WeMind Ethiopia
Відкрити в Telegram
1 193
Підписники
Немає даних24 години
-17 днів
-1030 днів
Архів дописів
1 193
የስኪዞፍሬኒያ ታካሚ ቤተሰብ ነዎት
ስኪዞፍሬኒያ ብዙ አይነት መገለጫ ያሉት ታካሚምና ቤተሰብን ሳይሆን አንዳንዴ ህክምናንም የሚፈትን ህመም ነው፡፡ የቤተሰብ፣ ታካሚ እና የጤና ባለሙያ ጋር ተባብሮ መስራት ለህክምናው ውጤታማነት ወሳኝ ነው፡፡ ነገር ግን በህመሙ ምልክቶችም ሆነ በሌላ ምክንያት በታካሚ እና በቤተሰብ መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር ያልተለመደ አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ የህክምናውን ቀጣይነት ጥያቄ ውስጥ ይከተዋል፡፡ የስኪዞፍኒያ ታካሚ የሆነ ቤተሰብ ካለዎት የሚከተሉት የተሻለ ተግባቦት (communication) ሊፈጥሩልዎ ይችላሉ
▪️የታካሚውን ስሜት ጠይቀው ለመረዳት ይሞክሩ፤ የማያስማማዎት ነገሮች ሊኖሩ ቢችሉም የሚያስማማዎ ነገሮች ላይ መተባበር ወዳጅነትን ያጠብቃል
▪️የቁም ቅዠት (hallucination) እና የተሳሳቱ ጽኑ እምነቶችን (delusion) በክርክር ለማሳመን አይሞክሩ፤ ጭንቀት ወይም ግጭት ከመፍጠር ውጭ ፋይዳ የለውም፡፡
▪️ስሜት የሚጎዱ እና ልክ ያልሆኑ አጠራሮችን፣ ቃላቶች፣ ግሳጼዎችን፣ የሰውነት እንቅስቃሴዎችን አይጠቀሙ
▪️ታማሚው ጠጣር እና ውስብስብ አ/ነጋገሮችን ለመረዳት ሊቸግረው ይችላል፡፡ በዚህም ትኩረት አድርጎ ንግግሩንም ላይከታተል ይችላል፡፡ ስለዚህ ንግግርዎን ግልጽና ቀላል ያድርጉት፡፡
▪️አበራታች ንግግሮችን ያብዙ ግሳጼዎችን ይቀንሱ፡፡ ህመሙ ተነሳሽት የመቀነስና ምንም ነገር ማድረግ እንደማይችል አድርጎ ሊሰማው ይችላል፡፡ ታማሚው ውስነነቱ ላይ ሊያተኩር ይችላል፡፡ ስለዚህ ባሳያቸው ጥሩ ነገሮች እያበረታቱ የበለጠ እንዲሰራ ይገፋፉት፡፡ በሚያጠፋው ጥፋት ሁሉ እግር በእግር እየተከታተሉ ከመገሰጽ ይቆጠቡ
▪️ታማሚው የሰዎችን ስሜት ማንበብ ሊቸግረው ይችላል፤ ስሜትዎትን በግልጽ ያስረዱ
▪️ያናደድዎን ነገሮች ገንቢ በሆነ መንገድ ይናገሩ፡፡ ንግግርዎ የሚያፈርስ ሳይሆን የሚርም ይሁን
▪️ አንዳንዴ ብዙ ቢጥሩም ላይሳከልዎና ውጥረት ውስጥ ሊከተዎ ይችላል፡፡ ያኔ ትንሽ እርፍት መውሰድ የታካሚንም የእርስዎን ውጥረት ሊያረግብ ይችላል፡፡
ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ)
t.me/gashaw_aweke
1 193
ከዲያሪዬ ገጾች ጥቂቶቹ
I think I got psychopathology in my notes
ክፍል 2
01/01/2011
ወደ አባባ ሻራ ስሔድ አባባ ውስጥ የሉም፡፡ ተመልሼ ወጥቼ የሃይላንዱን ኮካ፣ ሻይ ቅጠልና ሜንት ከረሜላ ገዝቼ ተመለስኩ፡፡ ግቢው የአባባ ሸራ እና ሁለት ክፍል ያላት ቤት አለው፡፡ ከጎረቤት የሚመጣው ትቦ ደም ተደፍቶበት ሽታው አያድርስ ነው፡፡አሁንም አባባ አልመጡም፡፡ ተቀምጬ እያነበብኩ ልጠብቃቸው ወሰንኩ፡፡ አባባ… ለረጅም ሰዓት ብጠብቃቸውም እስካሁን አልመጡም፡፡
አንድ ጊዜ የግቢው በር በነፋስ በሀይል ሲሰዘጋ በጣም ደነገጥሁ፡፡ ጪኸቱ በጣም ያስደነግጥ ነበር፡፡ ድንጋጤየን ያባባሰው ጥንቁልናና መተት ያደርጉብኛል ስላሉኝ ነበር አባባ፡፡ አከባቢየን ሳስተውል ከቤቱ በአንዱ ክፍል በር አጠገብ ለረጅም ጊዜ የተጋገረ ደም የሚመስል ነገር (ስፋቱ 30 በ40 ሳ.ሜ መሰለኝ በግምት) አየሁና ቅፍፍ አለኝ፡፡ ረጋ ብዬ ሳስበው ግን ቀይ አልጌ እንደሆነ ተረዳሁ፡፡
የቤቱ በር ሰላልተቆለፈ ክፈተው ክፈተው የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ከፈትኩት፡፡ የሽንቱ ሽታ ወደውጭ ይገፈትራል፡፡ ግን እንደምንም ተቋቁሜ ውስጡን ማስተዋል ጀመርከኩ፡፡ አንድ ለአንድ ሰው የሚሆን አልጋ በጥቁር ብርድ ልብስ ተነጥፎ፣ አነስተኛ መደርደሪያና ሌሎች ብዙም ያለሆኑ እቃዎች አሉ፡፡ ወለሉ በሻማ ሰም ቀልጦ ብዙ የክብሪት እንጨቶች ተዘርግፈው ይታያሉ፡፡ ወለሉ ግን የስሚነቶ ነው፡፡
