uk
Feedback
ሐበሻ ኢስላሚክ ሚድያ

ሐበሻ ኢስላሚክ ሚድያ

Відкрити в Telegram

قال الله تعالى ( وَلَا تَلْبِسُوا الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُوا الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ )البقرة (42) አሏህ በእርግጥም አለ፦[እውነትን በውሸት አትሸፍኑ እናንተ እውነታውን እያወቃቹህ] ምንጭ፦«ሱረቱ አል–በቀራህ አንቀፅ /42/ በኡስታዝ ሐምዛ [አሰዱሏህ]

Показати більше
1 995
Підписники
+124 години
-117 днів
-3430 днів
Архів дописів
عَن أَنَسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنهُ قَالَ: «مَا شَمَمتُ عَنبَرًا قَطُّ وَلَا مِسكًا وَلَا شَيئًا أَطيَبَ مِن رِيحِ رَسُولِ اللَّه
عَن أَنَسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنهُ قَالَ: «مَا شَمَمتُ عَنبَرًا قَطُّ وَلَا مِسكًا وَلَا شَيئًا أَطيَبَ مِن رِيحِ رَسُولِ اللَّهِ ﷺ»، رَوَاهُ البُخَارِيُّ. 📌 ከ'ኣነስ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንደተያዘው እርሳቸው እንዲህ ይላሉ፦「"ዐንበርንም¹ ሆነ ሚስክን እንዲሁ ሌላ ሽታው ሚማርክን ነገር አላሸተትኩም የነብዩን ሽታ የመሰለ"」። ምንጭ፦『ሶሒሑል ቡኻርይ』። ① መሃዛቸው ከሚያውዱ የሽቶ አይነት ነው።አይነት ያለው ሲሆን ከእርሱ ውስጥ በማጨስ ሽታው እንዲወጣ ሚደረግ አለ። ② ማራኪ እንዲሁ ልዩ ከሚባሉ ሽታ ካላቸው ነገሮች የሚመደብ ሲሆን ከሚዳቆ ሰውነት የሚቀሰም ልዩ የሽቶ አይነት ነው። FROM .......ABU AYSIL

♦ ثبت لدينا بالوجه الشرعي رؤية هلال 🌙شهر *المحرم* 1448 للهجرة بعد غروب شمس يوم الإثنين. ๏ በሂጅርያህ አቆጣጠር የ 1448 ኣመተ ሂጅርያህ የሙሐረ
♦ ثبت لدينا بالوجه الشرعي رؤية هلال 🌙شهر *المحرم* 1448 للهجرة بعد غروب شمس يوم الإثنين. ๏ በሂጅርያህ አቆጣጠር የ 1448 ኣመተ ሂጅርያህ የሙሐረም ወር ጨረቃ በሸሪዓዊህ መንገድ በተደረገ ክትትል መታየቷ ተረጋግጧል::

✧ እገሌን ተሳስተዋል ልትል ነው?! እነ ሸይኽ ፉላንን ጠመዋል ልትል ነው? እነ ምናምን እነ… ለምትሉ፤መመዘኛቹ ሸሪዓው ቀርቶ የሰዎች ማንነት የሆናችሁ ግለሰቦች ሰከን ብላችሁ አንብቡት። قال الشيخ العلامة الزاهد الكوثري في مقالاته ما نصه "[ الكُفْر كُفْرٌ كَائِنًا مَنْ كَانَ النَّاطِق بِهِ، وَالزَّيْغ زَيْغٌ كَائِنًا مَا كَانَ مَصْدَرهُ، وَلَيْسَ فِي الإِسْلاَمِ دِينٌ يَخْتَلِفُ بِاخْتِلاَفِ الأَشْخَاصِ، فَالإِيمَان إِيمَانٌ مُطْلَقًا، وَالكُفْر كُفْرٌ مُطْلَقً"]انتهى ¤ ኣ'ሸይኹ ኣል-ዐላመቱ ሙሐመድ ኣ'ዛሂዱ ኣል-ከውሰርይ እንዲህ ይላሉ፦ [“የተናገረበት ማንም ይሁን ማን ኩፍር ኩፍር ነው።ጥመትም ጠንሳሹ ማን ሆነ ማን ጥመትነቱ አይቀሬ ነው።በእስልምና ውስጥ በሰዎች መለያየት የሚለወጥ ሕግጋት የለውም።ኢማን ማንም እስካመነበት ድረስ ኢማን ነው።ክህደትም ማንም እስከካደበት ድረስ ክህደት ነው”]። ምንጭ፦[መቃላቱ ኣል-ከውሰርያህ]። HAMZA ....ASEDULLAH

قَالَ سَحنُونُ: «مَن اشتَرَى كُتُبَ العِلمِ أَو وَرِثَهَا ثُمَّ أَفتَى بِهَا وَلَم يَعرِضهَا عَلَى الفُقَهَاءِ أُدِّبَ أَدَبًا شَدِيدًا»، [ፉቀሃኦች ዘንዳ አቅርቦ ሳይቀራ የእውቀት ኪታቦችን በመግዛት አልያ በመውረስ (ብቻ)ፈትዋ ሚሰጥ ከፍተኛ በሆነ መልኩ አደብ እንዲይዝ ይደረጋል]።

መረጃ ይዳኘን ክፍል ①② [ሑጀቱል ኢስላም አል-ገዛልይ] ስማቸው ከቀደምት ግዜያት ጀምሮ እስካለንበት ዘመን ድረስ ሳይጠለሽ በክፉም ሳይደበዝዝ በበጎ ከሚታወሱ አኢማዎች መሀከል ሑጀቱል-ኢስላም የሚሰኙት ስመ ገናናው ኣቡ-ሓሚድ አል-ገዛልይ ረዲየሏሁ ዐንሁ ይገኙበታል።እኚህ ታላቅ ሰው የሰለፍን ዘመን አልፈው ኸለፍ ከሚሰኙት የእውቀት ሊሂቃን የሚመደቡ ሲሆን፤በመዝሃብ ደረጃ የሻፊዒይን፣ በዒልም ደረጃ አል-ሙጅተሂድ ፊል መዝሀብ የተሰኙ በዓቂዳ መንገድ አ'ሽዓርይነትን የተላበሱ ታላቅ የኢስላማዊ እውቀት ምሁር ናቸው። አል-ኢማሙ ኣል-ገዛልይ 450-505 አመተ ሂጅራ የቆዩ ሲሆን ከመሻይኾቻቸው መሀከል አቡል-መዓሊይ አል-ጁወይንይ አንዱ ሲሆኑ ከተማሪያቸው ውስጥ ደግም ታላቁ ወልይ ኣቡበክር ብኑል ዓረብይ ይገኙበታል። እኚህ ታላቅ የእውቀት ሰው ከዓቂዳ ዘርፍ አንስቶ እስከ ፊቅሂ የተዋጣላቸው የኢልም ባልተቤት መሆናቸው እብለት የሌለው ፍንትው ያለ እውነት ነው።ከሰነዷቸው ኪታቦች መሀከልም ኢልጃሙል ዓዋም ፊይ ዒልሚል ከላም፣ አል-ሙስተስፋ፣ ኢ'ሕያእ ሌሎችም ጥቂት ማይባሉ እውቀታቸውን በይፋ የሚያስተጋቡ መፅሀፎችን ለኡማው አበርክተዋል። እንዲህ ያሉ ታዋቂ ሊሂቃን ምእመኑ ኮርቶ ወደነርሱ በመጠጋት ንግግራቸውን በማስረጃነት ቀን ከሌት መፅሀፍቶቻቸውን በመያዝ እንደሚደጋግመው ሁሉ፤ በተቃራኒው የእስልምና ጠላት የሆኑ ሰዎች የነዚህ ሊሂቃን እውቅናን በመጠቀም ጥለው በሄዱት በጎ አሻራዎች ላይ የራሳቸውን መርዝ ቀስ በቀስ በቀለሙ እንዲሁ በአይነቱ አመሳስለው ለኡማው በመስጠት ለምእመኑ የእፍረት ካባ ለማከናነብ መጣር ከጀመሩም ዋል አደር ያሉም አልጠፉም። በዛሬው ርዕሴ ኣቡ-ሐሚድ አል-ገዛልይ (ሑጀቱል ኢስላም) በአህሉል ቢድዓዎች ላይ ከነርሱ ውስጥም ሙጀሲማ የሚሰኙት አንጃዎች ላይ ያላቸው ፅኑ አቋም ምን ይመስል ነበር የሚለውን ኪታቦቻቸውን እያስደገፍኩ አጠር ባለ መልኩ በማስረጃ የማቀርብ ይሆናል። ¤ በመጀመርያ ሑጀቱል-ኢስላም ኣቡ'ሓሚድ አል-ገዛልይ ኢ'ልጃሙል ዓዋም ፊይ ዒልሚል ከላም በተሰኘ ኪታባቸው ላይ ገፅ 96 ላይ እንዲህ ሲሉ ያሰፈሩትን እንመልከት፦ * قال في إلجام العوام 〔وأن من عبد جسماً فقد عبد صنماً سواء كان الجسم صغيراً أو كبيراً، قبيحاً أو جميلاً، سافلاً أو عالياً على الأرض أو على العرش، فكان نفي الجسمية ونفي لوازمها معلوماً لكافتهم على الضرورة بإعلام رسول الله صلى الله عليه وسلم والمبالغة على التنزيه لقوله: لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ ) سورة الشورى: (۱۱〕 ① [“ፈጣሪ ብሎ ያሰበው "አካል" ትንሽ አልያ ትልቅ፣አስጠሊታ አልያ ቆንጆ፣ከላይ ያለ ወይም ከታች ፣በምድር አልያ ከዓርሽ በላይ ብሎ ብያስበውም፤ አካልን የተገዛ #ጣኦትን እንደተገዛ ነው። አካልን ሆነ አካልን የሚያሲዙ ነገራቶች ከአሏህ የራቁ እንደሆኑ ሁሉ በሚጋራው መልኩ በነብዩ አድራሺነት እንዲሁ አሏህን በሚያጠሩ አናቅፅቶች የተሰራጨ ሲሆን ይህም <እርሱን ሚመስል የለም፤እርሱም ሰሚም ተመልካች ነው> የሚለውን የመሰለ አንቀፅን ይገኝበታል።”] ๏ አል-ገዛልይ ፈጣሪውን ጅስም አድርጎ የሳለ አልያ ያሰበ ሰው ከጣኦት አምላኪ ጋር ማመሳሰላቸው ጎልቶ የሚታይ ሐቅ ሲሆን ያን አካልም አቆሞ አልያ አስቀምጦ፣ ጭራቅ አልያ የውበት ሞዴል ቢያደርገውም አንዳች ልዩነት እንደማይፈጥር አስፍረዋል። ¤ ሑጀቱል-ኢስላም ኣል-ሙስተስፋ የተሰኘው ኪታባቸው ላይ በገፅ 332 በተመሳሳይ የሙጀሲም ዕምነት ከሚያከፍሩ የእምነት አይነቶች የሚመደብ መሆኑን ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፦ *وقال الغزالي في المستصفى ”أما إذا كفر ببدعته، فعند ذلك لا يعتبر خلافه، وإن كان يصلي إلى القبلة ويعتقد نفسه مسلماً.لأن الأمة ليست عبارة عن المصلين إلى القبلة، بل عن المؤمنين، وهو كافر، وإن كان لا يدري أنه كافر“ ② [«በቢድዓው የከፈረ እንደሆነ በዛ ግዜ ልዩነቱ ቦታ አይሰጠውም።ወደ ቂብላ ዞሮ በመስገድ እራሱን ሙስሊም አድርጎ ቢያስብም፤ ምክነያቱም ኡማህ ሲባል ወደ ቂብላ ዞረው የሚሰግዱ ሰዎች ገለፃ ሳትሆን ይልቅንስ የትክክለኛ አማኞች ናት።ይህ ደግሞ ካ*ፊር ነው።መክፈሩን ባያውቅም»]። ¤ በተመሳሳይ መልኩ ከመሞታቸው ከሶስት ቀን በፊት በፃፉበት የመጨረሻ ኪታባቸው ከሚሰኘው ውስጥ አንዱ የሆነው በኢልጃሙል ዓዋም ገፅ 5 ላይ ፍንትዋ አድርገው ሽምያ፣ማሽሟጠጥ ሆነ ማጣመም በማይቀመስበት ቃላት የሙጀሲምን ከሃዲነት በኢጅማዕ መሆኑን ያሰፍራሉ፦ وقال أبو حَامِدٍ الغَزَالِيُّ في كتابِهِ المسمَّى إِلْجَامَ العَوَامِّ عَنْ عِلْمِ الكَلَامِ ما نَصُّهُ: «فَإِنْ خَطَرَ ببالِهِ أَنَّ اللهَ جسمٌ مُرَكَّبٌ مِنْ أعضاءٍ فهو عابدُ صَنَمٍ؛ فَإِنَّ كُلَّ جسمٍ هو مخلوقٌ، وعبادةُ المخلوقِ كفرٌ، وعبادةُ الصنمِ كفرٌ لأَنَّهُ مخلوقٌ، وكان مخلوقًا لأَنَّهُ جسمٌ، فَمَنْ عَبَدَ جسمًا فهو كافرٌ بإجماعِ الأُمَّةِ السَّلَفُ منهم والخَلَفُ».اهـ ③[“በአዕምሮ ላይ አሏህን ከክፍለ አካላት የተገጣጠመ ነው ብሎ ካመነ ይህ ሰው #ጣዎትን አምላኪ ነው። ሁሉም አካሎች ፍጡሮች ናቸው። ፍጡርን መገዛት ደግሞ ኩፍር ነው።ጧኦትን ማምለክ ኩፍር ነው ምክነያቱም ፍጡር ስለሆነ። ፍጡር የሆነውም አካል ስለሆነ ነው።አካልን የተገዛ ደግሞ #በዑለማዎች የጋራ አቋም ከሀዲ ነው”]። ¤ ይህም ብቻ ሳይሆን በሙጀሲምና በፀሀይ አምላኪ መሀል ልዩነት እንደሌለም በኣሊቅቲሷድ ፊል ዒቲቃድ ገፅ 34 ላይ ሲጠቅሱ ይህን ይላሉ፦ فإن القائل بأن الله سبحانه جسم وعابد الوثن والشمس واحد〕 [“አሏህን አካል ነው ብሎ የሚል እንዲሁ ጣኦትና ፀሀይ የሚገዙ ሰዎች #አንድ ናቸው”] ∅ አንተ እውነትን ፈላጊ ሆይ ሐቅን ከመናገር ምኑ ነው ሚያስፈራህ?! ኣቡ ሐሚድ መጨረሻ ከእርሱ ቡሀሏ ሌላን ለመፃፍ ብእራቸውን አላነሱም በተባለበት ኢልጃሙል ዐዋም ኪታብ ላይ ሙጀሲማዎች ካፊር ናቸው። ይህም ኢጅማዕን በመመርኮዝ ነው ሲሉህ በግልፅ ፈንትው አድርገው ገልፀውልሀል።ከዚህ ሁሉ ማስረጃ ቡሀሏ ተጨምሮባቸው ነው የሚለው ቢያደናግርህ እውን ከአሏህ ውጪ ያለን በአሏህ ስያሜ አድርጎ ሚገዛን ሙስሊም አድርጎ ሚያስብ ኢማም አለን? እንዲሁ ኺላፍም ተነቅሏል ለማለት ምን ነክቶህ በምንስ ታውረህ ነው?! አሏህን በዲናችን ላይ ከሚመጣ አደጋ ሰላምን እንጠይቀዋለን። ሸይኽ ዓብዱሏህ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ፦ سلامةُ الدينِ لا يعادلُها شيءٌ [የዲን ሰላም መሆን ምትክ የለውም]። ↘ በስተመጨረሻም ወንድማዊ ምክሬ የሚሆነው ኪታብን በማንበብ ብቻ እውቀት አይያዝም። ማንበብን ብቻ ተመርኩዞ እውቀት ለመሰብሰብ ሲደከርት የከረመ ሸይኩ ሸይጧኑ ሆኖ እንጂ አልታየም።ለዚህም ታላቁ የሰለፍ ዓሊም ሰሕኑን አል-ማሊክይ ኪታብን (ከመርካቶ) እየሸመቱ ፈትዋ ሚሰጡ ሰዎችን እንዲህ በማለት ይገስፃሉ፦

