uk
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закритий канал

Показати більше
1 146
Підписники
-224 години
-47 днів
-1930 день
Архів дописів
photo content
+3

photo content
+9

ጥር 30/2017 ዓ.ም የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ለ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርእሳነ መምህራን እና ሱፐር ቫይዘሮች በTVT ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረክ አካሄደ ። የውይይት መድረኩን ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱል በር መሐመድ የሙያ ትምህርት የተስፋፋበትን እና አስፈላጊነቱ ላይ አውስተው TVT የወደቁ ተማሪዎች የሚገቡበት/የሚሰባሰቡበት ነው የሚለው እሳቤ የተሳሳተ መሆኑን ጠቅሰው ይህ የሆነበትን ምክንያት ሲያብራሩ በአመሠራረቱላይ ያልተወያየን እን የጋራ ያላደርገነው በመሆኑ የተፈጠረ ነውም ብለዋል ።  አያይዘውም ይህ ዘርፍ በ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት "የኤስቴቲክስ ክወና"  በመባል በቅንጅት የሚሰጥ ሲሆን በ2ኛ ደረጃ  የሙያ ትምህርትም  ተጀምሯል ።ሆኖም ግን በቂ የማስተማሪያ ማቴሪያል የሌላቸው በመሆኑ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ያለውን ክፍተት አመላክተዋል።  በመሆኑም የጋራ ሃላፊነት ያላቸው ተቋማት ተቀራርበው በመመካከር  የሰው ሃይልና ሌሎች ሃብቶችን በመጋራት መስራት መደጋገፍ እንደሚቻል ጠቁመው  ለዚህም ኮሌጃችን በማንኛውም ግዜ ቢመጡ ለማስተናግ ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል ። በመቀጠልም የኢንደስትሪ ትስስርና የስራ እድል ፈጠራ ባለሙያ አቶ ሙሉጌታ የTVT እስትራቴጅ የተብራራ ሲሆን ተሳታፊዎቹ እስትራቴጂውን በቅጡ በመረዳት ለማስፈጸም የሚኖራቸውን ሚና ያስገነዘበ ነበር ። ከስትራቴጂው ማብራሪያና ገለጻ በኋላ ተሳታፊዎቹ ኮሌጁ ስለሚሰጣቸው ስልጠናዎች የበለጠ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ የኤስቴቲክስ፣የብረታ ብረትና የሌዘር ስልጠና ዘርፍ የስልጠና ሾፖችን ተዘዋውረው እንዲጎበኙ ተደርጓል። ርእሳነ መምህራንና ሱፐር ቫይዘሮቹ ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና መደሰታቸውን በመግለጽ ከአሁን ቀደም ስለ TVT በዚህ ልክና መልክ የሚገለፅ መረጃ ካለመኖራቸውም በላይ ኮሌጁ ለስልጠና ያለው ዝግጅትና የሾፖች አደረጃጀት ከግምታቸው በላይ  ሆኖ እንዳገኙት ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት ቃለ ምልልስ ሳይሸሽጉ ተናግረዋል ።  ከገለጻውና ጉብኝቱ በኋላ ርእሳነ ምህራንኑ ሱፐር ቫይዘሮቹ በቢሯቸው አማካኝነት ከኮሌጁ ጋር የጋራ ዕቅድ በማዘጋጀት እንደሚተገብሩ፤ በሚገኙ አጋጣሚዎች ሁሉ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እንደሚሰሩና ተማሪዎች በዕውቀት ላይ የተመሠረተ የሙያ ምርጫ እንዲኖራቸው በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ገልፀዋል ። "ልጆች ቦታ አላቸው" በማለት ንግግር  ያደረጉት በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ት/ት ሱፐር ቫይዘር ዳይሬክተር አቶ ጥላዬ ጉሩሙ  ከአጠቃላይ ትምህርት ማጠናቀቅ በኋላ የከፍተኛ ትምህርት እድል ያላገኙ ወጣቶች ባክነው እንዳይቀሩና የTVT እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሁለቱም ተቋማት ጥረት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

