሆናል።
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
ካላወቁ፦
ተገላልጦ መማር መብት በሆነበት ሀገር ሰውነትን ሸፍኖ መማር በመመሪያ የሚከለከልበት ምክንያት አይኖርም።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያወጣውን ጨቋኝ መመሪያ ስንቃወም የነበረው ከመፅደቁ በፊት በረቂቅነት ደረጃ ካለበት ጀምሮ ነበር። መመሪያው የፀደቀው ጥቅምት 2017 ዓ.ል ቢሆንም መስከረም ወር ውስጥ ተማሪዎች ግቢ እንደገቡ የተማሪዎችን ሐሳብ ሳይቀበሉ ኦረንቴሽን በሚል ከቨር ለተማሪዎች በትዕዛዝ መልክ አስተላለፉ። ሆኖም ተማሪዎች ከዚያው ከመድረክ "ጥያቄ አለን!" በማለት አስተጋቡ። አመራሮቹ ግን መልስ ከመስጠት ይልቅ የተማሪዎቹን የጥያቄ አለን ማብራሪያ ስጡን ጩኸት በመሸሽ ወደ ቢሯቸው አመሩ። ተማሪዎቹም እንደተሰባሰቡ ከቢሯቸው ሄዱ። በሰዓቱ ለአሁን በረቂቅነት ደረጃ ያለ መመሪያ ስለሆነ መፍትሔ ይመጣል በውይይት እናድርገው ብለው ቃል የገቡ ቢሆንም ቃላቸውን አጥፈው መመሪያውን በማፅደቅ ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳሉ እስስካሁን አሉ።
ተማሪውም ሳይሰለች ሳያፍር ሳይፈራ እስካሁን አለ። አመት ከመንፈቅ ቢሞላም "ጥያቄ አለን!" የሚለው መፈክር ሳይደበዝዝ እስካሁን አለ። ተማሪዎች በሚዲያ፣ ቢሮ ውስጥ፣ በአደባባይ ጥያቄ አለን እያሉ እስካሁን አሉ። ፍትሐዊ መልስ መጥቶ ገፊ መግፋቱን እስኪያቆም፤ በዳይም በደሉን እስኪገታ ድረስ ጥያቄው ይቀጥላል።
አይደለም ወይ?
እኛ የምንሰለች ትውልድ አይደለንም። የጀመርነውን ጥያቄ ከግብ ሳናደርስ የምናቆምበት ምክንያትም ሆነ ሁኔታ አይኖርም።
ቪድዮ፦ ረቡዕ መስከረም 15 / 2017 ጨቋኙ መመሪያ በረቂቅነት ሳለ ለ5ኪሎ ተማሪዎች ትዕዛዝ ሲተላለፍ እና ተማሪዎችም ጥያቄ አለን ሲሉ የተቀረፀ
@aaumsu
