የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን🇪🇹
Відкрити в Telegram
828
Підписники
-224 години
-57 днів
-1630 день
Архів дописів
ነገ በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ተከትሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ነገ መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተጀምሮ እስከሚጠናቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስተባባሪነት የሚደረገረው ውድድር መነሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ ለገሀር፣ ሜክሲኮ አደባባይ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ብሔራዊ ቴአትር፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ ንግድ ባንክ፣ ጋንዲ ሆስፒታል ፣ ጊዮን ሆቴል በማድረግ መስቀል አደባባይ ፍጻሜውን ያገኛል።
ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ፦
. ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ )
. ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
. ከAU መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ )
. ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት )
. ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን
መታጠፊያ )
. ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ )
. ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ )
. ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ )
.ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ )
. ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ ላይ
. ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ )
. ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ )
. ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ )
. ከኤዩ መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ )
. ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
. ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
.ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
. ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
. ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
. ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
. ከአገር አስተዳደር መብራት ወደ ብሔራዊ ቲያትር (አገር አስተዳደር መብራት)
. ከንግድ ማተሚያ ወደ ኦርማ ጋራዥ (ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ)
ነገ ከንጋቱ 11:30 - ሰዓት ጀምሮ እስከ ፕሮግራሙ ፍፃሜ ድረስ መንገዱ የሚዘጋ ሲሆን በተጨማሪም በተገለፁት መስመሮች ላይ መኪና ለአጭርም ይሁን ለረጅም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ዋና ጠቅላይ መምሪያው አስታውቋል።
አዲስ አበባ እንደ አዲሲቷ ሲንጋፖር
የአንድን ከተማ ዕጣ ፈንታ ለመቀየር፣ ከፍ ያለ ራዕይ እና ከብረት የጠነከረ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ያላቸው የለውጥ መሪዎች ያስፈልጓታል።
የዚህ ዓይነተኛ ማሳያ የምትሆነው የእስያዋ የኢኮኖሚ ሞተር ሲንጋፖር ናት። ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት ሲንጋፖር ረግረጋማ፣ ድህነት ያንገላታት፣ የተበላሸ መሠረተ ልማት የነበራት እና ተስፋ የተቆረጠባት ደሴት ነበረች።
ነገር ግን በሪፎርሚስቱ መሪ ሊ ኳን ዩ ራዕይ፣ የከተማዋ አሮጌ ገጽታ ፈርሶ፣ ከሥረ መሠረቱ እንደ አዲስ ተገነባች። የሲንጋፖር የለውጥ ኃይል ከተማዋን ከጭቃ እና ከውድቀት አውጥቶ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የዓለም የቱሪዝም መዳረሻ፣ የፋይናንስ ማዕከል፣ እና የኢኮኖሚ ስበት ማዕከል አድርጓታል።
ይህ ታላቅ የከተማ ትንሣኤ፣ ቆራጥ መሪዎች ራዕያቸውን ወደ ተግባር ሲቀይሩ ከተማን ብቻ ሳይሆን የሀገርን ታሪክ እንዴት መቀየር እንደሚቻል ለዓለም ያሳየ ሕያው ምሥክር ሆኖ ተመዝግቧል።
