1 149
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 149
የተፈሪ መኮንነን ፖሊ ቴክንክ ኮሌጁ የ2017 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞችን የማስመዘን የንቅናቄ መድረክ አዘጋጃ!
🇹የካቲት 02/2018 ዓ.ም🇪
የተፈሪ መኮንነን ፖሊ ቴክንክ ኮሌጅ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሰልጣኞችን ለኢንዱስትሪ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማድርግና ለስራ ዝግጁ አድርጎ ለኢንዱስትሪዎች ማቅረብ ዋና ተልኮው ነው፡፡ ይህን ለማረጋገጥ ኮሌጆች የሰልጣኞችን ብቃት በምዘና መረጋገጥ እንዳለባቸው ይታወቃል፡፡ ይህን ተልኮ ለመወጣት የ2017 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞችን በልዩ ልዩ ምክኒያቶች ሳይመዘኑ የቀሩ ሰልጣኞችን ክህሎት ክፍተታቸውን በመለየትና በመሙላት እስከ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድረስ ሁሉንም ተመራቂ ሰልጣኞች ለማስመዘን የAction plan በማውጣት እንዲሰራ በመድረኩ ላይ ተገልጻል፡፡ ስለሆንም ሁሉም ከአሰልጣኝ ጀምሮ ሰልጣኞችን ዝግጁ ከማድረግና ከማሰመዘን ጋር ተባባሪ ሆኖ ምዘናው ውጤታማ እንዲሆን መስራት እንዳለብን ተገልጻል፡፡
https://t.me/EntotoPtc1917
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች
1. https://vm.tiktok.com
2. https://t.me/EntotoPtc1917
3. https://youtube.com/@entototms
4. https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ።
🇹የካቲት 02/2018 ዓ.ም🇪
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክ የኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሃያ አምስተኛ ሳምንት ተካሄደ። በኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ መድረኩን የከፈቱ ሲሆን የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ የኮሌጁ ማህበረሰብ የልምድ ልውውጥ በመውሰድ በተሻለ አፈፃፀም ስራውን እንዲያከናውን ማገዙን ገልፀዋል ።
በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት የኮሌጁ የኮንስትራክሽን ዘርፍ አሰልጣኝ አቶ ተስፋዬ ሀብቴ ወ/አብ "ስራን በራስ ተነሳሽነት መስራት " በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ ፈጥረዋል ። ከአስራ አምስት በላይ የስራ ልምድ ያላቸው ሲሆን ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ሙሉ በሙሉ ስራ በማስያዝ ያላቸውን ልምድ አካፍለዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://t.me/EntotoPtc1917
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች
1. https://vm.tiktok.com
2. https://t.me/EntotoPtc1917
3. https://youtube.com/@entototms
4. https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአብሮነት ፕሮግራም ።
🇪🇹 ጥር 30/2018 ዓ.ም 🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መቶኛ አመት ክብረ በዓል በማስመልከት ፣የኮሌጅን የስም ቅያሬ፣ የISO 21001:2018 EOMS የእውቅና ሰርተፍኬት እና ከኮሌጅ በሪፎርም ድልድል ወደ ሌላ ኮሌጅ የሄድ ሰራተኞች ሽኝት እና አዲስ ሰራተኞች አቀባበል በማስመልከት የተዘጋጀ የአብሮነት ልዮ ፕሮግራም ።
ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ " የእንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ለኮሌጅ ማህበረሰብ ያስተላለፉ ሲሆን የኮሌጁ አመራሮች ለፕሮግራሙ መሳካት ላሳዩት ቁርጠኝነት አክብሮታቸውን ገልፀዋል ።የኮሌጅ ማህበረሰብ ተባብሮ በመስራት ላሳየው ውጤት አመስግነው መልካም የአብሮነት ጊዜ እንዲሆን በመመኝት ፕሮግራሙን ከፍተዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሴት ሰራተኞች የሀብት አያያዝ ስልጠና ተጠናቀቀ ።
🇪🇹 ጥር 29/2018 ዓ.ም 🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች የሀብት አያያዝና አጠቃቀም እና ኮሚኒኬሽን ከፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምርትና ስልጠና ኢንስትቲውት በመጡ አሰልጣኞች ለኮሌጅ ሴት ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ ።