በጀመሪያ የአባባ ቤት መስሎኝ ነበር፡፡ በኋላ አባባ እንደነገሩኝ ግን ግቢው የእሳቸው ቢሆንም የሚኖርበት ሌላ ሰው ነው፡፡ ወደ ንባቤ ተመለስኩ፡፡ ለካ የግቢውን በር መልሼ ከፍቼው ኑሮ አሁንም ነፈሱ በሀይል ሲዘጋው መልሼ ደነገጥኩ፡፡ ግን ምንም አይነት መረበሽ አልተፈጠረብኝም፡፡ ‹‹ሌላ ሰውን›› ልጨርሰው 5 ገጾች አከባቢ ሲቀረኝ አባባ ኃ/* መጡ፡፡ መጽሑፍን እንደያዝኩ ወደ በሩ አከባቢ ሔጄ ተቀበልኳቸው፡፡
የግራዋ እንጨቶች፣ የማትለያቸውን መዳበሪያቸውን፣ እና በጥቁር ፌስታል የሆነ ነገር ይዘዋል፡፡ በነገራችን ላይ ግቢው ሰፊ የሚባል አይነት ነው፡፡ የሞቀ ሰላምታ አቅርበውልኝ ወደ ሸራቸው ሔዱ፡ እኔም ቦርሳዬን ይዤ ተከተልኳቸው፡፡
አሁን ሳያት ቁመቷ 1 ሜትር፣ ረዝመቷ 1.50 ሜ ወርዷ 50 ሳ.ሜ የሆነች፤ ከስር አሮጌ ቆርቆሮ ያላት፤ ከላይ ቆርቆሮው እንዳይበርደው ሸራ የተደረበላት፤ አራት እግር ያላት መካከለኛ ጠረጴዛና ናት አባባ የሚኖሩባት ሸራ (ቤት)፡፡ ውስጧ በጭስ ጠቁሯል፡፡ መሬቷ በሚቃጣጠለው እሳት ጠቁሯል፡፡ ከላይ በቻ ናት ሰማያዊ፡፡ የሚደገፉበት እንጨጥ ሁላ አብረቅራቂ ጥቁር ቀለም የተቀባ ነው የሚመስለው፡፡ አሁን ለምን ጥቁር እንደሆኑ ገባኝ፡፡ ለካ በጣም ሰልሚበርዳቸደው ከሰል አቅፈው እየተኙ ኑሯል፡፡ እኔም እስከነቦርሳዬ ጠረጴዛዋ ውስጥ ወደ ጥግ ያለች ለመጥቆር የጀማመራት ብሎኬት ላይ ከጎናቸው ተቀመጥኩ፡፡
ትናንት እኮ የምሔድበት አልነበረም እዚህ ተሳቅቄ ነው እንጅ እዚህ እንደምታየው የሚመች ቦታ አይለም ሲሉኝ አሳዘኑኝ፡፡ ያመጣሁላቸውን ነገሮች ስሰጣቸው ትንሽ ሰቀቅ ያሉ መሰለኝ፡፡ ልብሱን ስሰጣቸው ልብስማ ነበረኝ ስለብሰው ያመኛል እንጅ አሉኝና መዳበሪያቸውን ፈተው ልብሱን እያወጡ አሳዩኝ፡፡ ቆሽሸዋል እንጅ ደህና ደህና ልብሶች ናቸው፡፡
እያወራን ቆይተን እንጨቱን አስተካክለው በጫማ እሳት ሊያቀጣጥሉ ሲሞክሩ አምቢ አላቸው፡፡ በኋላ ቆይተው በፌስታል ሊያቀጣጥሉት ሲሉ እኔ ተቀብዬ በእንጨት ብቻ አቀጣጠልኩት፡፡ የበግ ፍ* ሲሰበስቡ ኖሯል የዋሉት፡፡ ወደ 6 የሚጠጉ ፍ*-ኦችን አውጥተው እሳቱ ላይ አደረጓቸው፡፡ “የተቆለፈበት ቁልፍ” ላይ የበጉን ** ከወንዶች ልጆች ቀምታ የበላችውን ልጅ አስታውሼ ፈገግ አልኩኝ፡፡
ስልኬን አውጥቼ 50 ሎሚ የሚለውን ፊልም ከፈትኩላቸው፡፡ መጀመሪያ እንደማንገራገር አሉና በኋላ ግን ተመቻቸው መሰል በእጃቸው ስልኩን ይዘው ማየት ጀመሩ፡፡ በየመሐሉ ከእኔ ጋር ስለፊልሙ ታሪክ እየተወያዩ ጠብሼ ስጨረስ እሳቱን አጥፍቼ መጽሐፌን አውጥቼ እስኪጨርሱ ድረስ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ቅመው የተጣሉት የጫት እንጨጥ ሰብስበው መጥተው ስለነበር እንደማፈር እያሉ አንድ 2ዬ ቀንጠሥ ቀንጠስ አርገው ጎረሱለት፡፡ እንዳላሳቅቃቸው ብዬ ትኩረቴን ሌላ ነገር ላይ ያረኩ መሰልኩ፡፡ ፊልሙ አልቆ ፎቶ ተቃቅፈን ተነስተን እኔም የምሔድበት አለኝ ብለው አብረን እስከጸበሉ ሂደን፡፡ እኔ ወደ ቤቴ፤ እሳቸውም ወደ መከኒሳ ሄዱ፡፡ እቤት ቤቱን ቆላልፈው ሆስፒታል ሰው ሊጠይቁ ሔደው ስለነበር መግባት አልቻልኩም፡፡ ቁልፍ አልያዝኩም፡፡ በዛው ላይ ርቦኛል፡፡ እስኪመጡ መጠበቅ ነበረብኝ፡፡
***
ተፈጸመ
***
ከዛን ቀን በኋላ “አትምጣ፤ ከኔጋ መታየትህ ጥሩ አይደለም ማለት ጀምረው ነበር፡፡ ከግቢ ለእረፍት ስመለስ በተለመደ መንገዳችን ላይ አገኘኋቸው፡፡ ነገር ግን ሸሹኝ፡፡ ስከተላቸው ሸሹኝ፡፡ በሌላ ቀን እሞክራለሁ ብዬ ተመለስኩ፡፡ ከዛን ቀን በኋላ አግኝቻቸው አላውቅም፡፡ አሁን ባገኛቸው ብዙ የምጠይቃቸው ነበረኝ።
t.me/gashaw_aweke
ጋሻው አወቀ
1 193
ከዲያሪዬ ገጾችች ጥቂቶቹ
May be I got psychopathology in my notes
ክፍል 1
አንድ ሰሞን በሆነ ምክንያት “አና ፍራንክ”ን ካልሆንኩ ብዬ ያዙኝ ልቀቁኝ ብዬ ነበር (ይዞ የሚለቀኝ አጣሁ እንጅ!) በዛም ምክንያት ትንሽ ማስታወሻዎች ጽፌ ነበር፡፡ አሁን እነዚህን ሳነባቸው ገረመኝ…
1/13/2010