ጉዳዩ በቅርቡ በመኪና አደጋ የሞቱትን የሸህ ሙሐመድ ሰዒድ ( ኮቻ) እዳ መክፈለን ይመለከታል። እንደሚታወቀው ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ በመኪና አደጋ ህይዎታቸው አልፏል። በመሆኑም ይህ የመኪና አደጋ ያስከተለው እዳ ከቤተሰብ አቅም በላይ በመሆኑ ወደ ሚዲያ እንዲወጣ ተገደዋል። ስለ ክስተቱ= ሸህ ሙሀመድ ሰዒድ በሳኡዲ አረቢያ "ሪያድ" ይኖሩ ነበር ፣ ከዛ መንጃ ፍቃድ ለማውጣት እንዲያግዘኝ ብለው በጓደኛቸው ስም እና መንጃ ፍቃድ መኪና ተከራዩ (ለመለማመድ)። ከተከራዩ ከ13 ቀን ብኋላ ለማንም ሳያሳውቁ (ከሚስታቸው ውጭ) ወደ መዲና ብለው ጉዞ ወጡ ከ ሪያድ 40 ደቂቃ ያክል ብቻ እንደተጓዙ "ቱመይር " ከተማ ከመድረሳቸው በፊት የመኪና አደጋ ደረሰባቸው። ሁለት መኪኖች ጋ ተጋጩ ፣ ህይዎታቸው ከዛው ቦታ አለፈ፣ ስምንት ሰዎችም በአደጋው ምክኒያት ወደ " ቱመይር" ጠቅላላ ሆስቲፓል ተወሰዱ። አምስቶቹ ሰዎች በ "ሱዙኪ" መኪና ሶስቶቹ ደግሞ በ "ጀይሊ" መኪና የነበሩ ሲሆን ሸህ ሙሀመድ ደግሞ በ "ኪያ" መኪና እንደነበሩ የሣዲቅ ከተማ የተራፊክ መረጃ ያመለክታል ግጭቱ ከተፈጠረበት ቅርብ ከተማ ነች። ስለ እዳው 1ኛ የሣዲቅ ከተማ ተራፊክ ጉዳዩን መርምሮ ሙሉ በሙሉ ጥፋተኛ ያዳረገው ሸህ ሙሀመድ ሰዒድን ነው። 2ኛ ኢንሹራንሱ ሻሚል ነበር ግን መንጃ ፍቃድ ስለሌላቸው የሟች ቤተሰብ መክፈል አለበት ህግን ለተጋጨ ሰው ኢንሹራንሱ እዳ አይሸከምም ብለዋል። ስለዚህ የሁለቱ መከኖች እዳ(99460) ሪያል ሲሆን፣ እነሱ የሚነዷት መከና ደግሞ (42780) ሪያል ባጭር ግዜ እንዲከፈላቸውም ጠይቀዋል። ይህ ማለት ድምሩ (142,140) ሲሆን ወደ ETB ሲመነዘር (6,543,040) ስድስት ሚሊዮን አመስት መቶ አርባ ሶስት ሺህ 40 ብር ። የስምንት ሰዎች ህክምና ወጪ ሲጠናቀቅ እናሳውቃለን ብለው አሳውቀውናል። ስለዚህ በተቻለን እንርዳቸው ለማለት እንወዳለን። ለበለጠ መረጃ +251 91 007 9091 ኡስማን ሰዒድ ( ወንድማቸው) +251 94 569 7852 ሸህ ዐብዱሸኩር (ጓደኛ) +251 93 039 7302 ሸህ ዐብዱረሕማን ( ጓደኛ ) ንግብ ባንክ Ousman seid and abdushukur habte 1000766398069

๏ ሸይኹና ሸይኽ ዑመር ኢማም አሏህ ይጠብቃቸውና በቂርአት መሀል ሳለን ወደ አንድ እጅግ አስተውሎት ስለሚሻ፡ እጃችንም ላይ ስላለ ትልቅ ጀውሃር እንዲህ ሲሉ አስታወሱን፦[“ሸይኽ ዓብዱሏህ¹ ረሒመሁሏህ
๏ ሸይኹና ሸይኽ ዑመር ኢማም አሏህ ይጠብቃቸውና በቂርአት መሀል ሳለን ወደ አንድ እጅግ አስተውሎት ስለሚሻ፡ እጃችንም ላይ ስላለ ትልቅ ጀውሃር እንዲህ ሲሉ አስታወሱን፦[“ሸይኽ ዓብዱሏህ¹ ረሒመሁሏህ በኣ'ሲራጥ ኪታባቸው ላይ አንድ ፀሀይን የሚገዛ ሰው ከነዛህ ሙሸቢሃዎች መሀከል አንዱን በአዕምሮ ማስረጃ ብቻ ለውይይት ቢፈልገው ፀሀይ ሚገዛው ያሸንፈዋል ሲሉ መናገራቸው በነ እፎይ ይገለጥልሀል” አሉ]። ¹ هو الشيخُ الحافظُ معلمُ التوحيدِ مجددُ زمانِه خادم علم الحديث عبد الله بن محمد بن يوسف الهرري الحبشي. መልካም ጁሙዓህ።

በስተመጨረሻ፦በነዚህ ርዕሶች ላይ #አደም ሙሐመድ ለውይይት እጠራሀለው።በፈለከው ግዜና ሰኣትም እንዲሆን ይደረጋል።ለዚህም ጥሪ ዝግጁ ከሆንክ በግዜ በማሳወቅ ለውይይቱ መንገድ ልታቀል ዘንዳ እጠይቃለው።

