1 149
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 149
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጸሙን ገመገመ ።
🇪🇹30/07/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር በጋራ ገመገመ። ተቋሙ በ2022 በሀገር አቀፍ ደረጃ ተመራጭና ተወዳዳሪ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመሆን የያዘውን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችሉ አበይት ተግባራት መከናወናቸው በግምገማው ወቅት ተገልጿል።
ኮሌጁ በበጀት ዓመቱ ትኩረት አድርጎባቸው በነበሩት ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ የትኩረት መስኮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።ውጤት ተኮር ስልጠና ስርአት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን፣ ብቁ፣ ተወዳዳሪ እና ስራ ፈጣሪ ሙያተኛን ለማፍራት በተከናወኑ ተግባራት አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸው ተመላክቷል። ይህ የሥልጠና እና የቴክኖሎጂ ልማት ዕቅድ በስድስት ስትራቴጂካዊ ግቦች ስር የተካተቱ 96 ዝርዝር ተግባራትን ይዞ ወደ ትግበራ መገባቱ ተጠቁሟል።
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአራቱም የድጋፍ ማዕቀፎች ኢንተርፕራይዞችን በመደገፍ ምርትና ምርታማነታቸውን ማሻሻልና ውጤታማነታቸውን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች መከናወናቸው በሪፖርቱ ቀርቧል።
በግምገማ መድረኩ ላይ ከኮሌጁ ማህበረሰብ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሚመለከተው የሥራ ኃላፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተመዘገቡ አመርቂ ተግባራትን በማስቀጠል በቀጣይ ይበልጥ ትኩረት የሚሹ ስራዎች ላይ ተቋማዊ ርብርብ ለማድረግ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።በመጨረሻም፣ ኮሌጁ የያዘውን ሀገራዊ ራዕይ ለማሳካት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ በመቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዲጂታላይዜሽን እና በ"ግሪን ቲቬት" ራሱን እያዘመነ መሆኑ ተገለጸ ።
🇪🇹29/07/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና የአካባቢ ጥበቃን መሰረት ያደረጉ የሪፎርም ስራዎችን በመተግበር አገልግሎቱን በዘመናዊ መልኩ እያቀለጠፈ መሆኑን አስታወቀ።
ኮሌጁ በተለይም በዲጂታላይዜሽን እና በ"ግሪን ቲቬት" (Green TVET) ዘርፍ እያከናወናቸው ያሉትን አበይት ተግባራት ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ለተውጣጡ የሱፐርቪዥን ቡድኖች በዝርዝር አቅርቧል።
የዲጂታላይዜሽን ስራዎች እና የቴክኖሎጂ መሰረተ-ልማት በተመለከተ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት በመታገዝ በግቢው ውስጥ የሚገኙ ህንፃዎችን በኔትወርክ የመተሳሰር ስራ (Network Infrastructure) በማጠናቀቅ የዲጂታል አገልግሎት መሰረቱን አጠናክሯል።
ይህንን ተከትሎም በኮሌጁ አሰልጣኞች በራስ አቅም የበለፀገ አዲስ ዌብሳይት ስራ ላይ መዋሉን ገልጸዋል። ይህ ዌብሳይት ኮሌጁን ለዓለም ከማስተዋወቅ ባለፈ ደንበኞች ባሉበት ሆነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ አክሰስ መፍጠሩን ፣ የተገነባው ሶፍትዌር ከሌሎች ውጫዊ ተቋማት ጋር በቀላሉ ሊተሳሰር በሚችል መልኩ መጠናቀቁንና በቀጣይም ሁሉንም የኮሌጁን የስራ ክፍሎች ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
ኮሌጁ ከአረንጓዴ ልማትና ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጋር የተያያዙ ተግባራትን በስፋት እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል ከGIZ ጋር በመተባበር በIT ዘርፍ "Networking with Prime Content" በሚል ርዕስ የካሪኩለም እና የሞጁል ልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
የአካባቢ ጥበቃ እና ፈጠራ በግቢው ውስጥ የችግኝ ተከላ ስራዎች ከመከናወናቸውም ባሻገር፣ ሰልጣኞች ከወዳደቁ ዕቃዎች ዳግም ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የፈጠራ ስራዎችን ለጉብኝት አቅርበዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