የኮሌጁ አካዳሚክ ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የኢዝ (EASE) ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሴቶችን ተሳትፎና ክህሎት ለማጠናከር የሚሰራ ሲሆን፣ ለዚህ ስልጠናም አስፈላጊውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ እጅግ የተሳካ ስልጠና በመሰጠቱ ስራና ክህሎት ኢንስቲትዩት እና የፕሮጀክቱን አስተባባሪዎች አመስግነዋል ።
በስልጠናው የሚሳተፉ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚሰሩ ሴት አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች በስራ ቦታቸው ውስን የሆኑ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም፣ ብክነትን መቀነስ እና የተቋሙን አጠቃላይ ውጤታማነት ማሳደግ እንዳለባቸው መልክት አስተላልፈዋል ።
የኮሌጅ የተቋማት ልማት አስ/ጉ/ም ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ በስልጠናው መዝጊያ ላይ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች ሴት ሰራተኞች በውሳኔ ሰጪነትና በሀብት አስተዳደር ያላቸውን ሚና ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመው፣ የተገኘውን እውቀት በተግባር ላይ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም ስልጠናው በኢዝ ፕሮጀክት (Education and Skills for Employability EASE) ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ የሰው ኃይል፣ የፋይናንስና የማቴሪያል ሀብቶችን በብቃትና በውጤታማነት ማስተዳደር የሚያስችል አቅም ለመገንባት የሚያስችል ግንዛቤ እንዳገኙ ስልጠናውን የወሰድ የኮሌጅ ሰራተኞች ገልፀዋል ።
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
እንኳን ደስ አላቹ !!!
የEASE ፕሮጀክት በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ዘመናዊ የአይሲቲ መሰረተ ልማት ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
🇪🇹 ጥር 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመማር ማስተማር ሂደቱን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እና ዓለም የደረሰበትን የዲጂታል ዕድገት ለመድረስ ያለመ ሰፊ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) መሰረተ ልማት ግንባታ እያከናወነ መሆኑን አስታወቃል።
ኮሌጁ በምስራቅ አፍሪካ የክህሎት ሽግግር እና የስራ ፈጠራ (EASE) ፕሮጀክት ተጠቃሚ በመሆን፣ በዓለም ባንክ (World Bank) በሚሸፈን ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ይህን ግዙፍ የቴክኖሎጂ ግንባታ ዝርጋታ ስራ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ።
ይህ ፕሮጀክት በዋናነት ዘመናዊ የኔትወርክ እና የዋይፋይ (WiFi) መስመር ዝርጋታን፣ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከል (Data Center) ግንባታን እንዲሁም የኃይል አቅርቦት መቆራረጥን የሚቀርፍ የጄኔሬተር ተከላን ያካተተ ነው። እነዚህ መሰረተ ልማቶች በኮሌጁ ለሚሰጡ ሁሉም የስልጠና ዘርፎች ጥራት ያለው እና ቀልጣፋ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችሉ ናቸው።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአካዳሚክ ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሪት ቤተልሄም አሰፋ እንደገለፁት ግንባታው አሁን ዓለማችን ያለችበትን የዲጂታላይዜሽን (Digitalization) ዘመን ያገናዘበ ነው።
ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ "በኮሌጃችን የኢንተርኔት ተደ ራሽነትን ለማስፋፋትም እና የሰልጣኞችን የተግባር ልምምድ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እነዚህ መሰረተ ልማቶች ወሳኝ ናቸው። በአሁኑ ሰዓት የዳታ ማዕከል ግንባታው እና የኔትወርክ ዝርጋታው በጥሩ ፍጥነት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የ EASE ፕሮጀክት ድጋፍ ኮሌጁን ወደ ዲጂታል ማዕከልነት ለመቀየር እና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።በመሆኑም ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ፈጣን እና አስተማማኝ የቴክኖሎጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
እንኳን ደስ አላቹ !!!