በማለት ኢብን ተ'ይሚያን ነፃ ለማድረግ ሐዲሱን በደንብ ባለመረዳት እመት ዐኢሻህን ረዲየሏሁ ዓንሃ በፈጣሪዋ ላይ ባላት እምነት ጎዶሎ ማድረግ ውጤቱ ሆኗል። ለዚህም በቅርቡ በአዲስ ዝግጅት እመለስበታለው። ሌላው በተእዊል ከሆነ ብሎ ኢብን ተ'ይሚያን ላለማክፈር ያነሳቸው ደዋቢጦች ኢብን ተ'ይሚያህ ሚያህል ሓፊዝ በየትኛውም በተጠቀሱ የስድ ደዋቢጦች ዓቂል፣ባሊግ ሆኖ ያለ ምላስ ወለምታ እስከተናገረው ድረስ ተእዊል የሚለው በዚህ ቀጥዕይ ጉዳይ ላይ ላለመክፈር ዑዝር ሊያሰጠው የሚችል ምንም ነገር ፈፅሞን አይኖርም።ለዚህም ረምልይ ባዘጋጁዋት በሚንሃጅ ሸርሓቸው ላይ አሕመድ ብኑ ዓብዲረዛቅ አል-መግሪቢይ አ'ረሺድይ በመባል ሚታቁት 1096 አመተ ሂጅራ የሞቱት እንዲህ ሲሉ የተእዊል ጉዳይ በስድ ለሁሉ ነጥብ ድርሻን ይዞ እንደ ዓቂል መሆን የሚጠየቅበት እንዳልሆነ በዚህ መልኩ ያስረዳሉ፦ قَالَ الْمُحَشِّي عَلَى الرَّمْلِيِّ أَحْمَدُ بنُ عَبْدِ الرَّزَّاقِ الْمَعْرُوفُ بِالْمَغْرِبِيِّ الرَّشِيدِيِّ الْمُتَوَفَّى سَنَةَ أَلْفٍ وَسِتٍّ وَتِسْعِينَ «قَوْلُهُ «وَاجْتِهَادٍ» أَيْ فِيمَا لَمْ يَقُمِ الدَّلِيلُ الْقَاطِعُ عَلَى خِلافِهِ بِدَلِيلِ كُفْرِ نَحْوِ الْقَائِلِينَ بِقِدَمِ الْعَالَمِ مَعَ أَنَّهُ بِالِاجْتِهَادِ» اهـ [“(ኢጅቲሃድ አልያ በተእዊል) ማለታቸው ከእርሱ በተቃራኒ ማስረጃ ባልቆመበት ላይ ነው።ለዚህም ዐለምን ጅምር የላትም በማለት የከፈሩ ሰዎችን የመሰለ: ይህም ከነርሱ በኢጅቲሃድ (ተእዊል) ከመሆኑም ጋር ነው”] በማለት ተእዊል ማድረግ ሁሌ ኩፍር ላይ ከመውደቅ እንደማይከለክልና በነዚህ ባሉ ቦታዎች ደግሞ ፈፅሞን እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደማይታይ ያስቀምጣሉ።ዓለምን ጅምር የላትም ያሉ ሰዎች በተእዊል ቢሆንም ነገር ግን ተእዊል ሁሌ ተክፊርን አይከለክልምና፤ ይህን ያለ ሰው ይከፍራል ሲሉ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ማለት ይህ ነው። አንደኛው ተእዊል ሁሉ ቦታ ኩፍር እንደማይከለክልና። ሁለተኛ ኢብን ተ'ይሚያህ በዚህ ንግግሩ ካፊር እንደሆነ እየገለፁ ነው።ኢብን ተ'ይሚያህ በዚህ ዓለምን ጅማሬ የላትም ባለበት ንግግሩ የቁርኣንና የሓዲስን ህግጋቶች ከመተላለፉ አልፎ በዚህም አቋሙ ላይ እርሱን የማክፈር ብያኔ ከምስራቅ እስከ ምዕራቡ ዳርቻ ያሉት ምእመናን እንደሰጡ በጥቂቱ እንገልፃለን ከነርሱ መሀከልም፦ وقال الحافظ اللغوي محمد مرتضى الزبيدي في شرح الإحياء عند الكلام على تكفير الفلاسفة ما نصه (21) "ومن ذلك قولهم بقدم العالم وأزليته، فلم يذهب أحد من المسلمين إلى شىء من ذلك" اهـ، ① አል-ሓፊዙ አ'ሉገውዩ ሙሐመድ ሙርተዶ ኣ'ዘቢድይ "ኢትሓፉ ሳዳቲል ሙተቂይን"ብለው በሰየሙት ኪታብ ላይ ስለ ፋላስፋዎች መክፈር ሲጠቅሱ ይህን ይላሉ፦[“ከንግግራቸው መሀከል ዓለም ጅምር የላትም የሚለው ይገኝበታል። አንድም ሙስሊም እነርሱ ባሉበት የተጓዘ የለም”]። ይህ ከሳቸው የተሰጠ የተክፊር ፍርድ እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል። ምክነያቱም በዚህ መንገድ የተጓዘ እንደሆነ ሙስሊም የለም፤ ሲሉ በዛ መንገድ የተጓዘ ኢማኑ የተነጠቀ እንደሚሆን አስምረውበታል። وقال الحافظ ابن حجر العسقلاني في فتح الباري (20) ما نصه "قال شيخنا- يعني العراقي- في شرح الترمذي: الصحيح في تكفير منكر الإجماع تقييده بإنكار ما يعلم وجوبه من الدين بالضرورة كالصلوات الخمس، ومنهم من عبر بإنكار ما علم وجوبه بالتواتر، ومنه القول بحدوث العالم، وقد حكى القاضي عياض وغيره الإجماع على تكفير من يقول بقدم العالم، ② አል-ሓፊዙ ኢብኑ ሓጀር አል-ዓስቀላንይ "ፈትሑል ባሪይ" በተሰኘው የሶሒሑል ቡኽርይ ሸርሓቸው ላይ ይህን ሲሉ ያስቀምጣሉ፦[“ሸይኻችን (ኣል-ዒራቅይ ማለታቸው ነው)በሸርሑ ኣ'ቲርሚዝይ ላይ"ኢጅማዕን የጣሰ ይከፍራል" የሚለው ንግግር ትክክሉ "ኢጅማዕ የተደረሰበት ነጥብ ግዴታነቱ ሁሉ ዘንዳ የተሰራጨ በሆነ ጉዳይ መሆን አለበት" ተብሎ መለየት ያስፈልገዋል። ለምሳሌ እንደ አምስት ግዜያት ሶለዋቶችን ያለ ይመስል።ከነኚህ ዑለማዎችም መሀከል ስለዚህ ገለፃ ሲያደርግ "ግዴታነቱ በተዋቱር የመጣን ነገር መቃወም በማለት ያስቀምጣሉ"። ከዚህ ጉዳይ መሀከልም የዓለም ጅማሬ መኖር ይገኝበታል።አልቃዲይ ዒያድ እንዲሁ ሌሎችም “ዓለምን ጅማሬ የላትም ብሎ በተናገረ ላይ #ካፊር እንደሆነ የጋራ አቋም አስቀምጠዋል”]። وقال في موضعءاخر منه ما نصه (22) "وقال السبكي في شرح عقيدة ابن الحاجب: اعلم أن حكم الجواهر والأعراض كلها الحدوث،ا فإذًا العالم كله حادث، وعلى هذا إجماع المسلمين بل وكل الملل، ومن خالف في ذلك فهو كافر لمخالفة الإجماع القطعي" ا.هـ.ا በሌላ ቦታ ላይ በዛው ፈትሑል ባሪይ ኪታባቸው ኣ'ሱብክይ "ሸርሑ ኢብኒል ሓጂብ" ላይ እንዲህ ብለዋል ይላሉ፦[“የመጠን እንዲሁ የመጠን ባህሪያቶች ሁሏም ፍጥረት ናቸው።ስለዚህም ዓለም በጠቅላላው ፍጡር ነው። በዚህም ላይ የሙስሊሞች የጋራ አቋም #ታስሯል። ይልቅንስ ከእስልምና ውጪም ያሉ እምነቶች በዚህ ላይ ያፀናሉ። በዚህ ላይ የተቃረነ #ካፊር ነው። ምክነያቱም በቁርጥ የታወቀን የሆነ የኢጅማዕ አቋም ተላልፏልና”]። قال القاضي عياض في الشفا (19) "وكذلك نقطع على كفر من قال بقدم العالـم أو بقائه أو شك في ذلك على مذهب بعض الفلاسفة والدهرية" اهـ.ا ③ አል-ቃዲይ ዒያድ "ኣ'ሺፋ" በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦[“እንዲሁ እንደ ከፊል ፈላስፋዎች እንዲሁ ደህሪያዎች ዓለምን ጅማሬ የላትም አልያ ዘውታሪ ናት፤ብሎ በተናገረ አልያ በተጠራጠረ ሰው በኩፍሩ ላይ በቁርጥ #እንወስናለን”]። نقل المحدّث الأصولي بدر الدين الزركشي في تشنيف المسامع (18) اتفاق المسلمين على كفر من يقول بأزلية نوع العالم فقال بعد أن ذكر أن الفلاسفة قالوا: إن العالم قديم بمادته وصورته، وبعضهم قال: قديم المادة محدث الصورة، ما نصه "وضلَّلهم المسلمون في ذلك وكفروهم" اهـ. ④ አል-ሙሐዲሱ አል-ኡሱልዩ በድሩ ዲን አ‘ዘርከሽይ የዐለምን መሰረት ጅማሬ የለውም ያሉትን ፈላስፋዎች ንግግራቸውን በ "ተሽኒፉል መሳሚዕ" ብለው በሰየሙት ኪታብ ከጠቀሱ ቡሀሏ በዚህም በመክፈራቸው ላይ የዑለማእን የጋራ አቋም ሲያስተላልፉ እንዲህ ይላሉ፦[“በእርግጥም ሙስሊሞች በዚህ ላይ አጥምመዋቸዋል ብሎም አክፍረዋቸዋል”]። ከዚህ ሁሉ የዑለማእ የጋራ አቋም ቡሀሏ የተለመደው ኺላፍ አለበት ምትለው ማታለያቹህ የምትሰራ አትሆንም።አልያ አሏህን ፈጣሪ አይደለም ያለ ሙስሊም ነው ትላላችሁ አልያ ካፊር ነው በማለት ኢብን ተ'ይሚያን በመተው የዑለማኡል ኣዕላምን መንገድ ትይዛላችሁ።

