1 149
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 149
ሰኞ:- የካቲት 9 ቀን 2018 ዓ.ም
130ኛው የአደዋ ድል በዓል መታሰቢያ በፓናል ውይይት ተዘከረ!!
የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ፋና እና የኢትዮጵያውያን የጀግንነት ኩራት ተምሳሌት የሆነው 130ኛው የአደዋ ድል በዓል ‹‹የአደዋ አደራ አንድነት፣ ሉዓላዊነትና ማንሰራራት›› በሚል መሪ ቃል ዝክረ አደዋ ፓናል ውይይት ተካሄደ።
ይህንኑ ታላቅ በዓል ምክንያት በማድረግ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሚገኙ ተቋማት የድሉን ታሪካዊ ፋይዳና ወቅታዊ አደራ የሚመረምር ሰፊ የፓናል ውይይት አድርገዋል። መድረኩ የድሉን መንፈስ ወደ ስራና ውጤታማነት ለመቀየር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህ ደማቅ የውይይት መድረክ ላይ ከ6 ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተውጣጡ ከ1600 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። በውይይቱ ላይ ከጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ ከኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ፣ ከደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ፣ ከአራዳ ማኑፋክቸሪንግ እና ከየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተገኙ ዲኖች፣ አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ዝርዝር ሰነድ የቀረበ ሲሆን የቀደምት አባቶቻችንና እናቶቻችን የጀግንነት ታሪክ በስፋት ተዳስሷል። ወራሪውን የቅኝ ገዢ ኃይል ድል ለማድረግ አርበኞች በአጥንታቸው፣ በደማቸውና በስጋቸው የከፈሉት ዋጋ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች የነፃነት አዋጅ መሆኑ ተመልክቷል። ይህም ታሪክ ለትውልድ የማይጠፋ የኩራት ምንጭ መሆኑ ተነግሯል።
ተሳታፊዎቹ በቀረበው ሰነድ ላይ ባደረጉት ሰፊ ውይይት በአባቶቻችን የጀግንነት ታሪክ መኩራት ብቻ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ የራስን ደማቅ አሻራ የመስራት ታሪካዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ለዚህ ስኬት ደግሞ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሙያ መስክ ታሪክ የሚዘክረው አሻራ ሊያሳርፍ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል። በተለይም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሙያዎች በቴክኖሎጂ ሽግግርና በምርታማነት ረገድ የሚያሳዩት ጥረት የሀገርን ሉዓላዊነት በኢኮኖሚ ለማረጋገጥና ማንሰራራትን እውን ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት በመድረኩ ተገልጿል።
ውይይቱ የአደዋ ድልን ከመዘከር ባለፈ፣ የአሁኑ ትውልድ በሙያውና በክህሎቱ የሀገርን ክብር ለማስጠበቅ ቁርጠኛ መሆን እንዳለበት ተገልጿል። ተሳታፊዎቹም የተጣለባቸውን "የአደዋ አደራ" ለመወጣትና ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት ሚናቸውን እንዲወጡ ተገልፆ የዕለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
1 149
በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ለማሻሻል ስኬታማ ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።
*
የካቲት 07-2018ዓ.ም
የጉለሌ ክ/ከተማ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር የመንግስት ማቺንግ ፈንድ ድጋፍ ለማድረግ የመጀመሪያ ዙር የንግድ ክህሎት እና የንግድ እቅድ ዝግጅት ለልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች ለ5 ተከታታይ ቀን ስልጠና መሠጠቱ ተገለፀ። የምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ለማሻሻል ስኬታማ ሥራ በመሥራት ከተረጅነት ወደ አምራችነት እንደሚሸጋገሩ የቁጠባ እና የስራ ባህላችሁን ይበልጥ ለማሳደግ የመንግስት ማቺንግን ፈንድን በመጠቀም በፈለጉት የሥራ ዘርፍ እንደሚሰማሩ ውስጣዊ ተነሳሽነተና ቁርጠኝነት ይኖራችሁ ዘንድ መንግስት አስፈላጊውን እገዛ የሚያደርግ መሆኑን ተገልጿል።
በመጀመሪያ ዙር በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ ከ650 በላይ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ ሠልጣኞች በ20 የሥልጠና ክፍሎች ሥልጠናውን መከታተላቸውን የተገኘው መረጃው ያመላክታል ኮምንኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ15 ቀን የሚቆይ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ።
🇪🇹የካቲት 06/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለኮሌጁ ማህበረሰቡ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መስጠት ጀመረ።የኮሌጅ በመስማትና በመናገር ችግር ያለባቸውን ሰልጣኞች በብቃት ማገልገል የሚያስችል ለ15 ቀናት የሚቆይ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ።
