uk
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Закритий канал

Показати більше
1 146
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
please share it

እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዚህ አመት የሚያከብረውን 100ኛ አመት ምክንያት በማድረግ የ 100ብር card giveaway አዘጋጅቷል የዚህ giveaway ተሸላሚ ለመሆን 1ኛ ፡- https://www.facebook.com/profile.php?id=100063988867313 Follow እና like ማድረግ 2ኛ ፡- https://www.youtube.com/@EntotoTMS Subscribe ማድረግ እና ካሉት videoች እንዱ ላይ Entoto ptc ብሎ comment ማድረግ 3ኛ፡- https://www.tiktok.com/search?q=%40entototms&t=1728148991360 Follow ማድረግ እና ካሉት videoች እንዱ ላይ Entoto ptc ብሎ comment ማድረግ 4ኛ፡- ይህንን መልዕክት ለ 30 ሰው share ማድረግ ይሄን ካደረጉ በኋላ @Yemir1 contact ያድርጉን

ሰላም እንዴት ናችሁ ሰሞኑን የኢንተርኔት መቆራረጥ እንደነበረ ይታወቃል በመሆኑም ዛሬ ከኢትዮ ቴለኮም ባገኘነው መረጃ መሰረት ከመነን እስከ ሽሮሜዳ ድረስ በኮሪደሩ ልማት ምክንያት መስመር እየተቀየረ በመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ  የኢንተርኔት መቆራረጥ እንደሚኖር ለማሳወቅ እንወዳለን ::

ዕለተ ሰኞ መስከረም 13/2017ዓ.ም በISO የትግበራ ሂደት ተጨማሪ ማብራሪያ ተሰጠ። በስላጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ስር የሚገኙ ክፍሎች እና የስልጠና ዘርፎች የISO የትግበራ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ
+4
ዕለተ ሰኞ መስከረም 13/2017ዓ.ም በISO የትግበራ ሂደት ተጨማሪ ማብራሪያ ተሰጠ። በስላጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ስር የሚገኙ ክፍሎች እና የስልጠና ዘርፎች የISO የትግበራ  አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በአስተባባሪዎች የተፈተሸ ሲሆን ከእይታው በተገኝ ግብረ መልስ  ተናቦ አለመስራት፣ በISO ደረጃቸውን ጠብቀው በተላኩ ፎርማቶች አለመጠቀም ፣ስልጠናውን የወሰዱ ተወካዮች በአግባቡ ድጋፍና ክትትል አለማድረግ የታዩ ክፍተቶች ሲሆኑ እነኝህን ለማስተካከል  ያስችል ዘንድ የጋራ መድረኩ ተመቻችቷል። በመድረኩ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ቅኝቱ ከተወሰኑ ስልጠና ዘርፎች ውጪ የISO ትግበራውን በውል ያለመረዳት ክፍተትን የሚያመላክት በመሆኑ በቀጣይ ባሉት ግዚያት ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ስልጠና ዘርፎችን በማቀናጀት የመደጋገፍ ባህልን ማጎልበት እና በእኔነት መንፈስ ትግበራው መሰራት እንዳለበት ገልፀው ይህ እውን እንዲሆን  ስልጠናውን የወሰዱ የታስክ ፎርስ አባላት አመራሩን ጨምሮ ወደስራ በመግባት በአጭር ግዜ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አሳስበዋል። በተመሳሳይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን ከመድረክ እና ከተሳታፊዎች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶበት በጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።                       ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ መስከረም 10/2017ዓ.ም የብልሹ አሰራር ተጋላጭነት ደረጃን በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ቀረበ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጥናትና ምርምር ቡድን ከስነ-ምግባር