መረጃ ይዳኘን ❿ قال الله تعالى"يُضِلُّ بِهِ كَثِيرًا وَيَهْدِي بِهِ كَثِيرًا ۚ وَمَا يُضِلُّ بِهِ إِلَّا الْفَاسِقِينَ" سورةُ البقرة ٢٦ [“ በርሱ (በምሳሌው) ብዙዎችን ያጠማል።በርሱም ብዙዎችን ያቀናል፡፡በርሱም አመፀኞችን እንጅ ሌላን አያጠምም”] "ሱረቱል በቀራህ 26" ፍትሓዊው ጌታ አሏህ ሁሉ የእርሱ ንብረት ነው። በችሮታው ያሻውን ገነት ቢያስገባ ቀሪውን በፍትሑ ቢቀጣ ውዳሴ እንዲሁ ልቅና እንጂ ፈፅሞን ውሳኔው ላይ ውግዘት አይታሰብም።ሁሉ የእርሱ ሁሉም ወደርሱ፣ ሁሉ ለእርሱ ተገዢ: ጉዳዩም ሁሉ ወደ እርሱ ተመላሽ ነውና። መሃሪው ጌታ አሏህ ነብያትን ያወጣበት ሰው የተባለን ዘር ከሁሉ ዘሮች በጥቅሉ አብልጦታል። ብሎም ይህ ዘር ከእርሱ ውስጥ ለፈጠረው ሀያል ጌታ ተገዢ እና ተዋዳቂ በትዕዛዙ በነብያቱ በኪታቡም ተመሪ ቢኖርም፤በተቃራኒው ደግሞ ሊመራበት ዘንዳ በተሰጠው መፅሀፍ አስተባባይ ሊመራው ሰበብ በመሆን በተላከለት ነብይ ክዶና አምፆ እሚገኝ ዘመን የተረከለን እልፈ አላፍ ለቁጥር ሚያዳግት ሆኖ ይገኛል። ነብዩና ሙሐመድ ﷺ በብዙ ትውፊቶቻቸው እንዲሁ ለእርሳቸው በተላከው ቁርኣን ላይ ጥቂት በማይባሉ አናቅፅቶች ውስጥ የአሏህን ፈጣሪነት የሌሎችን ፍጡርነት የአሏህን ጅማሬ አለመኖር የሌሎችን ግኝነት በዝርዝር አስፍረውና እንዲሁ ሰፍሮ ምናገኘው ከኢማን መሰረታዊ ነጥብ ከሆኑት ውስጥ የሚመደብ ችላ ማይሰኝ ትልቅ ጉዳይ ነው። አሏሁ ጀለ ጀላሉሁ በሱረቱል ኣ'ዙመር አንቀፅ 62 ላይ እንዲህም ይላል፦ قالَ اللهُ تعالى" اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ" الزمر آية 62 [“አሏህ የሁሉ ነገር ፈጣሪ ነው”] አንድ ግለሰብ ይህን ሶሪሕ የሆነ አንቀፅ እተርጉማለው በማለት የያዘውን ፍቺ ማጣመም አይበቃለትም።በዚህም አንቀፅ አሏህ የራሱን ፈጣሪነት የሌሎችን ደግሞ ፍጡርነት አፅድቋል። ይህም ሲፈታ አሏህ ጅማሬ የለውም ሌላው ደግሞ ጅምር አለው የተገኘ ነው ሚለውን ያለ ምንም ጥርጥር የሚያስረዳ ነው። የአሏህን ኪታብም ከሁሉ በላይ ተገንዛቢ የሆኑት ትልቁ ሰው ነብዩ ሙሐመድﷺ"አልቡኻርይ" በዘገቡት ሓዲሳቸው ከየመን በሕቡእ ሆነው በመምጣት ስለ መጀመርያው ፍጡር ምንነት ለጠየቋቸው ሰዎች እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፦ قالَ عليه الصَّلاةُ السَّلامُ "كانَ اللهُ ولَم يَكُنْ شَيءٌ غَيرُه" رواهُ البخاريُّ [“አሏህ ነበር ምንም ነገር ከመኖሩ በፊት”]። ይህ ሓዲስ ብዙ ቁም ነገሮችን ይዟል።ነገር ግን የማስረጃ ቦታውን በመጥቀስ ሲታጠር ነብዩ ﷺ ለነኚህ ሰዎች በመጀመርያ የአሏህን ጅማሬ አለመኖር አፅድቀውላቸዋል።ምክነያቱም ከእውቀቶች ሁሉ ሊቀደም የሚገባው አሏህን ማወቅ እንደሆነ እኚህ ትልቁ ሰው በመንገዳቸው ምልክት እየሰጡን ነው።ቀጥሎም ከእርሱ ውጪ ያለ በጠቅላላ ከእርሱ ጋር እንዳልነበርና አሏህ እንደፈጠረው ገለፃ አድርገዋል።ሐዲሱም ይቀጥላል… ብሎም አንድ ሰው ነብዩﷺያሉት ከእርሱ ውጪ ምንም አልነበረም ቢሆንም ነገር ግን "ምንም" የሚለው ቃል በራሱ ጥቅላዊ ውጤት እንዴት ያሲዛል ካለ እኛም በምላሹ ዑለማዎች ዘንዳም ምትታወቅ አንድ መመርያ አለች እርሷም "ነኪራህ የሆነች ቃል በነፍይ የንግግር ዘይቤ ላይ ከመጣች ጥቅላዊ ትርጉምን ትሰጣለች" ይህም ማለት ነብዩﷺሓዲሳቸው ላይ "شيء" የሚልን ቃል ተጠቅመዋል ይህች "ነኪራህ" ትሰኛለች። "ነፍይ" ደግሞ "لَمْ" የምትሰኘዋ ናት። ሁለቱ በአንድ ዐ.ነገር ሲጣመሩ ትርጉማቸው ጥቅልን የሚያሲዝ በዚህ ሓዲስ ደግሞ ከአሏህ ውጪ ያለን የሁሉንም ጅማሬ አለመኖር የሚያስክድ፤ፍጥሩነቱን ደግሞ የሚያፀና ነው።በዚህም ጅማሬ አለመኖርን ለአሏህ ብቻ የሚያረጋግጥ ይሆናል በማለት ገለፃ እናደርግለታለን”]። በዚህ ርዕስ በዒልማቸው ከጠመሙ ሰዎች መሀከል ኢብን ተ'ይሚያህ አል-ሓራንይ አንዱ ሲሆን በዚህም የፈላስፋዎችን መንገድ በመከተል ዓለም ጅምር የላትም(አሏህ አልፈጠረውም) በማለት "መጅሙዑ'ል ፈተዋ" በተሰኘው ኪታቡ ላይ ሙጀለድ 10 ገፅ 142 ላይ እንዲህ ሲል ያሰፍራል፦ ففي كتابه المسمى مجموع الفتاوى، المجلد العاشر، صحيفة 142، يقول ابن تيمية(وإن قدر أن نوعها لم يزل مع الله فهذه المعية لم ينفها شرع ولا عقل) وهذا من أشنع الكفر. [“የዓለም መሰረቱ ጅማሬ የለውም የሚለው ታሳቢ ተደርጎ ከሆነ "የዓለምን መሰረት ጅማሬ አለመኖር ሸሪዓም ሆነ አዕምሮ አይክደውም”]። በማለት ሽምጥጥ አድርጎ እረ ሸሪዓ እራሱ የዓለምን ጅማሬ አለመኖር አይክድም፤ አዕምሮ ሊክደው ይቅርና!? በማለት እጅ በአፍ በሉት እጅ በእግር የሚያሲዝ ዓቂል ሊያምንበት ቀርቶ እብድ ሊናገረው ሚከብድ ሃሳብ ሲያንተርስ ይታያል። ይህን የመሳሰሉ ጥመቶቹን በይፋ ለተመለከተ ዘይኑዲን አል-ዒራቅይ ስለ ኢብን ተ'ይሚያህ "ኣል-አጅዊበቱል-መርዲያህ" ብለው በሰየሙት ኪታብ ላይ እንዲህ በማለት መሳለቃቸው እውን ነው ያስብላል፦ عِلْمُهُ أكبرُ من عقلِهِ [“እውቀቱ ከጭንቅላቱ የበለጠ ነው”] ውዳሴ መስሎህ እንዳትሞኝ ይልቅንስ ጆሮ ሚያሲዝ ውግዘት እንጂ።የሆነው ሆኖ ነብይ የተላከለትና ተኣምራትን ከሙሳ ዓለይሂ ሰላም የተመለከተም ፊርዓውን ፈጣሪ ነኝ ከማለት አልተመለሰምና፤ ነገርዪው በእውቀት ብቻ ምንከላከለው ሳይሆን ቁልፉ ያማረ አሟሟት መሆኑን መዘንጋት የፊርዓውንና የኢብን ተ'ይሚያህን መጨረሻ ላየ ሚደበቅ አይሆንም።ለዛም ነው የገትይ ደረሳ የሆኑት አ'ሸይኽ ጀውሃር ብኑ ሓይደር፦ يَا ربّنَا بِحُسنِ الختامِ [“ጌታችን ሆይ መልካም አሟሟትን”] በማለት ቀን ከሌት ሲማፀኑ የመዋላቸው ሚስጥር፤ በመሆኑም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ለኢብን ተ'ይሚያህ የተለያዩ ማዕረጎችን በመለጠፍ ለዚህ ግልፅ ለሆነው የኩ*ፍ*ር ንግግሩ ለመከላከል ሲጋጋጥ ያገኘሁት #አደም ሙሐመድ ይህን ንግግር ባልሰማ ጆሮ ዳባ በማለት ኢብን ተ'ይሚያህን ሸይኽል ኢስላም ብሎ እስከመሰየም የመዳፈሩን ጉዳይ ስንመለከት ይህ ከናዳ ማውረድ ዑለማእን ኮርስ የመስጠት የዳና መውረድ አጀንዳ በነርሱ ላይ የተያዘ ስላቅ እንጂ ለፍሬ የታጨ ጉዳይ አለመሆኑ ልብ ያስብለናል። በነገራችን ላይ ከኮርሱ ስላቅ በፊት በብዙ ጉዳዮች ላይ ከጅምሩ የውድቀትን መንገድ እያስተናገደ የመጣው አደም ሙሐመድ በቅርቡ "ዶዋቢጡ ተክፊር" ብላ በተሰየመችው ሪሳላህ ስለ መክፈርያ ነጥቦቹ ሲዘረዝር ለሰማው ጉድ ለካ ጅህልናም እንዲህ ይሰፍራልን በማለት ማስተዛዘቡ አይቀሪ ነው። እንዲሁ አንዱ ከሌላው ሚጣረስና ከተሕቂቅ በፀዱ ንግግሮች መመርኮዙን ላስተዋለ የዒልም ሰው ሳይሆን የህልም ሰው መሆኑን ያውጃል። በመሆኑም የዓለምን ጅማሬ አለመኖር የሚያምነው ኢብን ተ'ይሚያህ ከራሱ አልፎ እነ ተቂዩዲን ኣ'ሱብክይም ይህን ንግግሩን በምስክርነት አኑረውታል።ይህንንም መካድ የነኚህን ታላላቅ ዑለማእ አመኔታ ማራቆት ተደርጎ ያስወነጅላል። ኢብን ተ'ይሚያን በዚህ ንግግሩ ላለማክፈር ዑዝር ለመፈለግ አደም ሙሐመድ ያነሳቸውን ማስረጃ ለተመለከተ በግዜ አቁሙሉን የሚል ጠያቂም ከተመልካች አይጠፋም። ከዛ ውስጥ አንዱ የእናታችን ዓኢሻህን (አሏህ በሰዎች የውስጥ ሚስጥር) ምንም ነገር ከእርሱ እንደማይደበቅበት አታውቅም ነበር በማለት ነብዩም "አሏህ ያውቃልን" በሚለው በዚህ ጥያቄዋ "አዎ ያውቃል" የሚል መልስ እንጂ አላከፈሯትምና: አንዳንድ በጅህልና ዑዝር ሚሰጡባቸው ባህሪዎች አሉ