ያ ጥቁር በጥቁር ለብሶ ጆንያ ነገር በላዩ ላይ ጣል አድርጎ የሚሔደውን ሰው አብሬው ቁጭ ብዬ ለረጅም ጊዜ አወራን፡፡ በ3 ስም እንደሚጠራ ነገረብ፥ ወ--፣ ኃ/*** እና ደ-- ፡፡ ኳስ ጎበዝ እንደነበርና ለትምህረት ጭንቅላቱ ክፍት እንደሆነ ነግሮኛል፡፡ 12ኛ ክፍል ጨርሷል፡፡ በየንግግሩ የእንግሊዘኛ ቃላት ጣል ያደርጋል፡፡ አንተ ብዬ በኋላ እድሜውን ሲነግረኝ ግን ተሸማቀቅሁ -አንቱ ባለማለቴ፡፡ አንተ ልበልህ ወይስ አንቱ ስለው በተመቸህ አለኝ፡፡ በአንተ ሰልጀመረኩ አንተን አጸናሁት፡፡ በ1954ዓ.ም አከባቢ ነው የተወለደው ስለዚህ አሁን ወደ 56 አከባቢ ነው ማለት ነው፡፡ ት/ት በ1965 ዓ.ም ነው የጀመረው፡፡ ኳስ ጎበዝ እንደነበረና አዲስ ጎማ ጋር እንደገባ (የኳስ ክለብ መሰለኝ) ነግሮኛል፡፡ ሶስት መንግስታትን አሳልፏል፡፡ የእኔን እድሜ 3 እጥፍ አከባቢ ኑሯል፡፡
ብዙ ምስጢሮችን የያዘና ተገሎ የኖረ ይመስለኛል፡፡ … ለምን ይሆን ራሱን እንደዚያ ያጠቆረው? ጥላሸት ተቀብቶ ይሆን ወይስ ከሰል? እንዴትስ አለቀቀም? ምን አልባት የጎማ አመድ ይሆን? ለመጀመሪያ ጊዜ ያዋራሁት ቀን ያበጠው ይፈንዳ ሰላም እለዋለሁ ብዬ ሰላም ስለው እንደማንኛው ሰው ሰላም አለኝ፡፡ ዛሬም የተቀመጠበት ቦታ ሄጄ አስፈቅጄ ተቀመጥኩና በዙ አወራን፡፡ ከዚያ ሰለቸሁ መሰል ለዛሬ እዚህ ላይ ይብቃን በሚል መንፈስ ሊነሳ ተዘጋጀ፡፡ እንዳጋጣሚ የምንሔድበት መንገድ ተመሳሳይ ነበርና በግምት 300 ሜትር አብረን እያወራን ሄድን፡፡ …
05/13/2010
ስለኬን ዘግቼ ሀይል መሙያው ላይ ሰክቼ መጻሕፌን ይዤ ጥቁር በጥቁር ለብሼ ወጣሁ፡፡ ለአለባበሴ ግድ አልነበረኝም፡፡ ግን ደን ማግኘት ስለፈለኩ ብዙም ስሜቱን እንዳልረብሸው ጥቁር መልበሴን አልጠላሁትም፡፡ ከጥቂት ማጠያየቆች በሀዋላ ደ ያለበትን አወኩ፡፡ አንዲት ባለሱቅ ስለእርሱ ስጠይቃት ‹‹እሳቸው›› ብላ ስታወራ ሀፍረት ተሰማኝና እኔም አንቱ ማለት አለብኝ ብዬ ካሁን በፊትም አንተ ስላልኳቸው ይቅርታ ለማለት ወሰንኩ፡፡ ስማቸውንም አባቴ ኃ/* የሚለው ተስማምቶኛል፡፡ ባለሱቆቹ በጠቆሙኝ መሰረት ሁለት ግቢዎችን ብቻ ነበር ያንኳኳሁት፡፡ … አንድ በሰንሰል ቅጠል በታጠረ ግቢ ውስጥ፤ ገርበብ ብሎ በተከፈተ የቆርቆሮ በር ኋላ፤ በግምት ሜትር በሜትር በምታክል ሸራ ተወጥራ፤ ከሷ ስር ብዙ ሃይላንዶችና ጎማዎች የሚቃጠሉበት ቦታ ስር ድሮታቸውን ይዘው ጥቅልል ብለዋል፡፡
በመጀመሪያ የድሪቶ ጥቅልል ነበር የመሰለኝ... ፈራ ተባ እያልኩ ትንሽ ቀረብ ብዬ ለማየት ሞከርኩ፡፡ ሲንቀሳቀሱ እሳቸው መሆናቸውን ተረዳሁ፡፡ ቤቴን እንድታይ አልፈቅድልህም ስላሉኝ ሲያዩኝ እንዳይቆጡ ብዬ በድመት እርምጃ ግቢወን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ ባለሱቆቹ ኮካ እና ሜንት ከረሜላ ይወዳሉ ስሉኝ እሱን ይዤ ለመምጣት አሰብኩ፡፡
ችግሩ ዘወር ብዬ አለያኋቸውም እንጅ ኮሽታዬ ሳይቀሰቅሳቸው አልቀረም፡፡ …ለምን ፊታቸውም እጃቸውም ሰውነነታቸውም እንደዚያ እንደጠቆረ የተገለጠልኝ መሰለኝ፡፡ ብርዱንና እና ጨለማውን ለመቀቋቋም በሚያነዱት ጎማ እና ሃይላንድ አጠገብ ስለሚተኙ እንደሆነ ገመትኩ፡፡
ወደ ሱቅ እያመራሁ እያለ እሳቸው ተነስተው ወደ ጸበሉ አከባቢ ሲሄዱ አየኋቸውና እየሮጥኩ ሂጄ ስማቸውን 2ዬ ስጣራ ዞር አሉና አዩኝ፡፡ እጃቸውን ዘረጉልኝ፡፡ ከዛ እንደማቀፍ አድርገውኝ ወደ ጸበሉ መታጠፊያ ድረስ እየሄድን እያወራልን፡፡ ልክ ጸበሉ አከባቢ ባለው መገንጠያ ጋር ስንደርስ ምን ሊለኝ እንደሆነ አላውቅም የቀጠረኝ ሰው አለኝ እናም ወደዚያ እየሄድኩ ነው ብለው የስንብት ምልክት ሰጡኝ፡፡ … አብርሬ መሔድ እችላለሑ? ስል አይ ሰው እኮ አታወቅም ሰው ይዘህ ስትመጣበት ሊከፋው ይችላል አይሆንም አሉኝ፡፡ …ተስማማሁ፡፡ በነጋታውምም አዲስ ዓመትን አብርን እንድናክብር ከቤት (ቤት አልኩ እንዴ ተሳስቼ ነው) ሳይወጡ እንዲጠብቁኝ ተነጋግረን ተለያየን፡፡
t.me/gashaw_aweke
ጋሻው አወቀ
1 193
‘Vital signs’ in mental health assessment
As it is known there is no, at least in clinical practice, laboratorial investigations and imagings to confirm mental heath problem; but they are used to rule out other medical conditions, to take a baseline, to make good decision on drug choice, and to confirm comorbid physical illness.
