1 145
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 145
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 28/2016ዐ.ም
የካይዘን አፈጻጸም ምልከታ ተካሄደ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የኮሌጆችን የካይዘን አፈጻጸም በገለልተኛ አካል ከካይዘን ልህቀት ማዕከል በመጡ ባለሙያዎች አስገምግሟል፡፡ ቡድኑ በናሙናነት በስድስት የሥልጠና ዘርፎች ላይ የካይዘን አደረጃጀትን፣ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ምልከታ አካሂዷል፡፡ በተመሳሳይም የሰነድ ምርመራና ከካይዘን ቡድን አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡
በአጠቃላይ በ2 ቀን ምልከታው የታዩ ጥንካሬዎችን እና መስተካከል አለባቸው ያሏቸውን ጉዳዮች የኮሌጁ የበላይ አመራር፣የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች እና የካይዘን ቡድን አባላት በተገኙበት የማጠቃለያ ውይይት መስተካከል አለበት ያሏቸውንም ጠቁመዋል፤ በቀረበው ግኝት ላይ የሚነሱ ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮች፣ማብራሪያ የሚሹ ሃሳቦች ካሉ እድሉን ለቤቱ ክፍት በማድረግ ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽ በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል፡፡
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ዕለተ ረቡዕ የካቲት 27/2016ዐ.ም
የአውቶ ሞቲቭ ሥልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ፡፡
የአውቶ ሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ በ2014ዓ.ም በአውቶ መካኒክስ በአዲሱ ካሪክለም ሲያሰለጥናቸው የቆዩ የደረጃ 3 ሠልጣኞች 28 ወንዶች እና 2 ሴት ሠልጣኞችን ለምዘና አስቀምጧል በተመሳሳይ በ2015ዓ.ም በአውቶ መካኒክስ እና በአውቶ ኤሌክትሪክ ያሠለጠናቸውን 50 የደረጃ 2 ሠልጣኞች በአጠቃላይ 80 ሠልጣኞች ከ1ወር የትብብር ስልጠና ቆይታ መልስ እና ከሁለት ሳምንታት የክለሳ ክፍለ ግዜ በኋላ በዕልት 19/06/2016 ተጀምሮ በዛሬው ዕለት የተጠናቀቀው ምዘና የንድፈሃሳብ እና የተግባር የምዘና ፓኬጅን የያዘ ሲሆን በምዘና ኮሚቴዎች ተዘጋጅቶ በስልጠና ዘርፍ ተጠሪና በአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ተረጋግጦና እውቅና አገኝቶ /ፀድቆ የቀረበ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በቀጣይ ባሉት ሁለት ቀናት መረጃው ተጠናቅሮ የሚቀርብ ሲሆን በምዘናው ብቁ የሆኑት ወደሚቀጥለው ደረጃ የሚሸጋገሩ ሲሆን በምዘናው ያልበቁ ሠልጣኞች በተጨማሪ ከ/ግዜ የማብቃት እና እንደገና የመመዘን ስራው እንደሚሰራ የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪው አቶ ደሳለኝ አዱኛ ጠቁመዋል፡፡
እንደ አስተባባሪው ገለጻ በአጠቃላይ በስልጠና ሂደቱም ሆነ በምዘናው ላይ አሠልጣኙ በተቀመጠለት የግዜ ሰሌዳ መሰረት ያለምንም መሸራረፍ በቁርጠኝንት እየሰራ በመሆኑ ለስልጠና ዘርፉ አሠልጣኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ አክለውም ትኩረት ቢሰጠውና ቢስተካከል ያሉትንም ጠቁመዋል፤በስልጠና ዘርፉ ያሉ ማሽኖች እድሜ ጠገብ መሆናቸውን ገልጸው ከግዜው ጋር ሊሄዱ የሚችሉ አዳዲስ ማስተማሪያ ማሽኞችን፣ ሠልጣኞች አንቀሳቅሰው ሊሰለጥኑባቸው የሚችሉ ተሸከርካሪዎች ቢኖሩ ምሉዕ በኩሌሁ /የተሟላ ስልጠና መስጠት ይቻል ነበር ይላሉ፡፡ እኛም ይህን ሃሳብ በመጋራት ስልጠና ዘርፉ ያቀረበው የማቴሪያል ጥያቄ አቅም በፈቀደ መልኩ ቅድሚያ ተሰጥቶት የሚሟላበት ሁኔታ ቢመቻችላቸው እያልን ለተመዛኞች መልካም ውጤትን እንመኛለን፡፡
1 145
+3
ዕለተ ሰኞ የካቲት 25/2016ዓ.ም
ከየስራ ስራ ክፍሉ ለተወጣጡ ተወካዮች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት መፈፀሙ እና ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል፤ ይህንን እውን ለማድረግ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ ተወካዮች በኢትዬጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዮት አማካኝነት ለአምስት ቀናት የሚዘልቅ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
የስልጠናው ዓላማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋትና ቴክኒካል ድጋፍ በመሰጠት ለቴክኖሎጂ ሽግግር ምቹ ሁኔታ መፍጠር ነው።