Repost from N/a
16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በደመቀ ስፖርታዊ ውድድር ተከፈተ።
🇪🇹አዲስ አበባ | መጋቢት 29/2018 ዓ.ም🇪🇹
"የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት፣ ስፖርታዊ ውድድር ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ይህ ስፖርታዊ ውድድር ማስጀመሪያ፣ በመክፈቻው ዕለት ከ5000 በላይ ስፖርተኞች የሚሳተፉበት ታላቅ ስፖርታዊ ውድድር አስተናግዷል።
በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚደክሳ ከበደ፤ ሀገራችን ያስመዘገበችውን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል ልማታዊ አስተሳሰብ ያለውና በክህሎት የዳበረ አምራች ዜጋ መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስልታዊ አካሄዶችን እየተገበረ መሆኑንም አክለዋል።
እንደ አቶ ሚደክሳ ማብራሪያ፤ ይህ ዓመታዊ አውደ-ርዕይ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በአሰልጣኞችና ሰልጣኞች የተሰሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች፣ የውጭ ምርትን የሚተኩ የኢንተርፕራይዞች ውጤቶች እንዲሁም የፈጠራ ስራዎች የሚቀርቡበት ታላቅ መድረክ ነው። ከቴክኖሎጂ፣ ከክህሎትና ከፋሽን ዲዛይን ውድድሮች በተጨማሪ በዛሬው ዕለት የተጀመረው ስፖርታዊ ውድድር በኮሌጆች መካከል ያለውን ትውውቅ ለማጠናከርና "ብቁና ንቁ የፐብሊክ ሰርቫንት" ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስግደው ኃይለጊዮርጊስ በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ከግብ ለማድረስ የቴክኖሎጂ አቅም መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው" ብለዋል። የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የዚህ ጉዞ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን የጠቀሱት ኃላፊው፤ የቴክኖሎጂ ልህቀት ያለ አካላዊና አእምሯዊ ጤንነት ሙሉ ሊሆን ስለማይችል ስፖርት ለዚህ ዘርፈ ብዙ ስኬት አይነተኛ መፍትሄ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ይህ ስፖርታዊ ውድድር በ15 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መካከል የሚካሄድ ሲሆን፣ ለሚቀጥሉት 15 ቀናት በእግር ኳስ፣ በአትሌቲክስ፣ በገመድ ጉተታና በቮሊ ቦል ዘርፎች ውድድሮች ይካሄዳሉ። ይህም ተቋማዊ ትብብር ለወጣቶች ሁለንተናዊ ዕድገት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሁለቱም ቢሮዎች ማኔጅመንት አባላት፣ የሁሉም ኮሌጆች አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም የስፖርት ቤተሰቦች ተወዳዳሪዎች በነቂስ ተገኝተዋል።<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
👉ለነፃ የስልክ ጥሪ
6524
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዕውቀት አስተዳደር የተከለሰ ዕቅድና የ“ወርቃማው ሰኞ” መርሃ ግብር ላይ ውይይት ተካሄደ ።
🇪🇹28/07/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዕውቀት አስተዳደር ቡድን (Knowledge Management Team) የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወር የተከለሰ ዕቅዱን በማቅረብ ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ውይይት አከናወነ። በመድረኩም ተቋማዊ ትውስታን ለማጠናከርና የባለሙያዎችን ክህሎት ለሌሎች ለማጋራት ታስቦ የተቀረጸው የ“ወርቃማው ሰኞ” የዕውቀትና የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር በዝርዝር ቀርቧል።
የዕውቀት አስተዳደር ቡድኑ ባቀረበው ሪፖርት፣ ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በቀሪው የበጀት ዓመት ትኩረት የሚሹ ዓበይት ስራዎችን አካቷል። በተለይም በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ዕውቀቶችን፣ የፈጠራ ስራዎችንና የአሰራር ጥበቦችን በስልታዊ መንገድ ለመያዝ፣ ለማደራጀትና ለቀጣዩ ትውልድ ለማጋራት የሚያስችሉ ስልቶች ላይ አፅኖት ተደርጓል።