The psychiatric evaluation and diagnosis is done based on the following cornerstones, after making comparison against a standard diagnosing criteria (DSM 5TR). Here, what we should take into account is that it is not the mere comparison against the DSM 5TR Criteria that makes the real diagnosis; the clinician’s critical evaluation of the case against different perspective is mandatory.
1) Functional impairment or clinical distress
For most psychiatric diagnoses, it not just the constellation of symptoms that makes it a disorder; the disorder highly interferes with basic day to day activities, social, school, work or other significant arenas of life. For instance, globally, an estimated 12 billion working days are lost every year to depression and anxiety at a cost of US$ 1 trillion per year in lost productivity [WHO.]
Or else, it has clinical distress… imagine how to feel your body, voice and thoughts are not yours in panic do, DPDR or agoraphobia…
2) Deviation from religious and cultural background
Some behaviors may better explained by cultural and religious backgrounds. there are also sociocultural phenomena which are called culture bound syndromes that are not included in psychiatric diagnosis. Zar is an example. so culture and religion is taken in consideration.
3) Premorbid history
The client’s history prior to the development of the sign and symptoms are taken into consideration to see what anomalous behaviors are there.
4) Substance, medication, other medical conditions and other mental disorder
To make diagnosis of specific mental disorder, the symptoms and signs must not be better explained by other conditions mentioned above.
Gashaw Aweke (Psychiatry Professional)
t.me/gashaw_aweke
1 193
ሜንታል ሄልዝ አዲስ ቀጣዩን ወርሃዊውን ዝግጅቱን ይዞላችሁ መጣ፡፡ በሚያዚያ 28/2015 ቅዳሜ ቀን ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በአዶር አዲስ ሆቴል “የአዕምሮ ህመም መንስኤው ይታወቃል? በዘር ወይንስ በእርግማን ነው ሚከሰተው?” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ እንዲናገሩ ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብን ጋብዟል፡፡ መግቢያ ክፍያ:- ነፃ!!! ለመታደም በ0933616212 ሙሉ ስሞትን ይላኩ ወይንም በዚህ መስፈንጠሪያ ይመዝገቡ፡፡ https://docs.google.com/forms/d/1JcXN5wU_CItM93fUVZgpFNXUq7xK0ZjBWa1ddxwfEww/edit?usp=drivesdk
Mental Health Addis has brought to you the next mental health talk free of entrance fee. It will be held on Saturday May 6, 2023 at 4:00PM in the afternoon at Adore Addis Hotel. Dr Yonas Bahiretebeb will be speaking on the title of “What Causes Mental Illness? Genetics, Generational Curses or Do we even know? RSVP by texting your full name on this number 0933616212 or by using the link provided here https://docs.google.com/forms/d/1JcXN5wU_CItM93fUVZgpFNXUq7xK0ZjBWa1ddxwfEww/edit?usp=drivesdk
1 193
በእለተ ጁመአ ወደ ስራ ክፍሌ ስገባ አንዲት ታካሚ በአንድ የስራ አጋሬ የህክምና እርዳታ እየተሰጣት እያለ ወደ ክፍሉ ዘለቅኩ፡፡
ምንም እንኳን በአዕምሮ ህክምና ህግ አንዱና ዋንኛው አስፈላጊ የህክምና አካል የታካሚ ታሪክ ግላዊነት (privacy) ቢሆንም ያለችን ክፍል አንድ በመሆነኗ ምክንያት እኔ እና ያሉት ሁለት የአዕምሮ ባለሟሎች ያሉንን ወንበሮች እና የታካሚዎቻችን ታሪክ በውዴታ ግዴታ አንተ ትብስ አንቺ ትብሽ እያልን እየተጋራን እንሰራለን፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በእለቱ ታከሚዋ እና የህክምና ባለመዋሉ እሚያደርጉትን ንግግር ለመመልት ከወደ ክፍሉ ዳር ጋር ያለ አግዳሚ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ታካሚዋ ከፊተዋ ግራ ክፍል በቀር ያለውን አካሉዋን ተለቅ ባለ ፎጣ ሸፋፍና በለሆሳስ ድምጽ ለባለሞያው ታስረዳለች፡፡ ሁኔታው ቀልቤን ስለገዛው ታሪኳዋን መዳመጥ ቀጠልኩ፡፡
የአራት ልጆች እናት የሆነችው እህታችን ምንም እኳን በተለያ ህክምና ስፍራ ብታደርግም ባለፉት ሁለት አመት በመዳኒት አቅርቦት እጥረት ምክንያት ህክምና ማቋረጧን በዚያን ምክንያት ህመሙ በድጋሚ አገርሽቶባት ከባድ አደጋ እንደደረሰባት አወጋችው፡፡
በደረሰባት ጉዳት ምክንያት ከማህበረሰብ እንደተገለለች ፤ ሰዎች ፊት መቅረብን እንማትችል እናም ለቤተሰቧ ችግር የሆነች እንደተሰመት እናም ልሎች ብዙ ነገሮችን ……………. በአሁኑ ሰአት መመገብ ስለተቸገረች እናም በዚህ ምክንያት ወደ ሆስፒታላችን መጥታ ወደ አዕምሮ ህክምና ክፍል እንደተላከች አስረዳችው፡፡ እናም እያለ ይቀጥላል…
ባልታከመ የአዕምሮ ህመም ምክንያት ስንቶቹ እንደ እህታችን አይነት ዜጎች ለተለያየ ህመም ተጋልጠዋል? ስንቶችስ ይሆኑ ህይወታቸው ያለፈው?
