5killo Jem'a official Channel
Відкрити в Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Показати більше1 159
Підписники
-124 години
Немає даних7 днів
-130 день
Архів дописів
"እንዴት እንዲህ ታደርጋላችሁ? ዋጋ ትከፍያለሽ እያንዳንድሽ። ወንድ አይደለሁም።" - የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የምርመራ ክፍል ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ጌታሁን ዳዲ
ሙስሊም ተማሪዎች ከ21 ቀናት በፊት በፋና ዋና ፅ/ቤት በመገኘት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እያደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት የሚዲያ ሽፋን ይሰጣቸው ዘንድ ጠይቀው ከሚዲያው የምርመራ ክፍል ዳይሬክተር ጌታሁን ዳዲ አዎንታዊ መልስ አጊኝተው ነበር። ሆኖም ምላሸ ከሰጡ ከ14 ቀናት ቡሃላ ውጤት ሲጠየቁ "የፌደራል መጅሊስን ሄጄ ስጠይቅ የተከለከላችሁት ሒጃብ (ኒቃብ) ለትርፍ ፅድቅ እንደሆነ ገልፆልኛል። ዩኒቨርስቲው መመሪያ በትምህርት ሚኒስቴር የፀደቀ ስለሆነ አላሻሽልም ብሏል። እኛም እንደ ሚዲያ ለጥቂቶች ስንል የሚዲያ ሽፋን አንሰጥም።" - በማለት መልሰው ነበር። ይህንን ምላሽ ጀመዓው ለተማሪዎቹ ካሳወቀ ቡሃላ ግን ከአንድ የሚዲያ ባለሙያ የማይጠበቀን የማስፈራሪያ ይዘት ያለውን መልዕክት ለተማሪዎች በመደወል አሳውቀዋል። በመልዕክታቸውም "እንዴት እንዲህ ታደርጋላችሁ? ዋጋ ትከፍያለሽ እያንዳንድሽ። ወንድ አይደለሁም።" በማለት ለማስፈራራት ሞክረዋል።
ይህ አግባብነት የሌለው ተግባር ነው። ሚዲያው ዳይሬክተሩ ባሉት ንግግር ላይ ያለውን አቋም እንዲያሳውቅ፤ ማብራሪያ እንዲሰጥ እና በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው በደል የሚዲያ ሽፋን እንዲሰጥ ዳግም እንጠይቃለን። መጅሊስም ስለተባለው የመጅሊስ አካል እና ስለሚዲያው አቋሙን እንዲያሳውቅ፤ የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ በዘላቂነት እንዲሰራ በአላህ ስም እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
💥 ደርስ ማስታወሻ :::::::::::::::::::::::
🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋
✅ ኢንሻአላህ ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል ::
📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ
⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ
🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ማክሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ። 6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል ቡዙ እናተርፍለን።
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
"የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው"
⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ
🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/durus_at_aqsa
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934
@fivekjemaa
🔈 Applied Mathematics I Tutorial Announcement🔈
Based on the poll results, the majority of freshmen have chosen Thursday for the Applied Mathematics I tutorial.
🗓 Day: Thursday, April 23, 2026.
⏰ Time: 10:20 LT
📍 Venue: To be announced
This session is prepared to support you in strengthening your understanding and building confidence in the course.
Come prepared, bring your questions, and make the most out of this opportunity!
May Allah put barakah in our time and knowledge.
©Academic sector
የአዲስ አበባ መጅሊስ ጠቅላላ ጉባዔ በዛሬው እለት ይጠናቀቃል።
፨ ለ19 ወራት ያክል መሐል አዲስ አበባ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሒጃብን (ኒቃብ) የሚከለክል መመሪያ አውጥቶ ሲያንገላታቸው ስለነበሩ ሙስሊም ተማሪዎች ምን ይል ይሆን? ጨቋኙ መመሪያ ይሻሻል ዘንድ ምን አይነት አቅጣጫዎችን ያስቀምጥ ይሆን? ተማሪዎችን ሙስሊም ስለሆኑ ብቻ እንግልት የፈፀሙ የተሳደቡ ያዋረዱ አካላትን በሕግ አግባብ ይጠይቁ ይሆን?
