uk
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закритий канал

Показати більше
1 146
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
photo content

photo content

photo content

photo content

ከጉለሌ ክ/ከተማ ለመጡ ከፍተኛ የፖሊስ አመራሮች/ሹፌሮች በአውቶሞቲቭ ስ/ክፍል እሮብዕ (05/10/2016) የመጀመሪያ ዙር ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። ስልጠናው መሰረታዊ የተሽከርካሪ ብልሽት ማወቂያ እና የመከላከያ ዘዴዎች ላይ ያጠነጠነ ሲሆን የአካዳሚክ ጉዳዎች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በድፓርትመንቱ በመገኝት ስልጠናውን አስጀምሯል።

photo content

ሰላም ሰላም ለክህሎት ታወዳዳሪዎች ስማቺው ከዚህ በታች የተጠቀሰ በሙሉ በክላስተር ደረጃ ተወዳድራቺው 1ኛ ለወጣቺው በከታማ ደረጃ የሚካሄደው ዉድድር የፊታቺን ሐሙስ እና አርብ ሲሆን ሰኔ 6 የአንቀሳቃሽ እና የሰልጣኝ ሲሆን አርብ ሰኔ 7 የአሰልጣኞች መሆኑን አዉቃቺው ከወዲው ዝግጅት እንድታደርጉ እያልኩ 1. በሆቴል ቱሪዝም ዲፓርትመንት የምትመዘኑ መመዛኛ ቦታ (ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ )መሆኑን እንድታዉቁ 2. በቴክስታይል ተመዛኝ መመዘኛ ቦታ (A. A Tegbared Polytechnic college)መሆኑን እንድታዉቁ . 3.ከላይ ከተጠቀሱት ዉጭ ያላቺው ተመዛኞች መመዘኛ ቦታቺው (ምርታመነት ) መሆኑን እንድታዉቁ አሳስባለው. የሰልጣኝ እና አንቀሳቃሽ ተመዛኝ ስም 1.ሩታ tewodros 2.እድላዊት እንዳለ 3.ፍፁም ተስፋዬ 4.ሄኖክ ካሳሁን የአሰልጣኝ ተመዛኝ ስም 1.ገታሰው ብዘለው 2.ዘመላክ ጌጡ 3.መላኩ ግርማ 4.ሺመልስ ግርማ 5.ሲሳይነሽ ጫኔ 6.መልካም ተረፈ 7.ዘሪሁን ፀጋሁን 8.ደበሎ ኦሊ 9.ኪሩቤል አከል 10.ኤርሚያስ ጴጥሮስ 11.ለሚ ተሬሳ 12.ጉቱ ልኬሳ ማሳሳቢያ : ምዘናው የሚጀምረው ጥዋት 2:30 መሆኑን አዉቃቺው አርፍዶ ለሚመጣ የማያስገቡ ስለሆነ ቀድማቺው ለመገኘት ሞክሩ.

⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️ 39% ⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️

ሠላም! ሠላም! የመቶኛ ዓመት የክፍለ ዘመን በዓል አከባበር ሞቶ መረጣው እንደቀጠለ ነው። በነበሩት ምርጫዎች ተሳትፎ ያደረጋችሁትን በሙሉ ምስጋና እያቀረብን ግሩፑ ላይ ካለነው 475 ውስጥ 117 (25%) ብቻ ነው ድምፅ የሰጡት በመሆኑም ብዙሃኑን ባሳተፈ መልኩ መረጣውን ለማከናወን ሁለት ከፍተኛ ድምፅ ያላቸው ተለይቷል። በምርጫው ተሳትፎ ያድርጉ! መረጃውንም ለሌሎች ያድርሱ

photo content
+4

ዕለተ ዓርብ ግንቦት 30/2016ዓ.ም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሴቶችን የማነቃቃትና የማብቃት ስልጠና ተጠናቀቀ። በግንቦት 28/2016ዓ.ም የተጀመረው ሴቶችን የማብቃት  ስልጠና በዛሬው ዕለትም የአመራር ምንነት፣ መሪ ሊላበሳቸው የሚገባ ባህርያት ፣ ውጤታማ አመራር እና የተግባቦት አይነቶች በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን በሁለትዮሽ መስተጋብር  ሰፊ የቡድን ውይይት አካሂደዋል። በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በራስ ተነሳሽነት ስልጠናውን ላዘጋጁት አሠልጣኝ ያለምወርቅ በቀለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ስልጠናው ሴቶችን ለማብቃትና ወደ ተሻለ ደረጃ ለማምጣት ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ገልጸው ሴቶችን ማብቃት የሴትነት ድጎማ ሳይሆን የሚገባቸው ና ስለሚችሉም የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+4