የአዕምሮ ህሙማን እንደ ኩላለት ታማሚ እሚጮህላቸው ሚዲያ የላቸው ፤ እንደ ኮሮና የማህበረሰቡን ቀልብ አልገዙ በዚህም ምክንያት ድምጽ አልባ ህሙማን ሆነዋል፡፡ ስለዘህ ሁላችንም በትንሹ አንድ እምናቀው የአዕምሮ ታማሚ ይኖራል ብዬ አስባለው፡፡ ስለዚህ ለአዕምሮ ህሙማን ደምጽ እንሁን፡፡
ይህን መልእክት ሼር (share) በማድረግ ለአዕምሮ ህሙማን ድምፅ እንሁን፡፡
ያለ አዕምሮ ጤና ፤ጤና የለም
ዶ/ር ቶፊቅ አብደላ Psychiatrist
via @HakimEthio
1 193
💉አዲስ ስለገባው መድሀኒት- Paliperidone |NVEGA 💉
🧠 ስኪዞፍሬኒያ ቀስ በቀስ የአንጎልን መጠን እየቀነሰ የሚመጣ ስር የሰደደ እና ውስብስብ ህመም ነው
🧠 በታካሚው፣ ለመኖር አስፈላጊ በሆኑ የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴዎች፣ ቤተሰብ፣ ስራ ክህሎት፣ ጤና፣ ማህበራዊ ክህሎት ላይ ከፍተኛ ተጽኖ ያመጣል
▪️ እንደታማሚው ሁኔታ ቢለያይም ሁለኛ ትውልድ መድሀኒቶች (SGA) ለህመሙ ተመራጭ ናቸው- የተሻለ ውጤት እና በአንጻሩ አነስተኛ የጎንዮሽ ጉዳት ስላላቸው
▪️ እነዚህ መድሀኒቶች (ኢንቬጋን ጨምሮ)፣ በተለይ ህመሙ እንደጀመረ ሲሰጡ፣ የአንጎል መጠን የበለጠ እንዳይቀንስ በመከላከል የህመሙን ምልክቶችን እና የስራ አቅምን ያሻሽላሉ
▪️ ህመሙ ሳይታከም በቆየ ቁጥር ለህክምና አስቸጋሪ እየሆነ ይመጣል
▪️ህመሙ ባገረሸ ቁጥር እየተባባሰ እና ለህክምና እያስቸገረ የሚመጣ ሲሆን በመርፌ የሚሰጡ መድሀኒቶች ግርሻን ለመከላከል የተሻለ አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይችላሉ
▪️በተለያየ ምክንያቶች በአፍ የሚወሰዱ መድሀኒቶችን በአግባቡ የማይወስዱ ታካሚዎች በመርፌ በየ2 ሳምነቱ ወይም በየወሩ እንዲሰጣቸው ይደረጋሉ
▪️በየወሩ የሚሰጡት መድሀኒቶች ከመጀመሪያ ትውልዶች የተሰሩ ስለሆኑ የጎንዮሽ ጎዳታቸው ከፍ ሊል ይችላል፡፡
💉 Paliperidone (INVEGA)
-› በቀናት ውስጥ ለውጥ ያሳያል
--›ምልክቶቸን በመቆጣጠር እና ግርሻን በመከላከል የተሻለ ውጤት እንዲሁም አነስተኛ የጎንዮሽ ጉዳቶች ነው ያሉት
-› ታካሚው በተሻለ የስራ አቅም እንዲኖር ይረዳዋል
-› መድሀኒት እያቆራረጡ በመውሰድ ምክንያት የሚመጣውን ችግር ይቀንሳል
-› በወር፣ በ3ወር ወይም በ6ወር አንድ ጊዜ ብቻ ሊወሰድ ይችላል (እስካሁን ሀገራችን የገባው ባለ አንድ ወሩ ነው)
ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ)
t.me/gashaw_aweke
▪️ Reference
- Stahls essential psychopharmacology prescribers guide, 7th ed, Cambridge.
- Textbook of psychopharmacology, 5th ed, APA.
- Workshop for Invega held by Sitota Center for Mental Health Care and Jansen Neuroscience.
1 193
ህክምናን በአግባቡ አለመከታተል (Treatment non adherence)
▫️ ህክምናን በአግባቡ አለመከታተል በተለያዩ የህክምና ዘርፎች አስቸጋሪ ጉዳይ ቢሆንም በስነ አእምሮ ህክምና ላይ ጎላ ብሎ የሚስተዋል ችግር ነው
▫️ 25በመቶ ታካሚዎች ከሆስፒታል በመወጡ በ10 ቀናት፣ 50 በመቶዎቹ በ1 ዓመት ውስጥ እና 75በመቶዎቹ በ2 ዓመታት ውስጥ ህክምናውን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ ያቋርጣሉ፡፡
▫️ አይነቶቹ (በጥቂቱ)
- ክትትል ሙሉ ለሙሉ ማቋረጥ ወይም ክትትል ማድረግ ግን ሀኪም ያለውን አለማድረግ
- ከፍል የህክማና አማራጮችን (መድሀኒቶችን) ተቀብሎ ሌላውን ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆን
- ሙሉ ለሙሉ አለማቋረጥ፣ ደግሞም በታዘዘው መሰረት አለመውሰድ
- መጀመሪያ አከባቢ መቃዎም፣ በኋላ ግን በአግባቡ መውሰድ
- ለተወሰኑ ጊዜያት በአግባቡ ተከታትሎ ከቆዩ በኋላ ችላ እያሉ መምጣት
- ከታዘዘው በላይ መውሰድ
- መድሀኒቱን በትክክል እየወሰዱም ቢሆን ከተከለከሉ ነገሮች አለመቆጠብ
▫️ የሚያመጣው ችግር
ስር የሰደዱ ህመሞች (chronic illnesses) ከህክምና አላማዎቹ መካከል
-› ምልክቶቹን መቆጣጠር
-› ተመልሶ እንዳያገረሹ መከላከል
-› ታካሚውን ወደሚቻለው የስራ አቅም ከፍ ማድረግ… ናቸው
ህክምናን በአግባቡ አለመከታተል እንዚህ አላማዎች ግብ እንዳይመቱ ያደርጋል፤ ህመሙ ተመልሶ (ምን አልባት አደገኝነቱን ጨምሮ) እንዲመለስ ያደርገዋል፡፡
▫️ ምክንያት እና መፍትሔው… [ጥቂቶቹ]