ጥያቄያችን እንዳለ ነው _ መልስ አላገኘንም _ መልስ እንፈልጋለን _ ያልተድበሰበሰ መልስ _ ፍትሐዊ መልስ እንፈልጋለን ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
💫የላቀ ምንዳ!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿من قال إذا أصبح: لا إله إلا اللهُ وحده لا شريك له، له الملكُ وله الحمدُ، وهو على كلِّ شيءٍ قديرٌ، كان له عِدلُ رقبةٍ، من ولد إسماعيلَ، وكُتِبَتْ له بها عشرُ حسناتٍ، وحَطَّ عنه بها عشرَ سيِّئاتٍ، ورَفع له بها عشرَ درجاتٍ، وكان في حِرْزٍ من الشيطانِ حتى يُمسيَ، وإذا قالها إذا أمسى كان له مثلُ ذلك حتى يُصبِحَ﴾
“በጠዋቱ ክፍለ ግዜ እንዲህ ያለ፦ ‘ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አንድ ነው፡፡ ሸሪክ የለውም። ስልጣን የርሱ ብቻ ነው። ምስጋናም የሚገባው ለርሱ ብቻ ነው። እርሱ በማናቸውም ነገር ላይ ቻይ ነው።’ ከእስማኤል ዘር የሆኑ አስር ባሪያዎች ነፃ እንዳወጣ ይቆጠርለታል፣ አስር ሀሰናት (ምንዳዎች) ይመዘገብለታል፣ አስር ኃጢያቶች ይሰረዝለታል፣ በአስር ደረጃው ከፍ ይደረጋል፣ እስኪመሽ ድረስ ከሸይጣን ምሽግ (ጥበቃ) ይደረግለታል። ይህንኑ በምሽቱ ክፍለ ግዜ ካለ ደግሞ እስኪነጋ ድረስ ከላይ ያለው ተመሳሳይ ይደረግለታል።”
📚ሶሂህ አልጃሚ፡ 6418
+1
የወልዲያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የእኛም ነው በማለት የአቋም መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው መፍትሔ ይመጣ ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ የተቀመጠ ሲሆን አንብቡት። የጥቂቶች ጥያቄ ነው ላሉት አካላትም ላኩላቸው። ከጀሰዲን ዋሂድ ይሉት ይህ ነው። በሐረማያ ጀመረ _ ወራቤ ተከተለ _ ከማሌዢያ ያሉ እንቁ እህቶቻችን ተከተሉ _ ወልዲያዎችም መጡ።
ጥያቄው የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነው ያልነውም ለዚህ ነው።
ጥያቄው የእኔ ነው!
ጥያቄው የእኛ ነው!!
ጥያቄው የሁላችንም ነው!!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
"የኒቃብ ጉዳይ በዘላቂነት ይፈታ ዘንድ ስንት ተማሪ መባረር አለበት? ስንት እህት ማልቀስ አለበት? በቃ ሊባል ይገባል።"
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ኒቃቢስቶች በዩኒቨርስቲው የደረሰባቸውን ግፍ ከመጀመሪያው ቀን እስከ ዛሬ አስቀምጠዋል። https://vt.tiktok.com/ZS91ujBSR/ በመግባት ተመልከቱ። ለሌሎችም አሰራጩ። ሙሉው የሚለቀቅ ይሆናል።
ይህ እንባ ሊታበስ ይገባል። ጥያቄያችን የፍትሕ ነው። ጥያቄያችን ይህ በደል ይቁም ነው። ጥያቄያችን የሴት ልጆቻችን እንባ ይቁም ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ።
@aaumsu
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ _ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት !
መሬት ላይ ያለ እውነታ በሚዲያ ጋጋታ አይሸፈንም። በመመሪያ ደረጃ ሙስሊም ተማሪዎችን የሚያገል ድንጋጌ ካወጡ ቡሃላ የሁሉም ኢትዮጵዬዊ ቤት ብሎ መፃፍ ስላቅ ነው።
እውነታውን ንገሯቸው። https://www.facebook.com/100064311447035/posts/1392178756269159/?app=fbl በመግባት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየተፈፀመ ያለውን የመብት ጥሰት አጋልጡ። ይህ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
✨ኢስላማዊ የስ‐ነምግባር እሴቶች!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إيّاكُمْ والظَّنَّ، فإنَّ الظَّنَّ أكْذَبُ الحَديثِ، ولا تَحَسَّسُوا، ولا تَجَسَّسُوا، ولا تَنافَسُوا، ولا تَحاسَدُوا، ولا تَباغَضُوا، ولا تَدابَرُوا، وكُونُوا عِبادَ اللهِ إخْوانًا﴾
“ጥርጣሬን ተጠንቀቁ። ምክንያቱም ጥርጣሬ ከቅጥፈቶች ሁሉ የላቀው ነውና። ወሬ አነፍናፊ አትሁኑ፣ የሌላውን ነውር ተከታታይ አትሁኑ፣ እርስ በርስ ተጨቃጫቂ አትሁኑ፣ አትመቀኛኙ፣ አትጠላሉ፣ ጀርባ አትሰጣጡ። ወንድማማች የአላህ ባሪያ ሁኑ።”
📚 ቡኻሪ (5143) ሙስሊም (2563) ዘግበውታል
🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ። 6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል ቡዙ እናተርፍለን።
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
"የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው"
⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ
🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/durus_at_aqsa
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934
@fivekjemaa
+1
በማሌዢያ የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች "The Question is ours too - ጥያቄው የእኛም ነው። We have a Question - ጥያቄ አለን። We want an answer - መልስ እንፈልጋለን። Justice For Addis Ababa University Muslim Students - ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በማለት በሙስሊምነታቸው ሳቢያ እየተጨቆኑ ላሉ ሙስሊም ተማሪዎች አጋርነታቸውን አሳይተዋል። ጥያቄው የጥቂቶች ነው ሲሉ ለነበሩት ይህንን ላኩላቸው። ጥያቄው በሀገር ውስጥ የሚማረውም ሆነ በውጭ ሀገር የሚማረው ኢትዮጵያዊ ጭምር ነው። ጥያቄው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ያሉ ሙስሊሞች ጥያቄ ነው። ጥያቄው በሰብዓዊ መብቶች የሚያምን የሰው ዘር በሙሉ ነው።
እነርሱ እንዳሉት ፦
Open doors to every student _ በሩን ለሁሉም ተማሪዎች እኩል ክፈቱ!
No student should be denied education _ አንድም ተማሪ ከትምህርት መታገድ የለበትም!
Respect Beliefs. Protect Education _ እምነትን አክብሩ ትምህርትንም ጠብቁ!
ጥያቄው የእኛም ነው!
ጥያቄው የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ነው!
ጥያቄው ሰብዓዊነት ለሚገደው ሁሉ ነው!!!
ጥያቄ አለን _ መልስ እንፈልጋለን ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
ያልተደፈረው ሲደፈር፤ ቀኑ ሚያዝያ 12 ነበር- 1966 ዓ.ል!
የታሪክ ጸሐፊያን "ግዙፉ ሰላማዊ ሰልፍ" ሲሉ ያሞካሹታል፤ 'ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች' የሚልን ስያሜ ከንጉሡ ያገኙት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከመኖር ባሻገር ያላቸውን በገዢዎች የማይሻር የሀገር ባለቤትነት ያረጋገጡበትን ይህንን ሰልፍ! በዚያች ቀን የእምነት እና የሀገር ፍቅር በልባቸው የተቀጣጠለ ሙስሊሞችና ሌሎችም ከፍትሕ ጎን የቆሙ ኢትዮጵያውያን ታሪክ ዝንትዓለም የሚዘክረውን ገድል ሰሩ! በርግጥም ••• ያልተደፈረውን ደፈሩ! ምድራዊ ስሌት የማይተምነውን የመስዋዕትነት ዋጋ ከፍለው የእምነት እሴቶቻችን ሳይሸራረፉና ማንነታችንን ሳንለቅ ቀና ብለን የምንሄድባትን ውድ ሀገራችንን አስረከቡን። ዝቅ እንዳንል ራቅ አድርገው አኖሩን!!! በዘመኑ የማይታሰበውን አስበው የዘመናችንን ፈተና ከንቱ አደረጉብን! ታዲያ እኛ -የነርሱ ልጆች- ዛሬ እንዴት መብታችንን አሳልፈን እንሰጣለን ተብሎ ይታሰባል?!