+2
ዕለተ ዓርብ መስከረም 10/2017ዓ.ም የብልሹ አሰራር ተጋላጭነት ደረጃን በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ቀረበ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጥናትና ምርምር ቡድን ከስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር የአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የስራ ክፍሎች የብልሹ አሠራር ተጋላጭነትን ደረጃ በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ቀረበ። ጥናቱን ያቀረቡት ወ/ሪት ቤተልሄም የጥናቱን አስፈላጊነት ፣የጥናቱን ስልት ፣የጥናቱን ይዘት፣ ዓላማ ፣የጥናቱን ግኝቶች ፣ማጠቃለያና ምክረ ሃሳቦችን በሰፊው በማብራራት የተለያዩ ክፍሎች ያሉበትን ደረጃ አመላክተዋል ። አክለውም ጥናቱ ያመላከታቸውን ምክረሃሳቦች ሰንዝረዋል ። በመቀጠልም  ከቤቱ ቢታዩ፣ ቢታከሉ ያሏቸውን ሃሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ ተጠናቋል ።              ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ መስከረም 10/2017ዓ.ም ከተቋሙ የሪፎርም ስራዎች አንዱ ተገመገመ። የቀድሞ ተፈፈሪ መኮንን ት/ቤትየአሁኑ እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘመናት ጉዞው አንቱታን ያተረፉ ባለሙያዎችን ያፈራ
+8
ዕለተ ዓርብ መስከረም 10/2017ዓ.ም ከተቋሙ የሪፎርም ስራዎች አንዱ ተገመገመ። የቀድሞ ተፈፈሪ መኮንን ት/ቤትየአሁኑ እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዘመናት ጉዞው አንቱታን ያተረፉ ባለሙያዎችን ያፈራና በተያዘው በጀት ዓመት 100ኛ ዓመቱን የሚያከብር አንጋፋ ኮሌጅ ነው። ሆኖም ግን የኮሌጁ ምድረ ግቢ ኮሌጁን የሚመጥን አለመሆኑ በተለያዩ ግዚያት በተለያዩ አካላት እየተጠቆመን መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ይህንን አንጋፋ ኮሌጅ በደረጃው ለማስቀመጥ ከሚከናወኑት ተግባራት መካከል ምድረ-ግቢውን ውብና ማራኪ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ሙያዊ በሆነ መልኩ የታገዘ ስራን ለመስራት በECO-SOLV ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበ ከዋናው መግቢያ እስከ ቸርች ህንጻ ድረስ ያለው ላንድስኬፕ ዲዛይን  ከአካባቢው የአየር ንብረት አንጻር የተቃኘ ፕሮጀክት ዲዛይን ቀርቦ ለኮሌጁ የበላይ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት ፣ለአካዳሚክ ኮሚሽንና የሚመለከታቸው አካላት ቀርቦ ግምገማ ተካሂዶበታል። ፕሮጀክቱን ያቀረቡት እና ለቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ የሰጡት የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ቤተልሄም ገ/መድህን፣ሳሬም ጉልላትና ስምረት አረጋይ ከቤቱ ለተነሳላቸው ጥያቄና አስተያየት ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተውበታል። በተጨማሪም ከውይይቱ ለፕሮጀክቱ ማጎልበቻ የሚሆኑ ሃሳቦችን እንዳገኙበትም ጠቁመዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዋናዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የዚህ ፕሮጀክት እውን መሆን ያለውን ፋይዳ ጠቁመው ይህንን ለማሳካት ሁሉም በየደረጃው የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።               ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content