ጥር 30/2017 ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች በንግድ ስራ ክህሎት ለሚሰጠው ስልጠና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡ ለስራ ፈላጊ ወገኖች በንግድ ስራ ክህሎት በተ
+8
ጥር 30/2017 ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወገኖች  በንግድ ስራ ክህሎት ለሚሰጠው ስልጠና ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡ ለስራ ፈላጊ ወገኖች በንግድ ስራ ክህሎት በተለያዩ ግዚያት በርካታ ወገኖችን እያሰለጠነ የሚገኘው ኮሌጃችን እንደተለመደው ሁሉ ስራ ፈላጊ ወገኖች መደበኛውን የሙያ  ስልጠና  ከመጀመራቸው በፊት የህይወት ክህሎት ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን ሰልጣኞች እንደየ ዝንባሌያቸው ስራ ፈጥረው የራሳቸውን ስራ ለሚጀምሩ እና ተቀጣሪ ሆነው መስራት የሚፈልጉ ወኖችን ያማከለ ስልጠና የሚወስዱ ሲሆን ስልጠናው የተግባቦት አቅምን በማሳደግ የሙያ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት እንዲሁም በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ስራቸውን በአግባቡ ለመከወን ትልቅ ሚና ያለውና  በህይወታቸው ስኬታማ ለመሆን መከተል ያለባቸውን ነገሮች በዝርዝር ያቀረቡት የስልጠናና አካዳሚክ አስተባባሪ አቶ ዘላለም ሲሳይ ናቸው ።   በዚህ ስልጠና የተሳተፉት ከ 1100  በላይ በንግድ ዘርፍ የሚሰለጥኑ ስራ ፈላጊዎች እና ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ የመጡ 37 አካል ጉዳተኞች በቆዳ ስራ ና ጋርመንት የሚሰለጥኑ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በያዝነው ሳምንት የህይወት ክህሎት ስልጠናውን አጠናቀው በከቀጣይ ማክሰኞ ጀምሮ ሞያዊ ስልጠናውን የሚጀምሩ መሆናቸውን እና ከስልጠና በኋላ በምዘና ብቃታቸውን አረጋግጠው የሚወጡ ይሆናል በማለት የስልጠና አስተባባሪው አቶ ታደሰ አበራ መረጃውን አጋርተውናል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

ቀናት ወደ መቶኛ  ዓመት....... ⤵️⤵️

photo content

photo content

ቀናት ወደ መቶኛ ዓመት....... ⤵️⤵️

photo content

photo content
+4

photo content
+8

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም የሁለት ተከታታይ ቀናት ዎረክሾፕ እና ስልጠና  በአዳማ ተካሃደ። በዚህ ዎርክ ሾፕ የ(EASE (Education and Skill Employability) ፕሮጀክት አጠቃላይ ዕቅድ ለኮሌጁ ማኔጅመንት፣ ለአካዳሚክ  እስታፍ እና   ከአስተዳደር  ለተውጣጡ  ተሳታፊዎች የኢዝ ፕሮጀክት ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተሰርተዋል፡፡ በዎርክሾፑ የተከናወነው ሌላው አብይ ጉዳይ ደግሞ በሞሃስ ኮንስልታንት የተሰጠው የሊደርሽፕ ስልጠና  ለኮሌጁ ማኔጅመንት፣ ለአካዳሚክ  እስታፍ እና   ከአስተዳደር  ለተውጣጡ  ተሳታፊዎች ተሰጥቷል። በ EASE project በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ ኮሌጆች ዉስጥ ተወዳድረዉ ያሸነፉት 3 ኮሌጆች ሲሆኑ ከነዚህ መካከል አንዱ እንጦጦ ፖሊ ኮሌጅ መሆኑን ታውቋል፡፡  ይህ እድል የተገኘው ውድድሩን ለማሸነፍ ባስቻሉት 5 የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ከፍተኛ ጥረት ስለሆነ ላስገኙት ዕድል በኮለጁ እና በዝግጅት ክፍላችን ስም አስተባባሪዎቹ ምስጋና ይድረሳቸው እንላለን፡፡  ይህ ዕድል  ለኮሌጁ ማህበረሰብ  ባጠቃላይ እና ለሴቶች እንደዚሁም  ለአካል ጉዳተኞች  ጥቅም ደግሞ በተለየ የሚሰራ ሲሆን በ world bank እንደሚታገዝም ለማወቅ ተችለዋል፡፡ በተያያዘ በዎርክሾፑ በኮሌጅ ውስጥ ሊሰሩ የታሰቡት ፕሮጀክቶች ደግሞ ዘመናዊ የከብትች መኖርያ (በረት) ፡ ካፈቴሪያ  ፡ እግርኳስ ሜዳ እና የግቢዉ መግቢያ መንገዶችን  ማሳመር እና ግቢ የማስዋብ ስራዎችን እንደሚያካትት ታውቋል።  በተመሳሳይ የ ISO ሂደት እና አካሄድም ለመዳሰስ ተችለዋል፡፡ በተጨማሪም የንግድ ፈቃድ ሂደት የወጣላቸዉ ዲፓርትመንቶች እና ኢንተርፖራይስ ወደፊት እንዴት አቅደዉ መስራት እንዳለባቸዉም  አቅጣጫ በመስጠት ወደፊት ብዙ ስራ መሰራት እንደሚገባ የሚገልጹ ፕሮግራሞች መካሄዳቸዉን የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች አሳዉቀዋል፡፡                           ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