በግዳጅ የተጫነብንን ስንቀበል ታይቶ ይታወቃል እንዴ?
የማይሆነውን?!
ከረሳችሁት፦
እንኳን ዛሬ፤ ትላንትም አልፏል!
"ታሪክን አለማወቅ የታሪክን ስሕተት ካለፈው በባሰ መልኩ እንድንደግመው ያደርጋል።" እንዲሉ ትላንትን በደንብ መርምሩት ወገኖቼ። ስሕተቱ እንዳይቀጥል ዘንድ! "ሀገር እንዴትና በማን ቆመች?" "እንዴትስ ቀጠለች?" "የሀገሩ ነገር ማንን ሲገደው ኖረ?" ብላችሁ ጠይቁ። ማንም በአባቱ ስህተት ባይጠየቅም፤ ስህተቱን ማስቀጠል በመፈለጉ ግን በታሪክም፣ በሕግም፣ በህሊናም፣ በሞራልም፣ በአምላክ ዘንድም ተጠያቂ ይሆናል።
አላህ የምንወዳትንና የምንወዳቸው ነብይ (በፍትሐዊነቷ) የሚወዷትን ሀገራችንን ይጠብቅልን።
©aaumsu
@fivekjemaa
+1
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ከ19 ወራት ቡሃላ የመጀመሪያ ንግግራቸውን አድርገዋል። እርሳቸው እንደተናገሩት ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አድርገዋል። የሀሩን ሚዲያ ዘገባ እንደሚያመላክተው ደግሞ ስለጨቋኙ መመሪያ የተናገሩት ነገር የለም።
አሁንም ጥያቄያችን ግልፅ ነው። መጅሊስ ሀላፊነቱን በአግባቡ ይወጣ። የተበደሉ ተማሪዎች አስፈላጊው ካሳ ይሰጣቸው። ጨቋኙ መመሪያ ይሻሻል።
ጥያቄ አለን _ መልስም እንፈልጋለን!!!
©aaumsu
@fivekjemaa
የአዲስ አበባ መጅሊስ ለሁለት ቀናት የሚቆየውን ጠቅላላ ጉባዔ በዛሬው እለት ጀምሯል።
፨ እዚሁ መሐል አዲስ አበባ ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ላለፉት 19 ወራት የመብት ጥሰት ሲደርስባቸው የነበሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ጉዳይ ያነሱ ይሆን? መብታቸው ተጠብቆ ይማሩ ዘንድ ዘላቂ መፍትሔ የሚመጣበትን መንገድ ያስቀምጥ ይሆን? በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የፈፀሙትን በዶክተር ሳሙኤል የሚመራውን አመራር በሕግ አግባብ ይጠይቁ ይሆን? መጅሊስ ኒቃብ ሱና ነው ብሎናል ስላሉት የመንግስት ሚዲያስ ምን ይሉ ይሆን?
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ዩኒቨርስቲው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ባለው የመብት ጥሰት ዙሪያ የፍትሕ ሚኒስቴር አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት እንዲያደርግ ጠየቀ ! ! !
--------------------------------------
ሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል
--------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፍትሕን የሚያጓድል መመሪያ አውጥቶ ለ19 ወራት ያክል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት ሲፈፅም እንደነበር ይታወቃል። ፍትሕ ይሟላ ዘንድም ሙስሊም ተማሪዎች ያለፉትን ጊዜያት በሰላማዊ መንገድ ደጋግመው ለመጠየቅ ቢሞክሩም በዶክተር ሳሙኤል ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የዩኒቨርስቲው አመራር የውይይት በርን ዘግቶ በበደሉ ላይ ቀጥሏል። የፍትሕ ሚኒስቴር የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ እና የዜጎችን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች የማስከበር ያለበት ተቋም እንደመሆኑ አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት አድርጎ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዲያስቆም እና ኢ- ሕግመንግስታዊው መመሪያ እንዲሻሻል አስተዋፅዖ እንዲያደርግ ተጠይቋል።
ጥያቄ አለን _ መልስም እንፈልጋለን !
©aaumsu
@fivekjemaa
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ዩኒቨርስቲው በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ባለው የመብት ጥሰት ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አስቸኳይ የሕግ ጣልቃ ገብነት እንዲያደርግ ጠየቀ ! ! !