ዛሬ ላይ፣ ይህንኑ የታሪክ እና የለውጥ ድግግሞሽ በእናት ሀገራችን እምብርት፣ አዲስ አበባ ላይ እያየነው ነው። "አዲስ አበባ የብልጽግና ተምሳሌት" በሚል የለውጥ መንፈስ፣ ከተማዋ የድሮ አሮጌ እና ጨርጫሳ ገጽታዋን አራግፋ፣ ፈርሳ እንደ አዲስ እየተሠራች ትገኛለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጀመሩት የለውጥ ንቅናቄ አዲስ አበባ ስሟን የሚመጥን "አዲስ አበባ" ለመሆን፣ ወደማይቀለበስ የለውጥ ማዕበል ውስጥ ገብታለች።
የሲንጋፖር መሪዎች አሮጌዋን ከተማ አፍርሰው ወደ ዓለም አቀፍ መዳረሻነት እንደቀየሯት ሁሉ፣ የኛዎቹም መሪዎች ጊዜያዊ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር፣ ሌት ተቀን በመረባረብ አዲስ አበባን አፍሪካዊት የቱሪዝም እና የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል፣ አፍሪካዊት የኢኮኖሚ ሞተር እና የውበት ስበት ማዕከል እያደረጓት ነው።
አሁን በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማቶች፣ የወንዝ ዳርቻ ድንቅ ዐሻራዎች፣ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክቶች፣ እና ሰፋፊ የመንገድ መሠረተ ልማቶች የዚህ ትውልድ ተሻጋሪ ራዕይ አካል ናቸው። ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ንጹሕ፣ አረንጓዴ እና ምቹ ከማድረግ አልፎ፣ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች፣ ግዙፍ ኢንቨስተሮች እና ዲፕሎማቶች የሚመኙት ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው።
እንደ ሲንጋፖር ሪፎርሚስቶች ሁሉ፣ አዲስ አበባን የሚመራው የለውጥ ኃይል ፈተናዎችን፣ ትችቶችን እና ጊዜያዊ ዘመቻዎችን በጽናት ተቋቁሞ፣ ከፍ ያለውን ትልቅ ምስል በማየት ከተማዋን ዳግም እያነጻት ይገኛል።
የከተማዋ ዕድገት በመንገድ ማስፋፋት ብቻ የተገደበ ሳይሆን፣ ማኅበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክር፣ እንዲሁም ከተማዋን ዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ እና የስብሰባ መዳረሻ እንድትሆን የሚያስችል ነው።
ይህ የሪፎርሚስት መሪዎች የጋራ ርብርብ የሚያሳየው አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ የትኛውም ታላቅ ከተማ በአጋጣሚ፣ በምኞት ወይም በዕድል የማይፈጠር መሆኑን።
ራዕይ ያላቸው መሪዎች አሮጌውን አፍርሰው አዲስ በመሥራት፣ ከተማዋን ከዘመኑ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር በማስተሳሰር የዓለም ምርጥ ከተማን በእውን መፍጠር እንደሚችሉ በተግባር እያሳዩን ነው።
አዲስ አበባ በእነዚህ የለውጥ ኃይሎች በፈጠሩላት አዲስ የልማት መዋቅር መሠረት፣ የአፍሪካ የፖለቲካ መዲናነት ክብሯን ከኢኮኖሚ እና ከቱሪዝም ልዕልና ጋር በማዋሐድ፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ከዓለም ምርጥ ዐሥር ከተሞች ተርታ የምትሰለፍ የዓለም አቀፍ ስበት ማዕከል መሆኗ የማይቀር ታሪካዊ ሐቅ ነው።
ማፍረስን እንደ ጥፋት ሳይሆን እንደ አዲስ ጅማሬ፣ እንደ ዳግም ውልደት የቆጠሩት የኢትዮጵያ ሪፎርሚስት መሪዎች፣ የነገዋን አዲስ አበባ የብርሃን ከተማ ለማድረግ የያዙት ቆራጥ አቋም በእርግጥም የሚያኮራ ነው።
በመሆኑም ከነአሮጌው አስተሳሰብ አዲስ ከተማ እንደማይገነባ ሁሉ፣ አሮጌውን አፍርሶ በተግባር በመሥራት፣ አዲስ አበባ የዓለም ምርጥ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ከተማ የመሆን ራዕይዋን አሳክታ፣ ለትውልድ የምትሻገር የአፍሪካዋ ሲንጋፖር ሆና እንደምትወጣ ምንም ጥርጥር የለውም።
በአዲስ አበባ አስተዳደር ስር የሚገኙ የመንግስት ሆስፒታሎች የትላንትናው ሁኔታቸው እየተቀየረ ነው።
ለዘመናት ተዘንግተው በእርጅና የተጎሳቆለውና የቆሸሸው ገፅታቸው በአዳዲስ ዘመናዊ ህንፃዎች እየተተካ፣ ኋላቀር የነበሩት የህክምና መሳሪያዎች ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን በሚጠቀሙ መሳሪያዎች እየተቀየሩ የታካሚውን ብቻ ሳይሆን የሀኪሞቻችንን ስራም እያቃለሉ ነው።
በተለይም አንዳንዶቹ ጠረናቸው ተቀይሯል፤ ወደ ቅጥር ጊቢያቸው ሲገባ ንፁህ የፈውስ ስሜት ይፈጥራሉ። ለዚህም ዘውዲቱ መታሰቢያ፣ ሚኒልክ እና ትላንት የመረቅነው ራስ ደስታ ህያው ማሳያዎች ናቸው።
ይህ ሁኔታ በሁሉም ሆስፒታሎቻችን ላይ እንዲተገበር ጠንክረን እንሰራለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን አና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
እነሆ ዛሬም ሌላ አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል!!