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ አካዳሚክ ጉዳዬች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ ስልጠናው የISO ትግበራን እውን ለማድረግ ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው መልካም የስልጠና ግዜ በመመኘት ስልጠናውን በይፋ አስጀምረዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+4
ዕለተ ሐሙስ የካቲት 21/2016 ዓ.ም
ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ አራት ለተወጣጡ ከ3ሺህ በላይ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ለአምስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀመረ።
ስልጠናው የተግባቦት አቅምን በማሳደግ የሙያ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት እንዲሁም በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ትልቅ ሚና ያለውና ህልማቸውን ለማሳካት በር ከፋች የሆነ ስልጠና ነው።
የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጉለሌ ክ/ከተማ ጽ/ቤት ሀለፊ አቶ እንዳሻው ምንይችል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በሚወስዱት ስልጠና የሙያ ክህሎታቸውን አዳብረው ወደ ስራ በመግባት እራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን የሚጠቅሙ እንደሚሆኑ ባለሙሉ ተስፋ መሆናቸውን ገልፀዋል። አክለውም በስልጠናው ወቅት የግቢውን ህግና ደንብ ማክበር እንደሚገባ በማመላከት ስልጠናውን አስጀምረዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+3
ኤች.አይ.ቪ ኤድስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር ተካሄደ።
የኮሌጁ ፀረ ኤድስ ክበብ ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞች ኤች.አይ.ቪ ኤድስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር ያዘጋጀ ሲሆን በመርሀ-ግብሩ ላይ የተጋበዙት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ልዩ ትኩረት ለሚሹ ማህበረሰብ ባለሙያ የሆኑት አቶ ደሳለኝ ካርሾ
- የበሽታውን አመጣጥ፣
- የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት በሀገር ደረጃ ምን
ይመስላል?
- የበሽታውን ስርጭት ለመግታት በቤተሰብ ደረጃ ሊኖር ስለሚገባው ግልፀኝነት፣
- በበሽታው ለተያዙ ወገኖች ሊደረግ ስለሚገባው
እንክብካቤ እንዲሁም የመከላከልና የመቆጣጠር ስራን ለመስራት መከናወን ያለባቸው ተግባራትን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ በማድረግ መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+4
ዕለተ ማክሰኞ የካቲት 19/2016ዓ.ም
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ ተደረገ።
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በሀገር አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት መፈፀሙ እና ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል፤ ይህንን እውን ለማድረግ እንዲያስችል በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለISO ትግበራ ሂደት የተከናወኑ ተግባራትን ላይ የልምድ ልውውጥ ተካሂዷል።
በጉብኝቱ የተሳተፉት የኮሌጁ "ISO 21001:2018 Educational quality management system" የታስክ ፎርስ አባላት ሲሆኑ በISO ትግበራ እስከ ፍፃሜ የተከናወኑ ተግባራት፣ በትግበራ ሂደት ያጋጠሙ ተግዶሮቶችና የተወሰዱ የመፍትሄ ሀሳቦች እንዲሁም በማኔጅመንቱ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል። በተመሳሳይ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪ የሰጡት የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሌጅ የISO ታክስ ፎርስ አባላት ሲሆኑ ይህ ተግባር በዋነኝነት የሚከወነው በማኔጅመንቱ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት መሆኑን ገልፀዉ ከዚህም ባሻገር የኮሌጁን ማህበረሰብ በማሳተፍ ታሪካዊ ሀላፊነትን መወጣት እንደሚገባ አመላክተዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+4