«ባንቱ በመቅራቴ ልቅና ይሰማኛል» "እኛ የአሏህ ነን ወደ አሏህም ተመላሾች ነን" የአስ-ሱናህ ቲቪ ኸሚስን በአስ-ሱናህ ባልደረባ የነበሩትና በበርካታ የዲን ማዕከላት እንዲሁም የሚዲያ አማራጮች ዲንን
«ባንቱ በመቅራቴ ልቅና ይሰማኛል» "እኛ የአሏህ ነን ወደ አሏህም ተመላሾች ነን" የአስ-ሱናህ ቲቪ ኸሚስን በአስ-ሱናህ ባልደረባ የነበሩትና በበርካታ የዲን ማዕከላት እንዲሁም የሚዲያ አማራጮች ዲንን በማስተማር ላይ የነበሩት ኡስታዝ ሙሐመድ ሰዒድ ባጋጠማቸው ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይዎታቸው አልፏል።በኡስታዛችን ሙሐመድ ሰዒድ ሕይዎት ማለፍ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅኩ ለቤተሰቦቻቸው ፤ ለተማሪዎቻቸው ፤ ለዕውቀት ጓዶቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እመኛለው አሏህ ሶብሩን ይለግሳቸው ዘንድም እማፀናለው ሁላችንም ፋቲሃ ቀርተን ለኡስታዛችን ዱዓ እናድግላቸው። ..................................................................... إن العلماء ورثة الأنبياء وإن الأنبياء لم يورثوا دينارا ولا درهما إنما ورثوا العلم ዑለማዎች የነብያቶች ወራሾች ናቸው ነብያቶችም ዕውቀትን እንጂ ለዑመቶቻቸው ገንዘብን አላወረሱም። የሁሉም ነብያቶች እምነት የሆነዉን ኢስላምን በማስፋፋትና በማስተማር አይነተኛና የማይተካ ሚና ያላቸው ዑለማዎች ናቸው። ወደ አኼራ ያለፉትን የአሏህ እዝነት አይለያቸው ያሉትንም አሏህ ያቆይል አሚን። HAMZA ...ASEDULLAH

① [“ይህ ንግግር ልክ ሙጀሲማዎች አሏህን ጅስም ላ ከል አጅሳም እንዳሉት ነው።አንዳንዶች አህሉ ሱናዎችን አሏሁ ሸይኡን (ያለ ነው) ላ ከልአሽያእ (ነገር ግን ያሉትን አይመስልም) ሲሉ በሰሙ ግዜ እኛም ጅስሙን ላ ከል አጅሳም እንላለን በማለት ጅስም የሚለው መውጁድ በሚለው የሚመጣ አድርገው በማሰብ መናገር ጀመሩ“]። ስለዚህ ሸይእ ማለት ያለ ማለት ሲሆን:ዑለማዎች አሏሁ (ሸይኡን ላ ከልአሽያእ) ሲሉ አሏህ ያለ ነው ያሉትን አይመስልም በሚለው ትርጓሜ ይጠቀሙታል። ይህን የሰሙ ዓረበኛ ቋንቋ ላይ ጥልቅ እውቀት የሌላቸው ከፊል ከራምያዎችን የመሰለ አህሉ ሱናዎች (ሸይእ) በማለት መውጁድ ሚልን ነው ምንፈልግበት ስለሚሉ:እኛም (ጅስሙን ላ ከል አጅሳም) ብለን መውጁዱን ላ ከል መውጁዳት የሚልን ትርጓሜ ይዘንበት እንጠቀመዋለን በማለት ለአሏህ ጅስም የሚለውን ስያሜ በመስጠት ትርጉሙንም መውጁድ በሚል ነው ሲሉ ከብዙ ዑለማዎች ጋር ሙግትን ጀመሩ።ዑለማዎችም ይህን ሲናገር በሰሙት ላይ በብዙ መልኩ ሲፃረሩ ብሎም እያወቀ ከሆነ እንደሚከፍር ገለፁ።ይህም ጅስም ማለት መውጁድ በሚል ትርጓሜ ፈፅሞ ስለማይመጣ ነው። 📍ቀጥሎም ኣቡ መንሱር ስለነርሱ በዚህ መልኩ የሚያስቀምጡትን ገለፃ እንመልከት፦ قال البغداديُّ في التَّبصرة البغداديَّة المُسمَّاة [أُصول الدِّين]: <وقد شاهدنا قومًا مِن الكرَّاميَّة لا يعرفون مِن الجسم إلَّا اسمه ولا يعرفون أنَّ خواصَّهم يقولون بحُدوث الحوادث في ذات الباري تعالى. ② ኣ·ቡመንሱር ኣል–ባغዳድይ ኣ·ተብሲረቱ ኣል ባغዳድያህ ኡሱሉ ኣ·ዲን ብለው በሰየሙት ኪታባቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦ ["በእርግጥም ከከራምያህ የሆኑ ሰዎችን ተመልክተናል "አሏሁ ጅስሙን" ሲሉ ጅስም ከሚለው ቃል ስሙን መወርወር ብቻ እንጂ የቃሉን ትርጓሜውን ማይገነዘቡ የሆኑትን።እነኚህ ሰዎች ጅስም ሲሉ የቃሉን ዋና የሆነውን ትርጓሜ ግኝ ነገራቶች ፈጣሪ ላይ ይከሰታል የሚለው አይገነዘቡበትም።(ምክነያቱም አካል ማለት ግኝ ስለሆነ)። እነርሱ አሏሁ ጅስሙን ሲሉ አሏህ ያለ ነው።አልያ በራሱ የተብቃቃ ነው ሚለውን በራሳቸው ያመጡትን (የፈበረኩትን) ፍቺ ነው ሚረዱበት።ቃሉ ማለትም ጅስም ማለት በዚህ ትርጉም ባይመጣም) فهؤُلاء يحِلُّ نكاحُهُم وذبائحُهُم والصَّلاة عليهم> انتهَى فهؤُلاء الَّذين لم يُكفِّرهُمُ الأشاعرة. ሲሉ አስከትለው ኣል–ባዳድይ እንዲህ አሉ፦እነኚህ ሰዎች ጋብቻቸውም፣ እርዳቸውም እንዲሁ ከሞት በእነርሱ ላይ መስገድም ይበቃል"]። ๏ ወንድሜ እነኚህን ሙጀሲማዎችን ነው ኣሻዒራዎች ያላስከፈሩት።ከቃሉ የአካልነትን ትርጓሜ የሚገነዘቡትን አይደለም።ይልቅንስ የአካልነትን ትርጓሜ የማይገነዘቡትን ነው። የሃገሬው ሙጀሲማህ ጋር ይህ ፍርድ ምንም ግኑኝነት የለውም።የሃገሬው ሙጀሲም በግልፅ አሏህን እጅ፣እግር ወዘተ አለው እያለ ግኝነትን ለአሏህ የሚያረጋግጥ ነው።እንዴት አይከፍርም ይባላልን?! ።አስተውል።!በዚህ ቦታ ላይ የተጠቀሰው ሁሉም ከራምያዎችን አያካትም። ከነዚህ ከራምያዎች ከሚባሉት ቡድኖች መሀከል አሏህን በጅስም እየገለፁ የቃሉን ትርጓሜ በደንብ ሚረዱ አሉ።እነርሱ ካፊሮች ናቸው።ከላይ ኢጅማዑ መጠቀሱን አትዘንጋ። ¤ በጥቅሉ ስለ ሙጀሲማዎች ያለው ማብራርያ ይህን ይመስላል።ስለ ሀገራችን ውሃብያ ሲጠቀስ "ስቅ" እና "ትን" ሚላቸው ሰዎች በጣሙን ሚገርመው ሽንጣቸውን ገትረው አንዳቸውም ሙጀሲም አይባሉም ሲሉ ቀን ከሌት ይሞግታሉ።ብሎም ዑለማዎችም ካፊር ሲሉ የሀገራችንን እነኚህን ሙሸቢሃ አያካትም እስከማለት ደርሰዋል።ነገር ግን ከፊል ውሃብያ ሙሸቢሃዎች በግልፅ ለአሏህ ጀሀነም ውስጥ ሚከተው እግር እንደሚያደርጉለት የሚከፍተው ባትና እንደ ሊፍት መውጣትና መውረድን በዛቱ በማለት እንደሚሰጡ ይታወቃል።እነርሱም ሙጀሲም ናቸው። በኩፍራቸውም ላይ ምንም ሸክ የለውም።እነኚህ ሙጀሲም ካልተባሉ ማነው ሙጀሲም ሚሰኘው?! ለዚህም ከላይ የተቀመጠውን ብያኔ መመልከት በቂ እገዛ ያደርጋል። ሸይኻችን አሸይኽ ዓብዱሏሂ ኣል ሃረሪይም በዚህ ነጥብ ላይ ነው ያሉት።ለዚህም አንድን የኩፍር ቃል የተናገረ ሰው ነገር ግን ለዛች ኩፍር ቃል ሌላ ኩፍር ያልሆነ ትርጓሜ አሏት በማለት ቢጠቀማት ልክ አሏህን ጅስም ብለው መውጁድ በሚል ትርጓሜ የሚመጣ መስሎን ነበር እንዳሉት እነኚህም አይከፍሩም።ኣሲራጥ፣ ኣሸርሑል ቀዊም እንዲሁ ሶሪሑል በያን የተሰኘውን የሸይኽ ዓብዱሏህ ኪታብ መመልከት ለዚህ በተገቢው መልኩ የሚረዳ ይሆናል። HAMZA ...ASEDULLAH