ይህ ስልጠና በዋናነት ለኮሌጁ የአካዳሚክ አሰልጣኞች እና ለአስተዳደር ሰራተኞች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ አላማውም በግቢው ውስጥ የሚገኙ መስማትና መናገር የማይችሉ ሰልጣኞች ከማህበረሰቡ ጋር ያለምንም እንቅፋት እንዲግባቡና የሚገባቸውን አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል ነው።
አካታች የስራ አካባቢን በመፍጠር፣ የአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞችን ተጠቃሚነት ስልጠናው ሰራተኞች ከመስማት የተሳናቸው ሰልጣኞች ጋር በቀጥታ እንዲግባቡ መንገድ የሚከፍት በመሆኑ፣ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ፍትሃዊ እና ጥራት ያላቸው እንዲሆኑ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በእኩልነት ለማስተናገድና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚከተለውን ስትራቴጂካዊ ግብ የሚያሳይ እንደሆነ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
ለኮሌጁ ውድ የተከበራቹ ሰራተኞች በሙሉ
(ሴፍትኔት ስልጠና ላይ ከተመደባችሁ በስተቀር)
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
⭐️ የአድዋ የድል በዓል ምክንት በማድረግ የኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኞች በቀጥታ ለምትሄዱ በዊንጌት ክላስተር ሰኞ በ09/06/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እንድትገኙ እያሳሰብን ከተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ ለምትነሱ ጠዋት ከ1:30 -2:00 ሰዓት ብቻ መኪና የተመቻቸ መሆኑ አናሳውቃለን፡፡
መልካም ቀን !!!!
1 149
አስቸኳይ ማስታወቂያ
ለኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኞች
የፊታችን ሰኞ የካቲት 09 /2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰአት ጀምሮ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የውይይት መድረክ የተዘጋጀ በመሆኑ የኮሌጁ ሠራተኞች በሰዓቱ እንድትገኙ በጥብቅ እያሳሰብን።
በማይገኙ አካላት ላይ ኮሌጁ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ15 ቀን የሚቆይ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ።
🇪🇹የካቲት 06/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለኮሌጁ ማህበረሰቡ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መስጠት ጀመረ።የኮሌጅ በመስማትና በመናገር ችግር ያለባቸውን ሰልጣኞች በብቃት ማገልገል የሚያስችል ለ15 ቀናት የሚቆይ የምልክት ቋንቋ ስልጠና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ።
ይህ ስልጠና በዋናነት ለኮሌጁ የአካዳሚክ አሰልጣኞች እና ለአስተዳደር ሰራተኞች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ አላማውም በግቢው ውስጥ የሚገኙ መስማትና መናገር የማይችሉ ሰልጣኞች ከማህበረሰቡ ጋር ያለምንም እንቅፋት እንዲግባቡና የሚገባቸውን አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል ነው።
አካታች የስራ አካባቢን በመፍጠር፣ የአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞችን ተጠቃሚነት ስልጠናው ሰራተኞች ከመስማት የተሳናቸው ሰልጣኞች ጋር በቀጥታ እንዲግባቡ መንገድ የሚከፍት በመሆኑ፣ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ፍትሃዊ እና ጥራት ያላቸው እንዲሆኑ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ይህ ተነሳሽነት ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በእኩልነት ለማስተናገድና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚከተለውን ስትራቴጂካዊ ግብ የሚያሳይ እንደሆነ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አደረገ ።
🇪🇹የካቲት 04/2018 ዓ.ም🇪🇹
የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአሰራር ጥራትን ለማሳደግና ተቋማዊ አቅምን ለማጎልበት ያለመ የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም በአዲስ አበባው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካሄደ። በጉብኝቱ ላይ የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምክትል ዲሬክተሮች፣ የISO ታስክ ፎርስ አባላትና የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ልዑኩ በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በነበረው ቆይታ በሶስት ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ጥልቅ ገለጻና የመስክ ምልከታ አድርጓል ።