የነባር ሰልጣኞች  የምዝገባ እና ወርሀዊ ክፍያ መጠን ለቀን ሰልጣኞች ሀ.ከደረጃ 1 እስከ 2 በ 25 ብር የ6 ወር=150 ብር ለ.ከደረጃ 3 እስከ 5 በ 35 ብር የ6 ወር=210 ብር ሐ.የመመዝገቢያ= 50 ብር ለማታና የweekend ሰልጠኞች ሀ.ደረጃ 1= 250*3 ወራት=750 ብር ለ.ደረጃ 2= 275*3=825 ብር ሐ.ደረጃ 3=300*3=900 ብር መ.ደረጃ 4=325*3=975 ብር ሠ.ደረጃ 5=350*3=1050 ብር ረ.የመመዝገቢያ=50 ብር ማሳሰቢያ:- #ከተጠቀሰው የንግድ ባንክ አካውንት ውጪ በቴሌ ብርም ሆነ ሌሎች ባንኮች መክፈል አይቻልም። ለተማሪዎቻችሁ (ለሰልጣኞቻችሁ) እንዲያውቁት አድርጉ 🙏🙏🙏

የ2017 የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ማስታወቂያ

photo content

ሠላም ስማችሁ ከዚህ በታች ያላችሁ የቴክኖሎጂ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቡድን እና አስተባባሪዎች ነገ አጭር ስብሰባ ስለሚኖረን ነገ 10/01/2017 ዓም ጠዋት 4፡00 ላይ በቴክኖሎጂ ትንሹ አዳራሽ እንድትገኙ በትህትና እነጠይቃለን፡፡

photo content

photo content
+6

ዕለተ ማክሰኞ መስከረም 7/2017ዓ.ም የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች  ከስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና የክፍል ሃላፊዎች የጋራ የውይይት መድረክ አካሄደ ። በውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የእንኳን አደረሰቻሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው  የበጀት ዓመቱን ስራ ተናቦ ለመስራት የጋራ መድረክ መፍጠሩ ያለውን አስፈላጊነት፣እንዲሁም ወሳኝየሆኑ ርእሰ ጉዳዮችን እያዋዙና በሽልማት  እያበረታቱ አስጀምረውታል ። በውይይቱ  ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል  የTVET ስልጠና የትኩረት አቅጣጫ /ዓላማና ግቦች በ4 መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን እነሱም :- 1. ስልጠናን ተደራሽ ማድረግ 2. ስልጠናን ፍትሃዊ ማድረግ 3. የስልጠና አግባብነትን ማረጋገጥ 4. ጥራትን መሠረት ያደረገ /ገበያው የሚፈልገውን       ስልጠና ማቅረብ ሲሆን ይህን እውን ለማድረግ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ በመከፋፈል በየወሩ የሚከናወኑ ተግባራትን ማቀድና አፈጻጸሙንም  ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል። ስልጠና ዘርፎችም ሆኑ ክፍሎች ስራዎቻቸውን በ11ዱ ተግባራት የተቃኘ እንዲሆን እንዲሁም የክህሎት ልማት እሳቤዎች/DNA/ን ታሳቢ ያደረጉ ስራዎችን ተናቦ መስራት  እንደሚገባ  በጋራ መግባባት ተደርሶባቸዋል። የበጀት ዓመቱ የቅበላ መጠን 2039 ሲሆን ይህንን ለማሳካት የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች የተጀመሩ መሆናቸውም ተጠቁሟል። በተጨማሪ በተለያዩ ስልጠና ዘርፎች  ኮሌጁ ካለው  አቅም አንጻር የሌሎች የተሻሉ የተባሉ ከሐገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ምን እንደሚመስሉ በጥናቱ ተቃኝቷል።  ከነኝህም መካከል በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ የተጠናው ጥናት እንደማሳያ ቀርቧል። ኮሌጁ ባለው አቅም እና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እውን ቢያደርገው ከበዘርፉ የሚገኙ ጠቀሜታዎችን ጥናቱ አመላክቷል።  በመጨረሻም  ከቤቱ ሐሳብ አስተያየት ቀርቦ በወረዱ ዕቅዶች ላይ ከስልጠና ዘርፎች እና ክፍሎች ጋር የጋራ የስምምነት ሰነድ ፊርማ ተከናውኖ የፕሮግራሙ ማጠቃለያ ሆኗል ።                 ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ማክሰኞ መስከረም 07/2017ዓ.ም በጉለሌ ክ/ከተማ የኮሪደር ልማት እና የዘላቂ ማረፊያ ስፍራ ባለሙያዎች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሠጠ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውበትና ከተማ ል
+4
ዕለተ ማክሰኞ መስከረም 07/2017ዓ.ም በጉለሌ ክ/ከተማ የኮሪደር ልማት እና የዘላቂ ማረፊያ ስፍራ ባለሙያዎች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሠጠ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውበትና ከተማ ልማት ቢሮ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  የኮሪደር ልማት እና የዘላቂ ማረፊያ ስፍራ ባለሙያዎችን አቅም ለማጎልበት በተዘጋጀው ስልጠና ከ33 ማህበራት  325 አባላት ስልጠናውን መውሰድ እንደሚጠበቅባቸውና ይህም በጠንካራ ዲሲፕሊን የሚመራ መሆኑን የጠቆሙት በአስተዳደሩ ውበትና ከተማ ልማት ቢሮ አቶ ታደለ አለሙ ናቸው። በተመሳሳይ  ኦረንቴሽኑን የሰጡት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ስልጠናው ለ5 ቀናት የሚቆይ መሆኑንም ገልጸዋል። ሰልጣኞች በስልጠና ወቅት ማድረግ የሚገባቸው እና የሌለባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል ። አክለውም ምንም እንኳን የስልጠናው ቆይታ 5 ቀን ቢሆንም  በኮሌጁ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ  ማህበራቱ ከሚፈልጉት ድጋፍ አንጻር በጥናት ላይ ተመስርቶ የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚደረግላቸው በመጠቆም መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል።                 ኮሙኒኬሽን ቡድን   

photo content

photo content