وقال شيخ جامع الزَّيتونة الشَّيخ إبراهيم المارغني التُّونُسيُّ في كتابه المُسمَّى [طالع البُشرَى على العقيدة الصُّغرَى]: <ويُسمَّى الاعتقاد الفاسد كاعتقاد قدم العالم أو تعدُّد الإله أو أنَّ الله تعالَى جسم، وصاحب هذا الاعتقاد مُجمع على كُفره> انتهَى. ④ ሸይኹ ጃሚዒ ዘይቱናህ ኣሸይኽ ኢብራሂም "ጧሊዑል ቡሽራ" የተኘው ኪታብ ላይ እንዲህ ሲሉ በዚህ ላይ የተሰጠውን የጋራ አቋም ይጠቅሳሉ፦ [“የተበላሸ እምነት በመባል ከሚሰየሙት ውስጥ ዓለምን ጅማሬ የላትም፣ የፈጣሪን መብዛት አልያ አሏህን አካል ነው ብሎ ማመን የመሰለ: የነዚህ እምነት ባልተቤት በመክፈሩ ላይ #ዑለማዎች ከስምምነት ደርሰዋል”]። وَقَالَ القَاضِي عَبدُ الوَهَّابِ بنُ عَلِيٍّ بنِ نَصرٍ البَغدَادِيُّ المَالِكِيُّ: «وَلَا يَجُوزُ أَن يُثبِتَ لَهُ كَيفِيَّةٌ؛ لِأَنَّ الشَّرعَ لَم يَرِد بِذَلِكَ، وَلَا أَخبَرَ النَّبِيُّ ﷺ فِيهِ بِشَيءٍ، وَلَا سَأَلَتهُ الصَّحَابَةُ عَنهُ، وَلِأَنَّ ذَلِكَ يَرجِعُ إِلَى التَّنَقُّلِ وَالتَّحَوُّلِ وَإِشغَالِ الحَيِّزِ وَالِافتِقَارِ إِلَى الأَمَاكِنِ، وَذَلِكَ يَؤُولُ إِلَى التَّجسِيمِ وَإِلَى قِدَمِ الأَجسَامِ، وَهَذَا كُفرٌ عِندَ كَافَّةِ أَهلِ الإِسلَامِ». انتهى. ⑤ ኣል-ቃዲይ ዒያድ ዓብዱል ወሃብ ብኑ ዓልይ ብኒ ነስር አል-በግዳድይ አል-ማሊኪይ "ሸርሑ ዓቂደቲ አል ኢማም ማሊክ ኣሶጊይር" ላይ እንዲህ ይላሉ ፦ [“እንዴታን ለአሏህ ማፅናት አይበቃም።ምክነያቱም ሸሪዓችን በዚህ ነገር ስላልመጣ።ነብዩም አልተናገሩም ሶሓበቶችም አልጠየቁም።ምክነያቱም ይህ ጥያቄ ከአንድ ሁኔታ ወደ ሌላ ለሚሸጋር፣ ለሚቀያየር፣በአቅጣጫ ለሚወሰን እንዲሁ ወደ ቦታ ለሚከጅል የሚሰጥ ጥያቄ ነው።ይህ ደግሞ አሏህን በአካል ወደ መግለፅ እንዲሁ አካልንም ጅማሪ የለውም ወደማለት የሚመራ ነው።ይህ እምነት ደግሞ #ሁሉም ሙስሊም ዘንዳ ኩፍር ነው”]። 📌 በማለት የጋራ አቋም ሳይቀር በዚህ ላይ የፀና እንደሆነ ብዙ ዑለማዎች ያስቀምጣሉ። ሁለተኛ፦ ②ጅስም የሚለውን ቃል "ይረዳሉ" ። እናም አሏህ አካል ነው ነገር ግን አካሉ እንደኛ አይደለም። (ጅስሙን ላ ከል አጅሳም) በማለት ይናገራሉ። እነኚህ አንጃዎች ከላይ በጠቀስኩላችሁ መሰረት የዓረበኛን ቋንቋ የሚረዱና የተገጣጠመ ነው በሚል ገለፃ እንደሚናገሩ ይውቃሉ።አስከትለውም ላ ከል አጅሳም ወይም እንደኛ አካል ያልሆነ በማለት ለማስተባበል ይሞክራሉ።ጥቅላዊ ትርጓሜውም አሏህ (የተገጣጠመ ነው።ነገር ግን መገጣጠሙ የኛን አይመስልም) እያሉ ነው።እነኚህ ሰዎች ለአሏህ ግልፅ በሆነ በሚረዱት ቋንቋ መገጣጠም የተሰኘን የፍጡር ባህሪ አረጋግጠውለታል።ከዛ አስከትለውም መገጣጠሙ እንዳኛ አይደለም ቢሉ ከአሏህ የመገጣጠምን ባህሪ እንዳላነሱ ይህም ማጥራት እንደማይባል ንግግሩ ያስረዳል። እነኚህንም በማክፈር ላይ ዑለማዎች በብዙ መልኩ አቋማቸውን አስቀምጠዋል።ልክ ጅስም ነው። እንዳሉ የመጀመርያ ሰዎች በመሆናቸው ላይ ጥርጥር የለውም።ቋንቋ እየተረዱ ላ ከል አጅሳም ማለታቸው ዋጋ ቢስና የመክፈርን ሑክም ከነርሱ እንደማያነሳ ይገልፃሉ ከነርሱም በውስጥ፦ قال الشنقيطي في زاد المسلم" ولا قيمة لقول من قال: إن المجسم لا يكفر إلا أن قال: إنه جسم كالأجسام" ① ኣሸይኽ አሸንቂጢይ "ዛዱል ሙስሊም" የተሰኘው ኪታባቸው ላይ የስዩጥይን የሙጀሲም ማክፈር የዑለማን የጋራ አቋም ካሰፈሩ ቡሀሏ እንዲህ በማለት ይናገራሉ፦[“ሙጀሲም አሏህ እንደኛ አካል ካለ ይከፍራል።ነገር ግን እንደኛ አይነት አካል አይደለም ያለ ከሆነ አይከፍርም የሚለው ንግግር ዋጋ የለውም”]። 📍ማለትም አሏህን አካል ነው።ነገር ግን እንደኛ ያልሆነ ቢልም ከመክፈር አይድንም።"የኛን ማይመስል አካል" በማለቱ አጥርቷልና አይከፍርም የሚልም ሰው ንግግሩ ዋጋ አይሰጠውም በማለት በግልፁ ፅፈዋል። ذكر الإمام بدر الدّين الزركشيّ في تشنيف المسامع من نصّه؛قال الإمام أحمد "من قال الله جسم لا كالأجسام كفر" ② ታላቁ ኢማም በድሩ ዲን አ·ዘርከሽይ "ተሽኒፉል መሳሚዕ" ላይ የኣል ኢማም አሕመድ ብኑ ሐንበልን ንግግር እንዲህ ሲሉ ያስቀምጣሉ፦[“አሏህ አካል ነው።እንደኛ ያልሆነ ቢልም ይከፍራል”]። قال أبو شكور السالمي في التمهيد: ومنهم من قال بأنه جسم لا كالأجسام، هذا كفر لأنه وصف الله بالرأي بما لم يصف به نفسه وما اتفقت عليه العلماء» اهـ ③ ኣቡ ሸኩር አ·ሳሊሚይ ተምሂድ በተሰኘ ኪታባቸው ውስጥ ይህን ይላሉ፦[“ከነርሱ መሀከል አካል ነው ነገር ግን እንደ አካል አይደለም ያሉ አሉ።ይህ ደግሞ ኩፍር ነው።ምክነያቱም አሏህ እራሱን ባልገለፀበት:እንዲሁ ዑለማዎችም አሏህን በዚህ ባህሪ መገለፁ ላይ ባልተስማሙበት ነገር በራስ ግምት ስለተናገረ ነው”]። ስለዚህ የነኚህ ሙጀሲማዎችም ፍርድ ከመጀመርያዎች ሙሶሪሖች ከተባሉት እንደማይለይ በግልፅ ዑለማዎች አስፍረዋል። አሏህን የተገጣጠመ ነው ነገር ግን መገጣጠሙ የኛን አይመስልም እና መገጣጠሙ የኛን ይመስላል በሚሉት መሀከል ምንም አይነት ልዩነት የለም።እነዚህንም ቡድኖች የሙሶሪሕ ሰዎች ፍርድ ያጠቃልላቸዋል።እነኚህም በተመሳሳይ መልኩ ካፊር ናቸው የሚል ነው። ሶስተኛና የመጨረሻው ቡድን፦ ③ (አሏህን ጅስም ነው ነገር ግን ላ ከል አጅሳም) በማለት ይናገራሉ።ከሁለተኛ አንጃዎች ለየት ሚያደርጋቸው ዓረበኛ ቋንቋን በደንብ ስለማይረዱ ጅስም በሚሉበት ግዜ አሏህን ያለ ነው የእርሱ መኖር የኛን አይመስልም ማለትን እንደሆነ ሚረዱት ይገልፃሉ።በዚህም ብዙ ዑለማዎች ትርጉሙ አሏህ ያለ ነው ሚለው ባህሪ ላይ ብንስማማችሁም ነገር ግን "መኖር" ለሚለው ፍቺ ጅስም ነው ሚለውን ገለፃ መጠቀማቹህ ቋንቋው አይቀበለውም። ምክነያቱም ጅስም የሚለው መኖር በሚል ትርጓሜ አይመጣምና።በማለት ከነ ኣቡ መንሱር አል በግዳድይ እስከ ራዝይ ከኢማሙል ሐረመይን እስከ ነወዉይ ኪታባቸው ላይ የማለታቸውን ምክነያት ጨምሮ እንዴት እንደሚመለስላቸው ይናገራሉ። እነኚህንም ቡድኖች ሓጢያተኛ ሙብተዲዓህ እንጂ ካፊር ናቸው በማለት አይሰይሟቸውም። ከነርሱ መሀከል አል ኢማሙ ኣነወውይን "ሸርሑል ሙስሊም" ላይ ሚጠቅሱትን እናስቀምጥ፦ قَالَ (المازِرِيُّ): *"وَهَذَا كَقَوْلِ الْمُجَسِّمَةِ جِسْمٌ لَا كَالْأَجْسَامِ لَمَّا رَأَوْا أَهْلَ السُنَّةِ يَقُولُون: البارِئُ سُبحانَه وتَعالى شَىءٌ لَا كَالْأَشْيَاءِ، طَرَدُوا الِاسْتِعْمَالَ (أي قاسُوا هذه علَى تِلكَ فأَجْرَوْها في الاسْتِعْمالِ) فَقَالُوا: جِسْمٌ لَا كالاجسام،