📌 ምክንያት፡- አንዳንድ ህመሞች መታመማችንን እንኳን እንዳናውቀው ያደርጉናል፡፡ ስለዚህ ጤነኛ ነን ብለን ስለምናስብ ህክምና ልንቃወም እንችላለን
🔑 መፍትሔ
-› ይህ ችግር የተፈጠረበትን ምክንያት መለየትና ከተቻለ መፍትሔ መፈለግ
-› ተኝቶ መታከም
-› በመርፌ የሚሰጡ መድሀኒቶችን መውሰድ
📌ምክንያት፡- ተነሳሽነት ማጣት (የአንዳንድ ህመሞች ባህሪ)
🔑መፍትሔ
-› ተነሳሽነት የሚጨምሩ የስነ ልቦና እርዳታዎችን ማድረግ (ራስ አገዝ መጽፍት፣ ከቤተሰብ፣ ከባለሙያ)
📌ምክንያት፡- የጎንዮሽ ጉዳት
- ማንናውም መድሀኒት የጎንዮሽ ጉዳት ያለው ሳይሆን መድኒት ያስባለውም ልንቋቋመው በምንችለው የጎንዮሽ ጉዳት ልንቋቋመቸው የማንችለውን ህመም ማከሙ ነው
- አብዛኛዎቹ ታካሚዎች ስለ ህመሙ ባህሪ ይሁን ስለ መድሀኒቱ መረጃ የላቸውም፡፡ ስለዚህ ለውጥ ቢመለከቱ የጎንዮሽ ጉዳት ይሁን ወይስ ሌላ ጉዳይ መለየት አይችሉም፡፡ ምልክቶቹ እንዳይመለሱ በመፍራት ብቻ ዝምታን ሊመርጡ ይችላሉ፡፡ አብዛናዎቹ የጎንዮሽ ምልክቶች በጊዜ የሚስተካከሉ ቢሆንም ሁሉም የጎንዮሽ ጉዳት መፍትሔ ስላላቸው ከሀኪም ጋር በመማከር ካላስፈላጊ ጉዳት ራሳችንን መጠበቅ አለብን፡፡
- አንዳንድ ታካሚዎች የማህበረሰቡ አካል ስለሆኑ ልክ ያልሆነ አመለካከት እነርሱም ጋር ሊኖር ስለሚችል በጥቃቅን የጎንዮሽ ጉዳቶች ሊደናገጡ እና ከመጠን በላይ በመጨነቅ ህክምናውን ሀኪም ሳያማክሩ ሊያቆሙት ይችላሉ፡፡
🔑መፍትሔ
-› ስለ ህመሙ እና ስለመድሀኒቶቹ ሀኪምዎን ያማክሩ፣ ከታማኝ የመረጃ ምንጭ መረጃ ይውሰዱ
-› የተከሰቱ ምልክቶች ካሉ ጊዜውን እና መጠኑን መዝግበው ያስቀምጡ እና በክትትልዎ ጊዜ ከሀኪምዎ ጋር ይማከሩበት
📌ምክንያት፡- አንዳንዳንድ ህመሞች (ምሳሌ ካንሰር፣ HIV…) እንዳሉብን ሲነገረን መጀመሪያ አከባቢ ላንቀበላቸው እንችላለን ይህም ከህመሙ ከሚያደርሰው ተጽኖን ፍራቻ አእምሮ ራሱን የሚከላከልበት መንገድ ሊሆን ይችላል፡፡ ከከባድ የአእምሮ ህመሞች አንዱ እንዳለብን የማንቀበለው ከላይኛው ምክንያት በተጨማሪ ከማህበረሰቡ የሚያሰጠንን ስም ፍራቻም ጭምር ነው፡፡
🔑መፍትሔ
-› እንደማንኛውም ህመም የሚታከም መሆኑን ማስተማር
-› ታካሚው ራስን ማብቃት ላይ እንዲያተኩር ማስተማር
📌ምክንያት፡- መርሳት
🔑መፍትሔ
- አስታዋሽ ነገሮችን ማዘጋጀት፣ ለምሳሌ አላርም፣ ሪማይንደር፣ ከወዳጅ ማስታወሻ ቴክስት መቀበል…
- ከመደበኛ የእለት ከዕለት እንቅስቃሴዎች ጋር ማያያዝ፤ ለምሳሌ ጥርስ ከቦረሽን በኋላ፣ ራት ከበላን በኋላ፣ ልንተኛ ስንል….
ከዚህ በላይ ስለሚረዝም ሌሎቹን በሌላ ጊዜ ይጻፉ መሰል…!
ጋሻው አወቀ (የስነ አእምሮ ባለሙያ)
t.me/gashaw_aweke
1 193
ዘገምተኛ እንዳያደርገኝ እፈራለሁ!
“ዘገምተኛ እንዳያደርገኝ ስለምፈራ መድሀኒቱ ቢቀርብኝ” የሚሉ ጥያቄዎች ይጠየቃሉ፡፡
ሰዎች “ዘገምተኛ መሆን” የሚለውን አገላለጽ የሚጠቀሙት ለማስታወስ፣ መረጃን ለማውጠንጠን እና አዲስ ነገሮችን ለመማር መቸገር ወይም መዘግየት፣ እንዲሁም የሰውነት እና የስራ ቀልጥፍና መቀነስን ለመግለጽ ሊሆን ይችላል፡፡ ታካሚዎች እና ቤተሰቦች መድሀኒታቸውን በአግባቡ እንዳያስቀጥሉ ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ይህ “ዘገምተኛ የመሆን” ፍራቻ ነው፡፡
የማስታወስ አቅም መቀነስ ወይም በአእምሮ እና በአካል መንቀራፈፍ በሚከተሉት ምክንያቶች ሊሆን ይችላል
1. የህመም ምልክት
- ድባቴ (depression)፣ ሁለት ዋልታ ህመም (bipoar) እና መሰል ህመሞች የሰውነት መንቀራፈፍ፣ ደስታና ፍላጎት ማጣት፤ ትኩረት ለማድረግ መቸገር፣ ለማስታወስ መቸገር፣ ማቀድና ውሳኔ ለማሳለፍ መቸገር…. የመሳሰሉን ምልክቶች በተፈጥሮ አሏቸው፡፡ ድባቴ ከሌሎች ጽኑ አካላዊም ሆነ አእሞሯዊ ህመሞች ጋር አብሮ ሊመጣ ይችላል፡፡ ስለዚህ ችግሩ የመድሀኒቱ ሳይሆን ተዳብሎ የመጣው ህመም ነው፡፡
- አሉታ ምልክቶች (Negative symptoms)
አሉታ ምልክቶች በስኪዞፍሬኒያ እና መሰል ህመሞች የሚከሰቱ ደስታና ተነሳሽነት ማጣት፣ ስሜንን ለመረዳና ለመግለት መቸገር፣ ከሰው ጋር መቀላቀል የመሳሰሉትን ክህሎቶች የሚጎዱ ምልክቶች ሲሆኑ ለህክምናም አስቸጋሪ ናቸው፡፡
ከማህበራውና ስነ ልቦናዊ የህክምና እርዳታ ባለፈ ለነዚህ ምልክቶች እጅግ ውጤታማ የሆነ መድሀኒት ገበያ ላይ የለም፡፡ ለዚህ ነው ከመድሀኒት ህክምና በተጓዳኝ ስነ ልቦናዊና ማህበራው ህክምናዎችም አስፈላጊዎች ናቸው የምንለው፡፡ ነገር ግን በአብዛኛዎቹ የአእምሮ ህክምና ሆስፒታሎች እነዚህ የህክምና አመራጮች ያነሰ ትኩረት ስለተሰጣቸው “መምጣት በነበረበት ውጤት ልክ መራመድ አልቻልንም” ብዬ አምናለሁ፡፡