ኮሌጁ የትምህርት ተቋማት የአመራር ስርዓት ISO 21001:2018 አተገባበር ስታንዳርድን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ያለውን ስኬትና የሰነድ አያያዝ ተሞክሮ አጋርቷል። ይህም የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የራሱን የጥራት ማረጋገጫ ስርዓት ለመዘርጋት ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ተገልጿል።የስልጠና ክፍሎችን፣ ወርክሾፖችንና የተቋሙን ግቢ ለስራ አመቺ በሆነ መልኩ በዞን የመለየትና የማደራጀት ስራ ውጤታማነት ተጎብኝቷል። ይህ አሰራር ለሃብት አጠቃቀምና ለደህንነት ያለውን ጠቀሜታ ልዑኩ ተረድቷል።የEASE ፕሮጀክትን ውጤታማ በሆነ መንገድ የመምራት፣ የፋይናንስ አጠቃቀምና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር የማጠናከር ተሞክሮዎች ቀርበዋል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች እንደገለፁት እንዲህ ያሉ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የሚደረጉ የልምድ ልውውጦች ለዘርፉ እድገት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቁመው፣ የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ላሳየው የመማር ፍላጎት ምስጋና አቅርበዋል።
የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተወካዮች በበኩላቸው፣ በተፈሪ መኮንን ኮሌጅ ያዩዋቸው ዘመናዊ አሰራሮች በተለይም በISO ስታንዳርድ ዙሪያ ያገኙት ግንዛቤ ተቋማቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል።በተጨማሪም ጉብኝቱ በሁለቱ ታሪካዊ ኮሌጆች መካከል ያለውን ግንኙነት ከማጠናከሩ ባለፈ፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትን በጋራ ለማሳደግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ትልቅ እገዛ አለው ተብሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጉ/ክ/ከ ለተወጣጡ 2500 የሴፍትኒት ተጠቃሚዎች የንግድ ስራ ክህሎት እና የንግድ ሥራ እቅድ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ ።
🇪🇹የካቲት 04/2018 ዓ.ም🇪🇹
ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ለተወጣጡ 2500 የሴፍትኒት ተጠቃሚዎች በ3 ዙር የንግድ ስራ ክህሎት እና የንግድ ሥራ እቅድ ስልጠና በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ መሰጠት ተጀመረ ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአጫጭር ሥልጠና አስተባባሪ አቶ ታደሠ አበራ ለሰልጣኞች እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ በቆይታቸው ወቅት ማድረግ ስለሚገባቸው መብትና ግዴታ በዝርዝር ያብራሩ ሲሆን በተቻለ መጠን ሁሉም ሰልጣኝ በተመደበበት ክፍል በመገኘት ለተከታታይ አምስት ቀናት በመከታተል የስልጠናውን አላማ ግቡን እንዲመታ እና ሰልጣኞችም በቂ እውቀት አግኝታችሁ የቀጣይ የሂወት ውጣ ውረድን አሸንፋችሁ በስኬት ጎዳና እንድትጓዙ እንፈልጋለን ብለዋል። አያይዘውም ኮሌጁ የ100 ዓመት የካበተ ልምድና ISO 21001:2018 እውቅና ያገኘ በመሆኑ ብቃት ያላቸው አሰልጣኞችን በመመደብ በቅርብ ሆነን ክትትልና ድጋፍ የማድረግ ስራ እንደሚሠራ ገልፀው የሚያጋጥሙ ክፍተቶች ካሉም ፈጣን የሆነ የማስተካከያ መፍትሔ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ።በመጨረሻም ስልጠናው በአግባቡ ላጠናቀቁ ሠልጣኞች ሠርትፍኬት የሚሠጥ መሆኑን አሳውቀዋል ።በቀጣይም የተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በልዩ ልዪ መስኮች የአጫጭር ስልጠናዎችን ለዜጎች ለመስጠት በሙሉ አቅም እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካሄደ ።
🇪🇹የካቲት 04/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን የክህሎት ውድድር መነሻ በማድረግ፣ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ብቃት ለመመዘን ያስቻለ የውስጥ ውድድር አካሄደ።በእለቱም በሁሉም የውድድር ዘርፎች በመገኘት ለተወዳዳሪዎችን ግንዛቤ በኮሌጁ አመራሮች ተፈጥሮላቸዋል ።
ኮሌጁ ውድድሩን ያካሄደው በሰባት ቁልፍ የሙያ ዘርፎች ላይ ሲሆን፣ ሰልጣኞች በክህሎታቸው የታጀቡ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል። በውድድሩ ጄኔራል ሜታል ፋብሪኬሽን (GMF)፣ቴክስታይል እና ጋርመንት፣አውቶሞቲቭ፣ሆቴልና ቱሪዝም፣ቢውልዲንግ ኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽን፣ኮንስትራክሽን፣አይሲቲ (ICT) የተካተቱት ዘርፎችም ናቸው።
የውድድሩ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ እንዲህ ያሉ መድረኮች ሰልጣኞች ለሀገር አቀፍ ውድድር እንዲዘጋጁ ከማድረጋቸው ባለፈ፣ የኮሌጁን የማሰልጠን አቅም በተግባር የሚመዝኑ ናቸው። በውድድሩም የላቀ ብቃት ያሳዩ ሰልጣኞች ኮሌጁን ወክለው በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር እንደሚዘጋጁ ታውቋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