መረጃ ይዳኘን ክፍል ⑨ ትልቁ ሰው ከተናገሩት ነብያዊ ትውፊቶች መሀከል የኡመቶቻቸው በ 73 ፊርቃህ መከፈል አንዱ ሲሆን: በዚህም እውን ነው: በማለት ያለ አንዳች ማስተባበል መቀበል ከኛ ምእመናን የሚጠበቅ የውዴታ ግዴታም ጭምር ነው። ትልቁ ሰው እነዚህ ቡድኖች በየትኛው ነጥብ ከእርሳቸው ቀጥተኛው መንገድ እንደሚያፈነግጡ በዝርዝር ባይገልፁም: ነገር ግን የነብያት ወራሽ የሚሰኙት ዑለማኦች በዘመናቸው ከተገናኟቸው አንጃዎች ጋር ባደረጉት ውይይት የጥመት መነሻቸው እንዲሁ አስተሳሰባቸውን ከጠንሳሹ እስከ ተከታዩ ከአዋቂያቸው እስከ ጃሂላቸው ምን አይነት የልዩነት ዘይቤ እንደሚያራምዱ የሑክሙንም ልዩነት በዛው ልክ አስፍተው በመስጠት ኪታቦቻቸውን በማዘጋጀት አልፈዋል። ከነዚህ የጥመት አንጃዎች ውስጥ ከፊሉ የጥመቱ ደረጃ ወደ ኩፍር ያደረሰው ከፊሉ ደግሞ የሙብተዲዕ ደረጃ እንጂ ኩፍር የማያደርሰው ሲሆን ይህንም ከነ አል-በግዳድይ እስከ ገዛልይ ብዙ ትንታኔዎችን በመስጠት ጥቂት ማይሰኙ ኽልቆችም የተናገሩበት ትልቅ ርዕስ ጭምር ነው። ምክነያቱም የነኚህ አንጃዎች ጥመት መለየት እንዲሁ በያን ማድረግ በመጀመርያ ሸሪዓው ላዘዘን በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ለሚለው ህግ ተገዢ መሆናችንን የሚያሳይ ሲሆን በመቀጠልም ሰዉ በመታለል የመልዕክተኛው አስተምህሮት የጠማሞች አስተሳሰብ መስሎት እንዳይከተላቸውም ጭምር ትልቅ ግብን ያነገበ ይዘት ያለው ነው። እነኚህ ዑለማዎች በኪታቦቻቸው ከሚያነሷቸው አንጃዎች መሀከል "ሙጀሲማህ አልያ ሙሸቢሃ" የሚሰኙ ቡድኖች ይገኙበታል።አሁን ባለንበት ዘመንም በትላልቅ የስልጣን እርከኖች ላይ በመቆናጠጥ ሙስሊም ማህበረሰቡን በነርሱ የተሸቢህ እንዲሁ ተጅሲም እምነት ለማጥመቅ ሲሯሯጡ ማየት የተለመደ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው። እነኚህ ቡድኖች ከትልቁ ሰው ዕምነት ካፈነገጡባቸው ነጥቦች መሀከል ትልቁ እና ዋነኛው የዓቂዳህ ርዕስ በዋነኝነት የሚጠቀስ ሲሆን: ይህም መልዕክተኛው ዓለይሂ ሶሏቱ ወሰላም የሚገዙት ጌታቸውን አሏህ ከቦታ፣አቅጣጫ፣ አካልነት ከመውረድና እንዲሁ ከመውጣት እጅጉን አጥሪ ሲሆኑ እነኚህ ሙጀሲማህ የሚሰኙት አንጃዎች ደግሞ "አሏህን" መልዕክተኛው ባልገለፁበት መልኩ አሏህን በዛቱ መውጣትና መውረድን፣ብሎም መቀመጥና በአየር ላይ መንሳፈፍ አካልነትንም ጭምር ያረጋገጡ ሆነዋል። ይህም የተሽቢህ አካሄድ ከትልቁ ሰው እምነት እንዲሁ እርሳቸውን በዚህ ላይ ከሚከተላቸው ብዙሃኑ የአህሉ ሱና ዑለማእ አካሄድ ያፈነገጠ አስተሳሰብ በመሆኑ ላይ ሁሉን ሚያስማማ ጉዳይ ነው። ይህ ጉዳይ በሻፊዕይ እና በኣቡ ሓኒፋህ እንዳለው የውዱእ ማጥፋትና ያለማጥፋት የፊቅሃዊ ልዩነት እንዳልሆነና በመሰረታዊ የፈጣሪ ባህሪን በማወቅ ላይ እጅጉን የተራራቀ ልዩነት እንዳለ በግልፅ የሚያስረዳ ነው። ይህን የኢጅቲሀድ ጉዳይ ነውና የሳተው አንድ አጅር ሚያገኘው ደግሞ ሁለት አጅር አለው ሚያስብልም አይደለም።ዋናው ልዩነት ፈጣሪ ተብሎ ስያሜ የተሰጠውን "ዛት" (ማፅደቅ እና መካድ) ላይ ሆኖ ትልቁን ልዩነት ታገኘዋለህ። ዑለማዎች በነዚህ አንጃዎች ላይ ማለትም አሏህን ጅስም ነው አልያ አካል ነው: በማለት የሚገልፁት ላይ ቋንቋውን ተረድተው እስከሚናገሩበት ድረስ እንደኛ አካል አንፈልግበትም ቢሉም እንኳ ከሙጀሲማነት ስያሜ እና ለነርሱ ከሚሰጣቸው ፍርድ የሚድኑ ሆነው አይገኙም። ምክነያቱም ጅስም ማለት "የተገጣጠመ" የሚልን ፍቺን የሚሰጥ ሲሆን: አንድ ሰው አሏህን የተገጣጠመ ነው ነገር ግን "እንደተገጣጠሙት" አይመስልም አልያ ብዪ አልልም ቢል ለአሏህ የፍጥረታት ባህሪ የሆነው ለአካል ሚሠጥን መገጣጠም የተባለ ነገር ወደርሱ አስጠግቷልና ይህ ሰው ከዛ ቡሀሏ (ላ ከል አጅሳም) በማለቱ አጠራ ልንለው አይቻለንም። 📌 ዑለማኦች ሙጀሲም የሚሰኙትን አንጃዎች በሶስት የተለያየ ቡድንና እንደ ጥመታቸው ደረጃ በመለየት በተለያየ የሑክም ደረጃም የሚያስቀምጧቸው ሲሆን እነርሱም፦ የመጀመርያው አንጃ፦ ① ሙጀሲም ሙሶሪሕ፦አልያ አሏህን ጅስም ነው ልክ እንደኛ አይነት ጅስም የሆነ፤ ማለትም አካል ነው ልክ በኛ አይነት አካል የሆነ (ጅስሙን ከል አጅሳም) በማለት ይገልፃሉ።ዑለማዎች በነኚህ አንጃዎች በመክፈር ላይ ምንም አይነት ልዩነት አላሳዩም። ምክነያቱም አሏህን አልተገዙም። እነርሱ ጋር አሏህ አካል እንጂ ከአካል ሆነ ከአካል ባህሪያት የጠራ ነብያቶች የተገዙት ሙስሊሞች በሀቅ የሚያመልኩት አይደለም ፈጣሪ ብለው የሚያምኑበትም አይደለም። ዒባዳን ከአሏህ ውጪ ላለ ነው የሰጡትና በዚህም ከሃዲ ካፊር ናቸው: በማለት ዑለማዎች የጋራ አቋምን አስረዋል። ይህንም ካስተላለፉልን መሀከል፦ قال الإمام أبو جعفر الطحاوي رحمه الله : " وَمَن وصفَ اللهَ بِمَعنًى من معاني البَشَرِ فقد كَفَر " ① አል-ኢማሙ ኣቡ-ጃዕፈር ኣ'ጦሐውይ "ኣል-ዓቂደቱ ኣ'ጦሓውያ" በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዲህ ሲሉ በሙጀሲማዎ መክፈር ላይ የዑለማዎችን የጋራ አቋም ያስቀምጣሉ፦ [“አሏህን ከፍጡር ባህሪ በአንዱም ቢሆን የገለፀ በእርግጥም የከፈረ ይሆናል”]። قال ابن حجر الهيتمي (ت 974 هـ) في المنهاج القويم: «واعلم أن القرافي وغيره حكوا عن الشافعي ومالك وأحمد وأبي حنيفة رضي الله عنهم القول بكفر القائلين بالجهة والتجسيم، وهم حقيقون ② ኣ·ሸይኽ ኢብኑ ሐጀር አል-ሃይተሚይ "974" ሂ የሞቱት በ ኣል ሚንሃጁ ኣል ቀዊም ሸርሒል ሙቀዲመቲል ሓድረሚያህ ላይ እንዲህ በማለት የዑለማዎችን የጋራ አቋም ያስተላልፋሉ ፦ እወቅ [“ቀራፊይ እንዲሁ ሌሎችም #ከሻፊዒይ፣ #ማሊክ፣#አሕመድ እንዲሁ #ከኣቡ ሓኒፋህ ረዲየሏሁ ዓንሁም በመያዝ አሏህን በአቅጣጫ እንዲሁ በአካል የሚገልፅ ሰው እንደሚከፍር አስተላልፈዋል”]። قال أبو حَامِدٍ الغَزَالِيُّ (ت: 505هـ) في كتابِهِ المسمَّى إِلْجَامَ العَوَامِّ عَنْ عِلْمِ الكَلَامِ ما نَصُّهُ: «فَإِنْ خَطَرَ ببالِهِ أَنَّ اللهَ جسمٌ مُرَكَّبٌ مِنْ أعضاءٍ فهو عابدُ صَنَمٍ؛ فَإِنَّ كُلَّ جسمٍ هو مخلوقٌ، وعبادةُ المخلوقِ كفرٌ، وعبادةُ الصنمِ كفرٌ لأَنَّهُ مخلوقٌ، وكان مخلوقًا لأَنَّهُ جسمٌ، فَمَنْ عَبَدَ جسمًا فهو كافرٌ بإجماعِ الأُمَّةِ السَّلَفُ منهم والخَلَفُ».اهـ ③ ሑጀቱል ኢስላም ኣቡ ሓሚድ ኣል-ገዛልይ 505 አመተ ሂጅርያ ላይ የሞቱት በስተ መጨረሻ ከፃፉዋቸው ኪታቦች መሀከል አንዱ በሆነው "ኢልጃሙል ዓዋም" ላይ እንዲህ ይላሉ፦ [“በአዕምሮ ላይ አሏህን ከክፍለ አካላት የተገጣጠመ ነው ብሎ ካመነ ይህ ሰው ጣዎትን አምላኪ ነው። ሁሉም አካሎች ፍጡሮች ናቸው።ፍጡርን መገዛት ደግሞ ኩፍር ነው።ጧኦትን ማምለክ ኩፍር ነው ምክነያቱም ፍጡር ስለሆነ። ፍጡር የሆነውም አካል ስለሆነ ነው።አካልን የተገዛ ደግሞ #በዑለማዎች የጋራ አቋም ከሀዲ ነው”]።

“አሏህ ሲሰደብ አደብ፤ ሐሪማ ሲበላሽ ጥሰት” ምኑ ላይ ነው አደቡ? ከሰሞኑ በየሐሪማው እየተንፀባረቀ የመጣውን “ኢስላማዊ መሰረት የሌለውን” የምትል ገለፃን ከኢኽወንጅዩ አደም በቀኝ እጁ ከሚመራው ከ
+1
“አሏህ ሲሰደብ አደብ፤ ሐሪማ ሲበላሽ ጥሰት” ምኑ ላይ ነው አደቡ? ከሰሞኑ በየሐሪማው እየተንፀባረቀ የመጣውን “ኢስላማዊ መሰረት የሌለውን” የምትል ገለፃን ከኢኽወንጅዩ አደም በቀኝ እጁ ከሚመራው ከካስማ ገፅ ካነበብኩ ቡሀሏ በእውኑ መቀጠል ተስኖኛል። የሐበሻ መሻይኾች ሐሪማዎቻቸው ላይ አሏህን ሚሳደብ ሆነ በጉለት ባህሪ የሚገልፅ ሙስሊም አይደለም።እስልምናም ይህን አላስተማረም።ከአሏህ ጋር አደብ ከሌለው የምን ወንድማዊ አደብ ነው?! ይህም ከነ ሸይኽ ቀልቀልሻ እስከ ሸይኽ ዓብዱል ዓዚዝ እንደ ብሌናቸው የጠበቋት ሲጠብቋትም ያሉት የእምነታቸው ምሰሶ ናት።እኛም በዛ መንገድ ከተመሪዎች ነን።ከካፈሩን ጀርባ በመሆን አንሰግድም። ይህን መሰል ከቀደምቶች ያልታየን አስተሳሰብ አደም ለአላማው አስቦ ነገር ግን የሾለ እውቀትን ከያዙ አንደበቶች የተሰጠው ገራፊ ውግዘት ነው።ሸይኽ ቀልቀልሻህ ውሃብያ በዚህ ስያሜዋ ከመጠራቷ በፊት መካ ውስጥ ስላለ ሙጀሲም ስሙን ሲጠሩት “ሙዕተዚላህ” ማለታቸው መዘንጋት ፈፅሞን የለበትም። አደብ የሚቀድመው ከአሏህ ጋር ነው።የአሏህን ታላቅነት ፈርቶ ያልተቆጠብ የሐሪማ ባልተቤቶችን ደም ከማፍሰስ ወደሀሏ እንደማይል ቅሮት የለውም።የሐሪማ አደብ ተጣሰ ከማለት የሓሪማ ባልተቤቶችን የሰበሰበው ኻሊቀል ከውን አሏህን የእርሱ ድንበር መጣሱ ሊያሳስባቹህ በተገባ ነበር። Hamza ....asedullah