ዛሬ በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል” ገንብተን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ነባሩ ሆስፒታል በጣም በማርጀቱ ለታካሚዎች የማይመች መጨናነቅ የነበረበት፣ የነበሩት ኋላቀር የህክምና መሳሪያዎች ለታካሚዎች ብቻ ሳይሆን ለባለሙያዎቹም አገልግሎት ለመስጠት ጥራቱን ያልጠበቀና ምቹ ያልሆነ ነበር።
ይህንን አስከፊ ሁኔታ ታሪክ በማድረግ እጅግ ንፁህ ውብ የሆነ ባለ7 ወለል ህንፃ ገንብተን በይዘቱ የህክምና አገልግሎቶችን እጅጉን የሚያሻሽል፤ የዘመኑ ቴክኖሎጂ የተሟሉለት ሲሆን በነባሩ ህንፃ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በአጥፍ የሚያሳድግ ማዕከል ነው።
በአዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል የ2026 ምርቶች የሆኑ AI የሚጠቀሙ ዲጅታል ኤምአርአይ (MRI)፤ ሲቲስካን፣ የአልትራሳውንድ፣ ተንቀሳቃሽ ኤክስሬይ፣ በሰዓት 30,000 ሊትር የሚያመርት የኦክሲጅን ማምረቻ (Oxygen plant)፤ እንዲሁም ቀድሞ የነበረው የአስተኝቶ ህክምና አልጋ ከ147 ወደ 360 አድጓል፥ የኦፕሬሽን ክፍል ከ3 ወደ 7፣ የፅኑ ህክምና ክፍልም ወደ 19 አድጓል። በተጨማሪም ሰፊና የላቀ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ስታንዳርዱን ጠብቆ ተደራጅቷል። የሰራተኛ ማረፊያ ክፍሎች፣ ላይብረሪ፤ ዘመናዊ ቢሮዎች፤ መሰብሰቢያ አዳራሾች እና የሰራተኛ ካፍቴሪያ አገልግሎት ለታካሚዎች በሚመች መልኩ ተገንብቶና ተደራጅቶ ለአገልግሎት በቅቷል።
አዲስ አበባ ላይ ያለው የጤና አገልግሎት ፍላጐት በመንግስት ብቻ የማይሟላ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ በመደገፍም ወደ ውጭ በመሄድ ይደረግ የነበረውን ህክምና በአገር ውስጥ የህክምና አገልግሎት መስጠት መቻሉ፣ ዓለም በዘርፉ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የጀመርናቸው ሥራዎች ህያው ምስክር ናቸው።
አዲሰ የላቀ የህክምና ማዕከል በፍጥነትና በጥራት ተገንብቶ የነበረውን አገልግሎት በአጥፍ በማሳደግ የላቀ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ሆኖ እንዲጠናቀቅ አብራችሁን የነበራችሁ፣ የተባበራችሁ፣ የገነባችሁ በራሴና በታካሚው ሥም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በአከራይ ተከራይ ውል እድሳት ፈፅሞ የተከለከሉ ጉዳዮች?
✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
✍ የውል እድሳት ምዝገባን አለመፈጸም በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ የተጀመረውን አዲስ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እድሳት ምዝገባ ሳያከናውን መቅረት ወይም መሸሽ አይቻልም።
✍ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ዕድሳት አለማስመዝገብ፤
✍ ሕገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በከተማ አስተዳደሩ
ከተቀመጠው የ11.5% ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ በላይ መጨመር ወይም በየምክንያቱ ዋጋ ማናር በጥብቅ የተከለከለ ነው።
✍ አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
✍ በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
✍ አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ
እንዲፈጸም ማስገደድ፤
✍ በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የሆነ የኤሌክትሮኒክስ መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈጸም፤
✍ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት
እንዲቀመጥ ማድረግ፤
✍ የመንደር ወይም የ«ልዩ» ውል ማሰር፦ በየደረጃው በሚገኙ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ፅህፈት ቤቶች ሳይመዘገብና ዕውቅና ሳይሰጠው፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ብቻ የሚደረግ ማናቸውም ዓይነት "የመንደር ውል" ወይም "የውስጥ ስምምነት" በሕግ ፊት ዋጋ የለውም፤ የተከለከለም ነው።
✍ በጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አካባቢ የሚደረጉ ሕገ-ወጥ ውሎች በኮንዶሚኒየም መንደሮች ውስጥ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶችን ያለ ቢሮው ዕውቅናና ምዝገባ በሕገ-ወጥ መንገድ ማከራየትና ውል መዋዋል የተከለከለ ነው።
ከላይ የተጠቀሱ ክልከላዎችን የፈጸመ አስተዳደራዊ ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡
" ሕጋዊ ምዝገባን ባለመፈጸም ራስዎን ለሕግ ተጠያቂነትና ለአላስፈላጊ ቅጣት አያጋልጡ!"
5 ቀን ቀረው!
*
ኢትዮጵያውያን በጋራ የሚመክሩበት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ሊካሄድ 5 ቀን ቀረው!
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ትመክራለች!
የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ለተጠሪ የልማት ድርጅቶች የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ የሥራ አፈጻጸምና የፕሮጀክት ድጋፍና ክትትል ጀመረ
ሐምሌ 02/2018 :-የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን ለተጠሪ የልማት ድርጅቶች የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ የሥራ አፈጻጸምና የፕሮጀክት ድጋፍና ክትትል ሥራዎችን በቄራዎች ድርጅት እና በኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት በዛሬው ዕለት ጀምሯል።
የድጋፍና የክትትል መርሃ ግብሩ የድርጅቶችን የዕቅድ አፈጻጸም፣ የፕሮጀክቶችን እንቅስቃሴ፣ የበጀት አጠቃቀም፣ የፋይናንስ አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ብቃትን በተጨባጭ በመገምገም የተመዘገቡ ጠንካራ አፈጻጸሞችን ለማጠናከር እንዲሁም የሚታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ በመለየት ተገቢ የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ለማስቻል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም በቦታው በመገምገም በቀጣይ የሚከናወኑ ሥራዎች የተሻለ ቅንጅት፣ ፍጥነትና ውጤታማነት እንዲኖራቸው የሙያ ድጋፍና አስፈላጊ ምክረ ሃሳቦች እንደሚሰጡ ተጠቁሟል።
የማጠቃለያ ድጋፍና ክትትል ተግባር የተጠሪ የልማት ድርጅቶችን ውጤታማነት፣ ተጠያቂነትና ተቋማዊ አቅም ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ሲሆን፣ ከሚገኙ ግኝቶች በመነሳትም ለ2019 በጀት ዓመት የተሻለ የሥራ ዕቅድ፣ የአፈጻጸም ሥርዓትና የፕሮጀክት አስተዳደር እንዲዘረጋ ጠንካራ መሠረት እንደሚፈጥር አመልክቷል።
የድጋፍና የክትትል ሥራው በቀጣዮቹ ቀናትም በሁሉም ተጠሪ የልማት ድርጅቶች በመቀጠል የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸምና የፕሮጀክት ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ ተገልጿል።