የሆነው ሆኖ፣ መድሀኒቱ ሌሎች ምልክቶችን አክሞ እነዚህ ላያተካክላቸው ይችላል፡፡ ስለዚህም ታካሚው ወይም ቤሰብ እነዚህን ምልክቶች የመድሀኒቱ የጎንዮሽ ጉዳት አድርጎ ሊወስዳቸው ይችላል [በእርግጥ እነዚህን ምልክቶች የሚያባብሱ መድሀኒቶችች ያሉ ሲሆን ከሀኪም ጋር ተነጋግሮ ወደማያባብሱ መድሀኒቶች መቀየር ይቻላል]
- የማስታወስ፣ መማር እና የመወሰን አቅም መዳከም (coginitice impairment)
ስኪዞፍሬኒያን የመሳሰሉ ህመሞች ከግንባራችን ስር ያለውን የአንጎል ክፍል ያጠቃሉ፡፡ ይህ ክፍል ደግሞ ስሜትን፣ ባህሪን፣ መማር፣ መወሰን፣ ማቀድ የመሳሰሉን ላቅ ያሉ ተግባራት ማከናወኛና መቆጣጠሪያ ነው፡፡ መድሀኒቶች ይህን ችግር ላይስተካክሉት ስለሚችሉ ታካሚ ወይም ቤተሰብ እነዚህን ምልክቶች በመድሀኒት የጎንዮሽ ጉዳት ሊያሳስታቸው ይችላሉ
2. ሱስ አምጪ ነገሮች (ለምሳሌ አልኮል፣ ካናቢስ…)
ሱስ አምጪ ነገሮች እና ሌሎች የአእምሮ ህመሞች እርስ በእርስ ይሳሳባሉ፡፡ በተለይ ጽኑ የአእምሮ ህመሞች ጋር የሱስ ህመም አብሮ ይመጣል፡፡ በዚህም ሱስ አምጪ ነገሮቹ የማስታወስና የማገናዘብን አቅም ይቀንሱታል፡፡ ሱስ የመድሀኒቱን አቅም መቀነሱ ብቻ ሳይሆን የመርሳት ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡
3. እድሜያቸው የገፋ ታካሚዎች (geriatry)
ማገናዘብ እና እውቀትን የሚቆጣጣጠረው አሴታይልኮሊን የሚባል ነርቭ አስተላላፊ ኬሚካል ነው፡፡ መድሀኒቶች ይህን ኬሚካል ሊቀንሱት ይችላሉ፡፡ ስለዚህ አንዳንድ #ለካንሰር የሚሰጡ መድሀኒቶች፣ አንዳንድ #ሰውነት_ሲቆጣ (anti-inflammatory agents ለምሳሌ ለአስምና ለአንጀት ቁስለት የሚሰጡ መድሀኒቶች) የሚሰጡ መድሀኒቶች፤ አንዳንድ #ለህመም_ማስታገሻ የሚሰጡ መድሀኒቶች፣ አንዳንድ #ኮሌስትሮልን ለመቀነስ የሚሰጡ መድሀኒቶች፣ አንዳንድ #ለአእምሮ ህክምና የሚሰጡ መድሀኒቶች፣ አንዳንድ #ለልብ ህመም የሚሰጡ መድሀኒቶች… በተለይ እድሜያቸው የገፋ ሰዎች ላይ ይህን ችግር ሊያመጡ ወይም ሊያባብሱ ይችላሉ፡፡ ተመሳሳይ ተጽኖ ቢኖቸውም ከአእምሮ ህክምና ውጭ የሚሰጡ መድሀኒቶችን “ያጀዝቡኛል” በሚል ምክንያት የተቃወመ ሰው መኖሩን እንጃ!
በተጨማሪም፣ ይህ የጎንዮሽ ጎዳት የሚስተዋለሁ በድሮዎቹ መድሀኒቶች ነው፡፡ ታካሚው ለሌሎች መድሀኒቶች ብቁ ካልሆነ ወይም በነዛ ለውጥ ካላመጣ እነዚህ መድሀኒቶች ሊታዘዙለት ይችላሉ፡፡ ሆኖም እድሜያቸው ባልገፋ ሰዎች ይህ ጉዳይ ብዙም አሳሳቢ አይደለም፡፡
4. ያለ አግባብ መውሰድ
አስቸኳይ ለውጥ ግዴታ በሚሆንበት ጊዜ በልዩ ማዘዣ ወረቀት በልዩ ትዕዛዝ የሚሰጡ መድሀኒቶች አሉ፡፡ እነዘሱን ያለአግብ ለረጅም ጊዜ መጠቀም የማስታወስ ችግር ሊያመጡ ይችላል፡፡
5. የመጫጫን ስሜት (Sedation)
አንዳንድ መድሀኒቶች መነቃቃት ይፈጥራሉ ሌሎች ደግሞ መጫጫን እና እንቅል እንቅልፍ የሚል ስሜት ሊፈጥሩ ይችላሉ፡፡ ይህ እንደ ጎንዮሽ ጉዳት ብቻ አይወሰድም -- እንቅልፍ ለሚያስቸግራቸው ሰዎች እንዲተኙ ያደርጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም ጊዜያዊ እና በሆስፒታል ቆይታ ውስጥ የሚከሰት ነው -- ሌሎች ምልክቶችን ለመቆጣጠር መጠኑ ስለሚጨመር፡፡ ሰውነቱ ሲላመደው እንዲሀም፣ ከሆስፒታል ሲወጣ መጠኑ ስለሚስተካከል ይህ ጉዳይ ሊያሳስበን አይገባም፡፡ ነገር ግን ካልተሻሻለ እና ከንቃታችን ከከለከለን ከሀኪም ጋር ተነጋግሮ ወደተሻለ መድሀኒት መቀየር ይቻልል፡፡
6. ከመጠን በላይ መብሰልሰል (over concern)፡ ሁላችን ጉዳት እንዳይደርስብን መጠንቀቃችን አይቀርም፡፡ ስለዚህም ስጋት መኖሩ ተገቢ ነው፡፡ ይሁን እንጅ በማህበረሰቡ ዘንድ በአእምሮ ህክምናዎች ላያ ያለው ግንዛቤ ብዙም አለመሆኑ ጥቃቅን ነገሮችን መሰረት በማድረግ ስጋት ውስጥ ልንገባ እንችላልን
በተፈጥሮ የሰው ልጅ ከእውቀቱ ውጭ የሆኑ ነገሮች ከቁጥጥሩ ውጭ ሆነው ስሚያስፈሩት ያንን ጭንቀት ማርገቢያ ስለክስተቶቹ የራሱን ትንታኔ መስጠት ይቀናዋል፡፡ ያ ትንታኔ እውነትን የተተንተራሰ ቢሆንም እንኳ አንዳንዴ ምክንያት አልባ ይሆናል [“ሰማይ ቅርብ ነበር፣ በቅሎ በእርግጫ ስትረግጠው ሰማዩ ራቀ ፈጣሪም ረገማትና መውለድ አቃታት” አይነት ትንተና] አብዛኛው በማህበረሰቡ የሚሰነዘረው አስተያየቶች በልምድ የታየ መነሻ ቢኖረውም ሙያዊ ያልሆኑ እና በግምት የሚሰነዘሩ በመሆናቸው የመሳሳት እድል አላቸው፡፡ በአእምሮ ህመም እና ህክምናው ላይ ያለው ልክ ያልሆነ ስዕልም አንደኛው ምክንያት ይሄ ሊሆን ይችላል፡፡ ሚድያውም (ሁሉንም ማለቴ አይደለም) ይህንኑ ችግር አጉልቶ ስለሚያንጸባርቀው “ልክ ያልሆነውን ስዕል” የማባባስ ላይ ሚና ተጫውቷል፡፡