ለኮሌጁ የማኔጅመንት አባላት ሶፍት እስኪልና ዲጅታላይዜሽን ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ስልጠናው የተጀመረበት ሳምንት በሀገራቀፍ ደረጃ የዲጅታላይዜሽን ሳምንት መሆኑን ገልፀው በኮሌጁ የምንሰጣቸውን አገልግሎቶች የተሳለጠና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያግዝ ሶፍትዌር ወደ ስራ የማስገባት ሂደት የተጠናቀቀ መሆኑንና ከዚህም ባሻገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን እውቀትን እንድናዳብር የሚያግዝ መሆኑን በማመላከት መልካም የስልጠና ግዜ ተመኝተዋል።
በተያያዘም የኬፕለር ኢትዮጰያ ሊድትሬነርስ ስልጠናው የሚሰጠው ኬፕለር ኢትዮጰያ በተሰኘ ተቋም አማካኝነት መሆኑን ገልፀው ከቴክኒካል ችሎታ ባሻገር ሶፍት እስኪልን ማዳበር እንዲቻል Professionalizem, communcation, technology, problem solving ላይ ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። አክለውም ከሰልጣኝእና ከአሠልጣኝ ባሻገር የአስተዳደር ሰራተኛው በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራርን እንዲከውን ያግዝ ዘንድ መሆኑን በማመላከት ስልጠናውን አስጀምረዋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
ዕለተ ዓርብ የካቲት 15/2016ዓ.ም
ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ከየስልጠና ዘርፍ ከተውጣጡ የተማሪ ተወካዮች የጋራ የምክክር መድረክ አካሄዱ።
የምክክር መድረኩ ዓላማ ሰልጣኞች ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ማስቻልና የስልጠና ጥራት እና የግዜ አጠቃቀማቸው ያለበትን ደረጃ እንዲሁም ከትብብር ስልጠና አወጣጥ ጋር በተያያዘ ያለበትን ደረጃ መገምገም ላይ ያለመ ነው።
የኮሌጁ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ይህ የምክክር መድረክ ስልጠናው ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተሰጠ ነው ወይ? የስልጠና አሰጣጥና አቀባበል ፣ በትብብር ስልጠና አወጣጥ ላይ እንዲሁም የክበባት አወቃቀርና እንቅስቃሴን አስመልክቶ ውይይት ለማካሄድ መሆኑን ገልፀዋል።
በተያያዘም የIT ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ወ/ሮ መሰረት ስልጠና ዘርፉ የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎችን ከlevel 1-4 ያሉ Unit of competency እና የቆይታ ግዚያቸውን ተሞክሮ ያቀረቡ ሲሆን የስራ ትስስር ጋይዳንስና ካውንስሊንግ አስተባባሪ አቶ ሙሉጌታ ጋሻው ከስልጠና ጥራትና ግዜ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ከአሰልጣኙ ባሻገር የሰልጣኞች ተነሳሽነት ወሳኝ እንደሆነ ጠቁመው ከትብብር ስልጠና ጋር በተያያዘ 70% የኮሌጁ 30% የኢንዱስትሪው መሆኑንና ስልጠናውን በአግባቡ መሰልጠን እውቀትን ከማዳበር ባሻገር ስራ የማግኘት እድላቸው ሰፊ በመሆኑ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አመላክተዋል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ከተሳታፊዎች ከሰዓት አጠቃቀም ፣ ከግብአት እጥረት፣ ከስልጠና ዲሲፕሊን ጋር በተያያዘ የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዬች ም/ዲን የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል። በመጨረሻም የተማሪዎች ፕሬዝዳንት በስሩ ያሉትን አባላት በማስተዋወቅ መርሀ- ግብሩ ተጠናቋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+3
ዕለተ ሀሙስ የካቲት 14/2016ዓ.ም
የኮሌጁ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎችና የኮሌጁ ዲኖች የምክክር መድረክ አካሄዱ።
በበጀት ዓመቱ የክህሎት ውድድር ለማካሄድ ዕቅድ መተዘጋጀቱና ለስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች መቅረቡ ይታወሳል። በመሆኑም በዛሬው ዕለት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ, ምክትል ዲኖችና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች በተገኙበት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችና በስራ ወቅት የገጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱም ላይ በኮሌጁ ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋና የስራ ሂደት የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ክፍል አስተባባሪ አቶ ኪሩቤል አከለ ሲሆኑ ሰነዱ ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦
- ከቴክኖሎጂ ልየታ ጋር ተያይዞ የተሰሩ ስራዎች
- ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለበት ደረጃ
- አይሲቲ ፕሮጀክት
- ከፋሽን ሾውና ከክህሎት ውድድር ጋር ተያይዞ የተሰሩ ስራዎች በዝርዝር ተዳሰዋል።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ምክረ ሀሳቦችና አስተያየቶች በኮሌጁ ዋና ዲንና ምክትል ዲኖች መከወን ስላለባቸው ተግባራት የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥና በቀጣይ መሰል ውይይቶች እንዳሉ በማመላከት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+3
ከካንብሪጅ አካዳሚ ኢትዬጵያ የመጡ ተማሪዎች ኮሌጁን ጎበኙ።
ከካንብሪጅ አካዳሚ ኢትዬጵያ የመጡ ተማሪዎች የኮሌጁ መድመቂያ ፈርጥ የሆነውን ኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ በመምህሮቻቸው በመታገዝ ተዘዋውረው ጉብኘኘት ያደረጉ ሲሆን የጉብኝቱ ዓላማ ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ መነሳሳት እንዲኖራቸው ለማስቻል ታልሞ ነው።
ኮምንኬሽን ክፍል
1 145
+4
ዕለተ ረብዕ የካቲት 13/2016ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒ ኮሌጅ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቋሚ የጽዳት ዘመቻ ቀን መጀመሩ ይታወሳል። የስራ አካባቢን ምቹና ውብ ለማድረግ በተለያዩ ግዚያት እየተሰሩ ካሉ ስራዎች መካከል አንዱ የፅዳት ዘመቻ ነው። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠል ኮሌጃችንን ውብና ማራኪ እንዲሁም ምቹ የስራ አካባቢን መፍጠር የሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ ተሳትፎን የሚጠይቅ በመሆኑ "ምቹ የስራ አካባቢን በጋራ እንፍጠር" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል። ይህ ዘመቻ ቀጣይነት ያለው ሲሆን በዛሬው ዕለት በተከናወነው የጽዳት ዘመቻ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና የክፍል አስተባባሪዎች እንዲሁም ሰልጣኞች ተሳትፈውበታል።
"ምቹ የስራ አካባቢን በጋራ እንፍጠር"
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+3
የኮሌጁ IT ስልጠና ዘርፍ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች የጋራ የምክክር መድረክ አካሄዱ።
የምክክር መድረኩ ዓላማ ሰልጣኞችን ብቁ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል እየተሰራ ያለው ስራ ምን ይመስላል? ስልጠናው ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተሰጠ ነው ወይ? እንዲሁም ከትብብር ስልጠና አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና በቅጥረ ግቢው ለስልጠና አሰጣጥ እና አቀባበል ያሉ ሁኔታዎች አስመልክቶ ከስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ ፣ አሰልጣኞችና ከተማሪዎች ተወካዮች ጋር ምክክር ማድረግ ላይ ያለመ ነው።
የIT ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ወ/ሮ መሰረት ስልጠና ዘርፉ የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎችን ከlevel 1-4 ያሉ Unit of competency እና የቆይታ ግዚያቸውን ያቀረቡ ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ ከተሳታፊዎች ከሰዓት አጠቃቀም ፣ ከስልጠና ዲሲፕሊን እና ከግብአት እጥረት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ሀሳብ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዬች ም/ዲን የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መርሀ- ግብሩ ተጠናቋል።
ኮምንኬሽን ክፍል
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