በማለት ኣሱብክይ ይህ የተክፊር ጉዳይ "ሙስሊም ማሕበረሰቡም ዘንዳ"በማለት ለቃድይ ብቻ ነገርዪውን ጥለው እንዳላለፉ ያስረዳል።ይልቅንስ የኩፍር ውሳኔ ሚያሳርፍበት ነገር የተናገረ እንደሆነ ይህን ሰው በሐቅ ማክፈሩ አይከለከልም።ይህም ፈኽሩዲን በነ ሱብክይ ንግግር ላይ ያለው የአረዳድ ክፍተትን አጉልቶ ያሳያል።ሆኖም ሙስሊም ዘንዳ መባሉ ቀዋዒዱን ያሟሏ በመሆኑ ላይ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።የሁሉ መዋኛ ገንዳ አይደለም።የተክፊር በር ልቅ እንዳልሆነ የኩፍሩንስ ቃል የተናገረ ሰው በምላስ ወለምታ፣በግዳጅ፣ በሒካያህ በኢጅቲሃድ፣ በአቅል መራቅ አልያስ በማለት ከስሮቻቸውም የተለያዩ ገደቦች በመዘርዘር እነኚህ የእውቀቱ አምባ የማክፈርያን እንዲሁ ያለማክፈርያን ነጥብ በዝርዝር ያስቀምጣሉ። ለዚህም የሐበሻው የዒልመል ሓዲስ ኻዳሚ ሚሰኙት ኣሸይኽ ዓብዱሏህ አል ሃረሪይ ኣሲራጥ፣ ሶሪሑል በያን፣ቀዋዒድ እንዲሁ ሌሎችንም ኪታቦቻቸው ይህን በተመለከተ የሰጡትን ማብራርያ መመልከት ያስፈልጋል።እርሳቸውም ያለ ሐቅ የማክፈርን አደገኝነት እንዲህ በማለት ይናገራሉ፦ ثم إنَّ الحكمَ على شخصٍ بالكفرِ أو الإسلامِ إنْ كان مُسْتندًا إلى دليلٍ فذاك صوابٌ عندَ اللهِ، وإن كانَ لا يستندُ إلى دليلٍ فهو هلاكٌ على صاحِبِهِ. قالَ العلماءُ: إدخالُ كافرٍ في الملّةِ أمرٌ عظيمٌ وإخراجُ مسلمٍ عنها أمرٌ عظيمٌ. المعنى أنَّه لا يُحكمُ لشخصٍ بأنَه مسلمٌ بدونِ دليلٍ شرعيٍ ولا يُحكَمُ على مسلمٍ بالكفرِ إلا بدليلٍ شرعيٍ. [«አንድ ሰው ላይ በኩፍር አልያ በኢስላም መፍረድ በማስረጃ ተደግፎ ከሆነ ትክክለኛውም መንገድ እርሱ ነው።ማስረጃን ተመርኩዞ ካልሆነ ግን ባለቤቱ ላይ ጥፋትን ታስከትላለች።ለዛም ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል፦"ለአንድ ሰው በእስልምና መፍረድ ከባድ ነው።በኩፍርም እሱን መፈረጅ ከባድ ነው"።ይህም ማለት ለአንድ ሰው ያለ ሸሪዓዊ ማስረጃ በእስልምና አይፈረድለትም እንዲሁ ያለ ሸሪዓዊ ማስረጃ ኩፍርም አይታወጅበትም»]። በማለት ሸይኸ ዓብዱሏህ ያስጠነቅቃሉ።ይህም ሊታወቅ ሊገነዘቡት የተገባ ይሆናል።ከውጪ የሚሳለው ሁሉ ቀርበህ ስታይ ውሸት ሲደጋገም እውን ይመስላል የሚለውን አባባል እውን ሆኖ ታገኘዋለህ። ✧ አህሉል ቂብላና መከፈር ሚገባቸው አንጃዎች… ②“አል_ሙጅተሂዱ_ጦበሪይን_ወይስ_ፈኽሩዲንን” በአህሉል ቂብላ ስም የተሸፈነ ሁሏ ሙስሊም ነው የሚል ስያሜ እንደማይሰጠው ይልቅንስ የተውሒዱ ትክክለኝነት በዋነኝነት ለዚህ ስያሜ ጉልህ ሚና እንዳለው የሚያሳዩ ማስረጃዎች ውስጥ አል ሓፊዙ ኣጦበርይ ያሉት ንግግር ሲሆን፤ ይህም ፈኽሩዲን እና ዝና ፈላጊ ወጠጤዎችን በአፍጢማቸው የተከለ ንግግር ነው። قال الحافظ ابن حجر ما نصه [قلتُ وممن جنح إلى بعض هذا البحث الطبري في تهذيبه فقال بعد أن سرد أحاديث الباب - يعني أحاديث الخوارج - فيه الرد على قول من قال لا يخرج أحد من الإسلام من أهل القبلة بعد استحقاقه حكمه إلا بقصد الخروج منه عالما"] ፨ ኣል ሓፊዙ ኢብኑ ሓጀር ከጦበርይ ሲያስተላልፉ እንዲህ ይላሉ፦[“ወደዚህ ፍለጋ ከገቡት መሀከል ኣጦበርይ ተህዚባቸው ላይ ስለ ኻዋሪጆች የተጠቀሱትን ሓዲሶች ካወሱ ቡሀሏ እንዲህ ሲሉ አስፍረዋል፦("በዚህ ላይ የሙርተድነት ፍርድ እየተገባው ወደ ቂብላ ዞር ከሰገደ ከእስልምና ለመውጣት ካላሰበ በስተቀር አይከፍርም: ላሉ ሰዎች መልስን ይዟል”)]። ጦበርይ ኻዋሪጆችን ያለ ምንም መነጠል በጠቅላላቸው ካከፈሩ የሰለፍ ዑለማዎች ውስጥ አንዱ ነበሩ።በዚህም ላይ ወደ ቂብላ የዞረ ሁሉ ሙስሊም ነው በማለት: ሽንጣቸውን ገትረው ለሙጀሲሙ አለመክፈር ለሚሞግቱና፣እንዲሁ የሙስሊምን የመክፈርን ቅድመ ሁኔታ ሲጠቅሱ ኩፍር መሆኑን አውቆ ካልሆነ አይከፍርም፤ ለሚሉ ሰዎች መልስ በዚህ መልኩ የሰጡበት መሆኑን ልብ ልትል ይገባል። ③ ኣቡ ሓሚድ ኣል ገዛልይ ወደ ቂብላ ዞሮ የሚሰግድን በኩፍር መፈረጅ እንዲሁ ደሙን ማፍሰስ ስህተት ነው።ሲሉ የትኞችን የቂብላ ሰዎችን ነው በማለት በማስተንተን ፋንታ የፈኽሩዲን ጨለምተኛ አስተሳሰብ አሁንም እርሳቸው ያልፈለጉበትን በህቡእ ኪታቦቻቸው ላይ መቅጠፍን ከአጋሮቹ ጋር ተያይዞታል። قال الغزالي في كتاب التفرقة بين الإيمان والزندقة والذي ينبغي الاحتراز عن التكفير ما وجد إليه سبيلاً فإن استباحة دماء المصلين المقرين بالتوحيد خطأ، ✧ አል-ገዛልይ “አተፍሪቀቱ በይነል ኢማኒ ወዘንደቃህ” በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ይህን ማለታቸው ተቀምጧል፦«የተገባው የሆነ ነገር መውጫ መንገድ እስካገኘ ድረስ ከማ*ክ*ፈር መቆጠብ ነው።(በተውሒድ) በመፅናት ወደ ቂብላ ዞረው ሚሰግዱ ሰዎች ደምን ማፍሰስ ስህተት ነው”]። ይህ የገዛልይ ንግግር እውቀት አለኝ በማለት ለሹመት እራሱን ላጨ ቀርቶ በዚህ ሰው ዙርያ በጅህልና እያጨበጨበ ለሚገኘው በራሱ በቂ ትንተናን እርሳቸው አኑረው አልፈዋል።ኣቡ ሐሚድ ረሒመሁሏህ የማክፈርን ፍርድ ከመስጠት የከለከሉት በተውሒድ የመጣን ሰው በመሆኑ ላይ ግልፅ ነው።ተውሒድ ደግሞ ያለ ተንዚህ አይሆንም።ምክነያቱም ተሽቢህ ያለበት ሰው አሏህን ከፍጡሩ በሲፋ የለየ አልሆነም።ይህ ደግሞ ከተውሒድ ምሰሶዎች የሚመደብ ነውና ሙሸቢህ ተውሒድ ስለሌለው እዚህ ውስጥ እርሱን ማስገባት በራሱ ትልቅ ስህተት እንዲሁ የተውሒድን ፍቺ ካለመረዳትም የመነጨም መሆኑ በግልፅ ሊታወቅ ይገባል።ገዛልይ ሙጀሲምን እንደሚያከፍሩ ከመታወቁም ጋር ሙጀሲምን ላለማክፈር ይህን በማስረጃነት ማምጣት እጅጉን አስገራሚና አወዛጋቢም ነው።እንዲሁ የቂብላ ሰው በመሰኘቱ ብቻ እስልምና እንደማያሰጠው ኡማህ ተብሎ ሲባልም ገለፃው የአማኞች እንጂ የሰጋጆች ብቻ እንዳልሆነ ሲገልፁ በ"ኣል ሙስተስፋ" ላይ እንዲህ ይላሉ፦ قال الغزالي في المستصفى ”أما إذا كفر ببدعته، فعند ذلك لا يعتبر خلافه، وإن كان يصلي إلى القبلة ويعتقد نفسه مسلماً.لأن الأمة ليست عبارة عن المصلين إلى القبلة، بل عن المؤمنين، وهو كافر، وإن كان لا يدري أنه كافر“ [«በቢድዓው የከፈረ እንደሆነ በዛ ግዜ ልዩነቱ ቦታ አይሰጠውም።ወደ ቂብላ ዞሮ በመስገድ እራሱን ሙስሊም አድርጎ ቢያስብም፤ ምክነያቱም ኡማህ ሲባል ወደ ቂብላ ዞረው የሚሰግዱ ሰዎች ገለፃ ሳትሆን ይልቅንስ የትክክለኛ አማኞች ናት።ይህ ደግሞ ካ*ፊር ነው።መክፈሩን ባያውቅም»]። ሲሉ አቋማቸውን ለመረረው ይምረረው በሚመስል መልኩ ያስቀምጣሉ።ይህ ነው እንግዲህ የነዛህ ታላላቆቹ መንገድ።የከፈረን ከፍረሀል።ሙስሊምን ሙስሊም ነህ እንጂ እስልምናን ከ ኩፍር ሚደባልቁ አልነበሩም።በአቋማቸው ፅኑም ነበሩ።እኔ ሳይሆን አሏህና ረሱሉ ካሉ ነበር የሚሉት።አሏህ የተሻለን መረዳት እንዲሁ መልካም መጨረሻን ይግጠመን።