--------------------------------------
ሚያዚያ 12 / 2018 ዓ.ል
--------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት በመጋፋት የሐይማኖት ነፃነት መብታቸውን የሚጋፋ መመሪያ አውጥቶ ላለፉት 19 ወራት ተማሪዎችን ለእንግልት እና ለስነ-ልቦና ጫና ሲዳርግ እንደቆየ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ሙስሊም ተማሪዎች የተፈፀመው የመብት ጥሰት ቆሞ ተማሪዎች ነፃነታቸው ተከብሮላቸው ይማሩ ዘንድ ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ቢያደርጉም አሻፈረኝ በማለት ለተማሪዎቹ ቅሬታ ጆሮዳባ ልበስ ብሏል።
የውይይት በር መዘጋቱ የመብት ጥሰቶቹ ተደጋግመው እንዲፈፀሙ መደላድል ከመስጠቱ ባሻገር ተማሪዎችን አላስፈላጊ ለሆኑ ጫናዎች እየዳረገ ነው። ይህ በቶሎ ቆሞ ችግሮች በውይይት ይፈቱም ዘንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዛሬው እለት ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ አስገብቷል። በደብዳቤውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፦
1ኛ፦ የዩኒቨርስቲው አድሏዊ መመሪያ የዜጎችን የመማር መብትና ሕገ- መንግስታዊ ነፃነት በሚፃረር መልኩ የወጣ በመሆኑ፤ በአስቸኳይ እንዲነሳና መመሪያው እንዲሻሻል ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥ።
2ኛ፦ ዩኒቨርስቲው ለደህንነት ፍተሻ ያቀረብናቸውን ዘመናዊ እና ሐይማኖታዊ መብትን የማይጋፉ አማራጮች ተግባራዊ እንዲያደርግ ግፊት እንዲደረግ
3ኛ፦ ኒቃብ ለባሽ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ሳይሰተጓጎሉ እኩልነታቸው ተከብሮ እንዲማሩ ክትትል እንዲደረግ
ተጠይቋል።
ጥያቄ አለን _ መልስ እንፈልጋለን !
©aaumsu
ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ለሁሉም ኢማሞች፣ ዱዓቶች፣ ኡስታዞች እና መሻይኾች መልዕክቱን አድርሱልን _ የመጪውን ጁምዓ ኹጥባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኒቃባቸው ምክንያት የመብት ጥሰት እየደረሰባቸው ስላሉ ሙስሊሞች እንዲያደርጉ ! ! !
የአንድ ሙስሊም ጉዳይ የሁሉም ሙስሊም ጉዳይ ነው። ሙስሊም እንደ አንድ አካል ነውና አንዱ ክፍል ሲታመም ሌላውም አካል ሕመሙን ያስተጋባል። ሙስሊም እንደ አንድ ግንብ ነውና እርስ በዕርሱ ይጠነካከራል። ለዚህም ሲባል በሁሉም መስጂዶች ኹጥባው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ይሆን ዘንድ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በደብዳቤ ጠይቀናል።
ስለሆነም ኡስታዞች፣ መሻይኾች፣ ዱዓቶች እና ኢማሞች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መብታቸው ሙስሊም ስለሆኑ ብቻ መብታቸው እየተጣሰባቸው ስላሉ ተማሪዎች በማድረግ ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ በአላህ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
"የሙስሊም ምሳሌው ... ልክ እንደ አንድ አካል ነው። የሆነ ክፍሉ ሲታመም ሌላው ክፍል እንቅልፍ በማጣት እና በትኩሳት ይጣራል።" - ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ከተናገረው፦
"ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሀይማኖታቸው ምክንያት ወደ ዳር የሚገፉበት ስርዓት አለ። ዛሬ በምናወራበት ሰዓት እንኳ ሙስሊም ተማሪዎች ዩኒቨርስቲ አካባቢ ሒጃብ ለበሳችሁ ኒቃብ አደረጋችሁ እየተባሉ ከትምህርት ይስተጓጎላሉ።"
፦ ይህ የተንሻፈፈ ስርዓት በዚህ ትውልድ በቃ ሊባል ይገባል። አሁን ያብቃ!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