ዕለተ ሐሙስ ግንቦት 29/2016ዓ.ም "የ ISo 21001:2018 EOMS " ይፋዊ የትግበራ መርሃ ግብር ተከናወነ። ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘትና ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት በተለያየ ደረጃ  እየተከናወነ መቆየቱ ይታወሳል። በዛሬው ዕለት በይፋ የተጀመረው የትግበራ መርሃ ግብር  ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የቅድመ ዝግጅት ስራው እውን እንዲሆን ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ለተሳተፉ አባላት ምስጋናቸውን አቅርበው በተለያየ ደረጃ የተፈጠረውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመቀየር ሂደት የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቃል ሲሉ አክለውም የኮሌጁን መቶኛ ዓመት ስናከብር ኮሌጁ የነበረውን መልካም ስምና ዝና በማስጠበቅ በዓለማቀፍ እውቅና እንዲያገኝ በማድረግ ነው።  ዓለማቀፍ እውቅና ካለውና መልካም ስምና ዝናውን ከጠበቀ ኮሌጅ መመረቅም ሆነ መስራት የሚያስገኘው ጠቀሜታ በቀላሉ የሚገመት አለመሆኑንም ጠቁመዋል። በመቀጠልም የትግበራው ዓላማ ምቹ የስራ አካባቢና ወጥ የሆነ ተቋማዊ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ነው ያሉት አስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ የተዘጋጁት 546 ሰነዶች  በሚመለከተው አካል ጸድቀው ተግባራዊ ለማድረግ የቀረቡ መሆኑንና በሂደት ሌሎች ሰነዶች የሚካተቱ መኖራቸውንም ገልጸዋል ። የመጀመሪያ ዙር ትግበራው ለሦስት ወራት የሚቆይ መሆኑን በመግለጽ ይህ እውን እንዲሆን በጋራና በመናበብ እጃችን ላይ ባለው ቁሳቁስና የሰው ሃይል አቅም  መስራት እንደሚገባ በአጽንኦት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የኮሌጃችን የሙዚቃና የቲያትሪካል አርት ሰልጣኞች ይፋዊ ትግበራው በደማቅ ሁኔታ እንዲበሰር በማድረጋቸው ምስጋና ይገባቸዋል።                                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ሐሙስ ግንቦት 29/2016 ዓ.ም    ለኮሌጁ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው   በስነ-ምግባር ብዥታዎችና በጥቅም ግጭት ላይ ያተኮረ ሲሆን በስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳሬክቶሬት አማካኝነት የተዘጋጀ ነው። የስልጠናው ዓላማ በተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ብዥታዎችና የጥቅም ግጭቶችን አስመልክቶ ያለውን ብዥታ በማጥራት፣ ግንዛቤ በመፍጠር ና በማዳበር አሰራርን በመርህ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረግ ላይ ያለመ ነው። ስልጠናውን የሰጡት በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነ-ምግባርና ፀረ- ሙስና ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው ሲሆኑ በስልጠናው የተካቱት ርዕሰ ጉዳዮች፦ - የስነ-ምግባር ብዥታዎች - የመልካም አስተዳደር መርሆዎችና ተግዳሮቶች - በመንግስት ተቋማት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን     የሚጠቅሙ ነጥቦች - ስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ያለው    ፋይዳ - የጥቅም ግጭት ምንነት - የጥቅም ግጭት መንስኤዎች - የጥቅም ግጭት  ገጽታዎች - የጥቅም ግጭት አይነቶች በዝርዝር ተዳሰዋል። ስልጠናው በሁለትዮሽ መስተጋብር የተከናወነ ሲሆን በመጨረሻም ከቤቱ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት ከተደረገባቸው ቦኋላ ስልጠናው ተጠናቋል።                                     ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content

photo content