እንደኛ ባሉ ከድህነት ጋር የሚኖሩ ሀገራት የአእምሮ ህመም ጉዳት የሚያደርሰው በሁለት “የሰይፍ ስለት” ነው፡፡ አንደኛ በቀጥተኛ የህመሞቹ ተጽኖ ሁለተኛው ዝቅተኛ ግንዛቤ በሚፈጥረው ችግር፡፡ ስለዚህ “ዘገምተኛ እንዳልሆን” የሚለውን ፍራቻ “ጭራቅ” ያሳከለው ህብረተሰቡ እየተቀባበለው የመጣው ልክ ያልሆነ አረዳድ ነው ብል የተሳሳትኩ አይመስለኝም
ይህንን ስጋት ለመቀነስ ትክክለኛው መፍትሄ ስለሁኔታው ከጤና በለሙያዉን ጠይቆ መረዳት ችግር ካለም ተነጋግሮ መወሰን ነው፡፡
ማጠቃለያ፡- ለአእምሮ ህክምና የሚሰጡ መድሀኒቶች “ዘገምተኛ” አያደርጉም፡፡
t.me/gashaw_aweke
1 193
የማግለል ይዘቶች
``````ህዝባዊ ማግለል (public stigma): ማህበረሰቡ ታማሚው ላይ የሚያሳየው ማግለል ሲሆን ለታካሚው ከሚሰጠው ያልተስተካከለ አመለካከት እስከ ግልጽ አድሎ (ለምሳሌ ስራ መከልከል) ሊደርስ ይችላል የታሰበ መገለል (Anticipated stigma): ታማሚው የጤናው ሁኔታ ከታወቀ መገለል እንደሚደርስበት ያስባል ከስያሜ መሸሽ (label avoidance)፡ የአእምሮ ታማሚ ነው ላለባል በመፍራት ይህንን ስያሜ ያሰጠኛል ከሚለው አከባቢዎችና አገልግሎቶች (ሀኪም ቤቶች፣ የማገገሚያ ቦታዎ፣ የስነ ልቦና አገልግሎት ቦታዎች…) ራሱን ያርቃል፡፡ ይህም የህክምና እርዳታ በጊዜ እንዳያገኝ፥ ህክምና ጀምሮ ከሆነም እንዲያቋርጠው ያደርገዋል፡፡ ራስን ማግለል (self-stigma)፡ በማህበረሰቡ የሚንጸባረቁት ትክክል ያልሆኑን አመለካከቶች ትክክል አድርጎ መቀበል ሲጀምር እና አስተሳሰቡን ወደራሱ ማስረጽ ሲጀምር ነው፡፡ አንድ በግ ተሸክሞ ይሄድ የነበረን ሰው ሌቦች መንገድ ላይ ያገኙት በጉን መውሰድ ፈለጉ፡፡ በመንገድ ተደብቆ አንዱ “ምን ሆነህ ነው ውሻ ተሸክመህ የምትሄደው” ይለዋል፡፡ ትንሽ ራቅ ብሎ ሌኛው ይህንኑ ይደግምለታል፡፡ ሰውየው መጠራጠር ይጀምራል፡፡ አሁንም ራቅ ብሎ ሌላኛው ይህነኑ ሲደግምለት በጉን ትቶት ሄደ እንደሚባለው፡፡ በተለይ በህመሙ ጊዜ እንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይሆናል፡፡ የዝምድና መገለል (associative stigma)፡ ይህ በታማሚው ቤተሰብ፣ ዘመዶች ወይም የጤና አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የሚደርሰው መገለል ነው፡፡ በዚህም ተጽኖ ምክንያት ቤተሰብ ወይም ጓደኞች ታማሚውን ህመሙን በምስጢር እንዲይዝ ወይም ህክምናውን እንዲያቋርጥ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ ልክ እንደ ታማሚ ቤተሰብና ጓደኛም ሀፍረትና የተዛቡ አመለካከቶችን ወደ ውስጣቸው ሊያሰርጹት ይችላሉ፡፡ ሌላው፣ ቤተሰቦች (እንርሱ ላይ ባይደርስባቸውም) በልጃው ላይ በሚደሰው መገለል ምክንያት መጎዳት፣ ቁጭት፣ ተስፋ መቁረጥ እና መጠቃት ሊሰማቸው ይችላል፡፡ ለምሳሌ እናት በልጇ ላይ የሚደርሰው “ብሽሽቅ” ልቧን ሊሰብራት ይችላል፡፡ t.me/gashaw_aweke
1 193
Repost from Mental wellness የአእምሮ ጤና
ማግለልና መድልኦን ፍርሀት- ማሪያ ኬሪ
=========================
ማሪያ ኬሪ የባይፖላር ህመም አለባት። ነገር ግን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ተናግራው አታውቅም። ምክነኒያቱን ስታስረዳ "መጀመሪያ እኔም ህመሙን አልተቀበልኩትም። 'በቃ ደህና ነኝ።፤ መድሀኒት አልወስድም!' ብዬ ተመልሶ ሲመጣ ነው ህመም እንደሆነ ራሱ የገባኝ። ከዛ ደግሞ የአእምሮ ህመም እንዳለብኝ ሰዎች ቢያውቁ ስራዬ ላይ ተፅእኖ ይኖረዋል ብዬ ነው የደበቅኩት።
ከዛ ስለህመሟ በግልፅ ስትናገር "መድልኦን ፈርቶ ተደብቆ ከአእምሮ ህመም ጋር ለብቻ መታገል ከባድ ነው። ሰዎች የአእምሮ ህመማቸውን ደብቀው ለብቻቸው መሰቃየት የለባቸውም። ከሰው ጋር ካልተጋፈጡት ከባድ ነው።" ብላለች።
የስራ ባልደረቦችህን እያቸው። ጎረቤቶችሽን ተመልከች። ዘመዶችህን አስብ። ማን የአእምሮ እንዳለበት መገመት አትችልም። ማግለልና መድልኦን በመፍራት ሁሉም ደብቆ ነው የሚይዘው። ግን ሁላችንም ቤት፣ ሁላችንም ሰፈር፣ ሁላችንም የስራ ቦታ አለ። ብንነጋገር የተሻለ ህክምና የተሻለ አገልግሎት እንዲኖር ማድረግ እንችላለን።
የአእምሮ ጤና መረጃ በዩቲዩበ ለማግኘት https://www.youtube.com/@dryonaslakew3386
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