የ“ወርቃማው ሰኞ” የልምድ ልውውጥ መድረክ በዕቅዱ ውስጥ በልዩ ትኩረት የቀረበው የ“ወርቃማው ሰኞ” (Golden Monday) መርሃ ግብር ሲሆን ተግባራዊ ልምድን ማጋራት፣ አንጋፋና ከፍተኛ ልምድ ያላቸው የኮሌጁ መምህራንና ሰራተኞች ያከማቹትን ተግባራዊ ጥበብ ለወጣት ባለሙያዎች የሚያስተላልፉበት መድረክ በመፍጠር በስራ ሂደት ውስጥ የሚገኙ ውጤታማ አሰራሮችን በሰነድና በምስል በመቅረጽ ለተቋሙ ቀጣይ እድገት እንደ ግብዓት መጠቀም እና በየሳምንቱ ሰኞ በሚከናወኑ የውይይት መድረኮች አማካኝነት በሰራተኞች መካከል ጠንካራ የግንኙነትና የጋራ ዕውቀት ማበልጸጊያ ስርአት መዘርጋት ናቸው ።
በቀረበው የተከለሰ ዕቅድና በ“ወርቃማው ሰኞ” መርሃ ግብር ላይ የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችንም ሰንዝረዋል። ተሳታፊዎቹ እንደገለጹት፤ እንዲህ ያሉ መድረኮች አንዱ ካለው ጥንካሬ ሌላው እንዲማር ከመነሳሳቱም በላይ፣ በተቋሙ ውስጥ የሚጠፋ ወይም የሚረሳ ዕውቀት እንዳይኖር (Knowledge Loss) ትልቅ ሚና ይጫወታሉ።
በመጨረሻም፣ የዕውቀት አስተዳደር ቡድኑ ከውይይቱ የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት ዕቅዱን ይበልጥ በማበልጸግ ወደ ሙሉ ትግበራ እንደሚገባ አስታውቋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ
ማንኛውንም የኤጀንሲው መረጃ ማህበራዊ ሚዲያ ድረ-ገፅ ከታች የተቀመጠላችሁ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
ታማኝ፣ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት የኤጀንሲውን ማህበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇👇👇
ፌስቡክ :https://www.facebook.com/61575251932855/posts/122094478412841731/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v
ቴሌግራም:https://t.me/feedingagency8
ቲክቶክ:http://tiktok.com/@feeding.agency
ዩቲዩብ:https://youtube.com/@addisababacityadminstrationfa?si=QyoZiayxIloRxa5j
ኢንስታግራም:https://www.instagram.com/reel/DIXXS2EoUTA/?igsh=NTc4MTIwNjQ2YQ==
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስልጠናና አካዳሚክ ፕሮሰስ ካውንስል የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ
አካሄደ ።
🇪🇹መጋቢት 23/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስልጠናና አካዳሚክ ፕሮሰስ ካውንስል የዘጠኝ ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ገመገመ። በግምገማው ላይ በካውንስሉ ስር የሚገኙ የስልጠና ዘርፎች፣ የጥናትና ምርምር፣ የሬጅስትራር፣ የስራ ትስስር እና የሲኦሲ ዘርፎሎች ያከናወኗቸው ተግባራት ቀርበዋል።
የኮሌጁ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት ሪፖርቱ በዋናነት ሊመለከታቸው የሚገቡ ነጥቦችን አንስተዋል። ከነዚህም መካከል የ2017 ዓ.ም ሰልጣኞች የምዘና አፈጻጸም እና የስራ ቅጥር ሁኔታ ፣ የ2018 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞች ስልጠና የሚጠናቀቅበት ጊዜ ፣ የትብብር ስልጠና ያለበት ደረጃ ፣ የተቋሙ የውስጥ ምዘና እና ሀገር አቀፍ የምዘና ዝግጅት ላይ ያተኮረ እንዲሆን አስቀምጠዋል ። አክለውም ኮሌጁ እስከ 2030/32 የያዘውን የዲጂታላይዜሽን እቅድ መነሻ በማድረግ እያንዳንዱ ዘርፍ ስራውን ወደ ዲጂታል አሰራር ከመቀየር አንጻር የሰሩትን ስራ በዝርዝር እንዲያሳዩ አሳስበው የሰልጣኞች ዲሲፕሊን በተመለከተ ማብራሪያ እንዲቀርብበት አመላክተዋል።
ሪፖርቱ በቀረበባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ በኋላ፣ የቀጣይ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚረዱ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። ምክትል ዲኑ የቀረበው ሪፖርት አበረታች መሆኑን ገልጸው ለቀጣይ ስኬት ብሌንድድ ለርኒንግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና መደበኛውን ስልጠና በማቀናጀት መስራት ፤ የእለት ቼክሊስት እያንዳንዱ የስራ እንቅስቃሴ በየእለቱ በቼክሊስት እየተመዘገበ ክትትል እንዲደረግበት ፣ ዝግጅት ማጠናቀቅ በቀሪው ጊዜ ውስጥ መሟላት ያለባቸው ግብአቶችና ስራዎች በአፋጣኝ እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ ተሰጥተዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