ዕለተ ሐሙስ ጥር 22/2017ዓ.ም ለኮሌጁ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች Root cause Analysis and Corrective Action Plan ላይ ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የሽ
+3
ዕለተ ሐሙስ ጥር 22/2017ዓ.ም ለኮሌጁ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች  Root cause Analysis and Corrective Action Plan ላይ ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የሽሮ ሜዳ ካምፓስ ም/ዲን አት ተስፋ ጽዮን የISO 21001:2018 EOMS " ትግበራ እየተጠናከረ የመጣ መሆኑን ጠቁመው የታለመለትን እውን ለማድረግ በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል ። ለውይይት በቀረበው Root cause Analysis and Corrective Action Plan ላይ ያተኮረ ገለጻ ያቀረቡት አስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ  ከቤቱ ለቀረበላቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል ።                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

ቀን 22/05/2017 ዓ.ም የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስነ ምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኞች የስነ ምግባር ክበብ አባላት ጋር የልምድ ልውው
+3
ቀን 22/05/2017 ዓ.ም የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስነ ምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኞች የስነ ምግባር ክበብ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ ፡፡ የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስነ ምግባርና ፀረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ የሆኑት አቶ መከታው ሹመት እና የሰልጣኞች የስነ ምግባር መከታተያ ክበብ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪ የሆነው ተማሪ አቤሴሎም ብርሃኑ ስለክበቡ የስራ እንቅስቃሴ ገለጻ አድርገዋል ፡፡ የጄ/ዊ/ፖ/ቴ/ኮ የስነ ምግባር ክበብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን በክበቡ አባል ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ፡፡ ኮሌጁን ከሌሎች ኮሌጆች  ለየት የሚያደርገው በሌሎች ቴክኒክና ሙያ ተቋማት የማይገኘው የሙዚቃና አርት  ዲፓርትመንትን የያዘ ሲሆን ከትምህርት ክፍሉ ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረምና የስልጠና ዘርፉን ሰልጣኞች  በክበቡ በአባልነት በመያዝ  ክፍሉ በሚያዘጋጃቸው የንቅናቄ መድረኮችና የክበቡን የስራ እንቅስቃሴ በሙዚቃ፤ ግጥምና  ጭውውት በማስደገፍ የስነምግባርን አስተምህርቶችን ለሰልጣኙ በማድረስ የብልሹ አሰራርና የሙስና መገለጫዎችን  እያዝናና በማሳወቅ ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ለመረዳት ችለናል ፡፡

ዕለተ ሐሙስ ጥር 22 /2017 ዓ.ም በንግድ ዘርፍ ሲሰጥ የነበረው ሦስተኛ ዙር COC ምዘና ተጠናቀቀ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡና በንግድ ዘርፍ አጫጭር ስልጠና ለሰለጠኑ 420 ስራ ፈላጊ ወገኖች
+5
ዕለተ ሐሙስ ጥር 22 /2017 ዓ.ም በንግድ ዘርፍ ሲሰጥ የነበረው ሦስተኛ ዙር COC  ምዘና ተጠናቀቀ። ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡና በንግድ ዘርፍ አጫጭር ስልጠና ለሰለጠኑ 420 ስራ ፈላጊ ወገኖች ሦስተኛ ዙር የCOC ምዘና ከጥር 20 -  ጥር 22/ 2017ዓ.ም  ሲሰጥ የቆየው ምዘና መጠናቀቁን አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ገልፀዋል።                             ኮምንኬሽን ቡድን

ቀናት ወደ መቶኛ  ዓመት....... ⤵️⤵️