የEASE ፕሮጀክት በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ዘመናዊ የአይሲቲ መሰረተ ልማት ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
🇪🇹 ጥር 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመማር ማስተማር ሂደቱን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እና ዓለም የደረሰበትን የዲጂታል ዕድገት ለመድረስ ያለመ ሰፊ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) መሰረተ ልማት ግንባታ እያከናወነ መሆኑን አስታወቃል።
ኮሌጁ በምስራቅ አፍሪካ የክህሎት ሽግግር እና የስራ ፈጠራ (EASE) ፕሮጀክት ተጠቃሚ በመሆን፣ በዓለም ባንክ (World Bank) በሚሸፈን ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ይህን ግዙፍ የቴክኖሎጂ ግንባታ ዝርጋታ ስራ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ።
ይህ ፕሮጀክት በዋናነት ዘመናዊ የኔትወርክ እና የዋይፋይ (WiFi) መስመር ዝርጋታን፣ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከል (Data Center) ግንባታን እንዲሁም የኃይል አቅርቦት መቆራረጥን የሚቀርፍ የጄኔሬተር ተከላን ያካተተ ነው። እነዚህ መሰረተ ልማቶች በኮሌጁ ለሚሰጡ ሁሉም የስልጠና ዘርፎች ጥራት ያለው እና ቀልጣፋ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችሉ ናቸው።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአካዳሚክ ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሪት ቤተልሄም አሰፋ እንደገለፁት ግንባታው አሁን ዓለማችን ያለችበትን የዲጂታላይዜሽን (Digitalization) ዘመን ያገናዘበ ነው።
ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ "በኮሌጃችን የኢንተርኔት ተደ ራሽነትን ለማስፋፋትም እና የሰልጣኞችን የተግባር ልምምድ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እነዚህ መሰረተ ልማቶች ወሳኝ ናቸው። በአሁኑ ሰዓት የዳታ ማዕከል ግንባታው እና የኔትወርክ ዝርጋታው በጥሩ ፍጥነት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የ EASE ፕሮጀክት ድጋፍ ኮሌጁን ወደ ዲጂታል ማዕከልነት ለመቀየር እና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።በመሆኑም ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ፈጣን እና አስተማማኝ የቴክኖሎጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
እንኳን ደስ አላቹ !!!
የEASE ፕሮጀክት በዓለም ባንክ ድጋፍ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ዘመናዊ የአይሲቲ መሰረተ ልማት ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
🇪🇹 ጥር 27/2018 ዓ.ም 🇪🇹
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የመማር ማስተማር ሂደቱን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እና ዓለም የደረሰበትን የዲጂታል ዕድገት ለመድረስ ያለመ ሰፊ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) መሰረተ ልማት ግንባታ እያከናወነ መሆኑን አስታወቃል።
ኮሌጁ በምስራቅ አፍሪካ የክህሎት ሽግግር እና የስራ ፈጠራ (EASE) ፕሮጀክት ተጠቃሚ በመሆን፣ በዓለም ባንክ (World Bank) በሚሸፈን ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ይህን ግዙፍ የቴክኖሎጂ ግንባታ ዝርጋታ ስራ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ተጀመረ።
ይህ ፕሮጀክት በዋናነት ዘመናዊ የኔትወርክ እና የዋይፋይ (WiFi) መስመር ዝርጋታን፣ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከል (Data Center) ግንባታን እንዲሁም የኃይል አቅርቦት መቆራረጥን የሚቀርፍ የጄኔሬተር ተከላን ያካተተ ነው። እነዚህ መሰረተ ልማቶች በኮሌጁ ለሚሰጡ ሁሉም የስልጠና ዘርፎች ጥራት ያለው እና ቀልጣፋ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችሉ ናቸው።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአካዳሚክ ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሪት ቤተልሄም አሰፋ እንደገለፁት ግንባታው አሁን ዓለማችን ያለችበትን የዲጂታላይዜሽን (Digitalization) ዘመን ያገናዘበ ነው።
ምክትል ዲን እና ጊዜያዊ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ "በኮሌጃችን የኢንተርኔት ተደ ራሽነትን ለማስፋፋትም እና የሰልጣኞችን የተግባር ልምምድ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እነዚህ መሰረተ ልማቶች ወሳኝ ናቸው። በአሁኑ ሰዓት የዳታ ማዕከል ግንባታው እና የኔትወርክ ዝርጋታው በጥሩ ፍጥነት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የ EASE ፕሮጀክት ድጋፍ ኮሌጁን ወደ ዲጂታል ማዕከልነት ለመቀየር እና ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።በመሆኑም ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ፈጣን እና አስተማማኝ የቴክኖሎጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
