ሰዋስው ☘☘☘☘
Відкрити в Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Показати більше1 161
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፲፫ (13) ቀን።
❤ እንኳን ለቅዱስ እግዚአብሔር ስለ ልጅ ወልድ በዮርዳኖስ ለመሰከረበትና ቃና ዘገሊላን አሰመልክቶ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓልና 372 ዓመት አንቀላፍተው ለተነሱ ለሰባቱ ደቂቅ ስማቸው ለቅዱሳን ለአርሰሌዳስ ለዱአሚዶስ፣ ለአውጋንዮስ፣ ለድሜጥሮስ፣ ለብርጥስ፣ ለእስጢፋኖስና ለኪራኮስ ዕረፍት፣ ለቃሮስና ለሰሚኖስ ለመታሰቢያቸውና ሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች በስንክሳሩ ከሚታሰቡ፦ ከአባ ነካሮ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ፦ ሃሌ ሉያ "ኅቡር መንበሩ ምስለ አቡሁ ዘዕሩይ ምክሩ ምስለ ወላዲሁ ዘእምቅድመ ዓለም መንግሥቱ ሰፋኒት ለቅዱሳን እዘዝ እንዘ ነአምን ወንገኒ ከመ ውእቱ ረዳኢ ወመድኅን አማን እደ መዝራዕቱ ለልዑል"። ትርጉም፦ ከአባቱ ጋር ክብሩ አንድ ነው ከወለደው ጋር ምክሩ የተስተካከለ ነው ከዓለም አስቀድሞ መንግሥቱ ምሉዕ የቅዱሳን ጽናት መድኃኒት (አዳኝ) እና የሚረዳ እንደሆነ እያመንን እናመሰግናለን በእውነት የልዑል ልጁ ክንዱ ነው።
+ + +
❤ የዕለቱ እግ. ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ልደቱ መንክር አስተርእዮቱ ምስጢር ለዋህድ ለወልደ እግዚአብሔር በልደቱ ተርህወ ሰማይ ወበጥምቀቱ ተዐውቀ መለኮቱ"። ትርጉም፦ ልደቱ ድንቅ መገለጡም ምሥጢር ነው ለአንድ ለእግዚአብሔር ልጅ (ወልድ) በልደቱ ሰማይ ተከፈተ በጥምቀቱም መለኮቱ (አምላክነቱ) ታወቀ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ሰባቱ ደቂቅ፦ እነዚህም ስማቸው አርሰሌዳስ፣ ዱአሚዶስ፣ አውጋንዮስ፣ ድሜጥሮስ፣ ብርጥስ፣ እስጢፋኖስና ኪራኮስ ናቸው። እሊህ ቅዱሳን ሃይማኖታቸው ለቀና ለታላላቅ የአገር ሰዎች ልጆቻቸው ናቸው እነርሱም ክርስቲያኖች እንደሆኑ በከሀዲ ንጉሥ ዳኬዎስ ዘንድ ሰዎች ነገር ሠሩባቸው ወደርሱም አስቀርቦ ለጣዖት እንዲሰግዱ ግድ አላቸው እምቢ ባሉትም ጊዜ ከልባቸው ጋር ይመክሩ ዘንድ ቀጠሮ ሰጣቸውና እርሱ ወደ ተግባሩ ሔደ።
❤ እሊህ የተባረኩ ሰባቱ ደቂቅም ወደ ቤታቸው ሔዱና ገንዘባቸውን ለድኆችና ለምስኪኖች በተኑ የቀረውንም ለስንቃቸው ይዘው ሔዱ ከከተማውም በስተ ምሥራቅ በዋሻ ውስጥ ተሠውሩ ብልና አስተዋይ የሆነ ወጣት ዱአሚዶስ ወደ ከተማ ሒዶ ምግባቸውን በመግዛት የሚያገለግላቸው ሆነ የሰማውንም ነገር ይነግራቸዋል። ንጉሥ ዳኬዎስም ከሔደበት በተመለሰ ጊዜ እሊህን ሰባት ልጆች ፈለጋቸው በዋሻ ውስጥ ተሸሽገው እንዳሉ በነገሩት ጊዜ የዋሻውን አፍ በደንጊያ እንዲደፍኑ አዘዘ የእነዚህንም ቅዱሳን ነፍሳቸውን በተኙ ጊዜ ጌታችን ወሰደ። ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመትም እንዲአንቀላፉ አደረጋቸው ከንጉሥ አሽከሮችም ስማቸው ቴዎድሮስና መቅዶስዮስ የተባሉ ሁለት የእርሳስ ሠሌዳዎች ወስደው የእሊህን የሰባት ደቂቅን ዜናቸውንና የዘመኑን ቊጥር ጽፈው ቀርጸው ከዋሻው አፍ አኖሩት።
❤ ከዚህም በኋላ ዳኬዎስ ሞተ እስከደጉ ንጉሥ እስከ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ብዙ ነገሥታት ነገሡ በዚህም ደግ ንጉሥ ዘመን ትንሣኤ ሙታን የለም የማሉ ከሀድያን ሰዎች ተነሡ እሊህም ሰባቱ ደቂቅ የሚነቁበት ጊዜ ሲቀርብ ለበጎቹ ማደሪያ ሊአሠራ ሽቶ ደንጊያ እየፈለገ የዋሻውን አፍ አንድ መኰንን ከፈተው። እሊህ ቅዱሳንም በሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመት በነቁ ጊዜ ምግባቸውን ይገዛ ዘንድ ዱአሚዶስን ላኩት የአገር ሰዎችም የዳኬዎስ ስም የተጻፈበትን ዲናር በእጁ ውስጥ በአዩ ጊዜ የተሸሸገ የወርቅ ሣጥን ያገኘ መስሎአቸዋልና ይዘው ወደዳኞቹና ኤጲስቆጶሳት አቀረቡት በመረመሩትም ጊዜ እነርሱ ሰባት ልጆች እንደሆኑ ነገራቸው። በሔዱም ጊዜ ፊታቸው እንደ ፀሐይ ሲበራ አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱም የዕርሳስ ሠሌዳ አየ አንሥቶም በላዩ የተጻፈውን ዜናቸውንና የዘመኑን ቊጥር አነበበ በዳኬዎስ ዘመን እንዳንቀላፉ ሕዝቡ ሰምተው እጅግ አደነቁ። እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ላኩ እርሱ መጥቶ እጅ ነሣቸው ከእርሳቸውም ተባረከ ከሠራዊቱ ጋር ከተነጋገሩም በኋላ ሁሉንም ባረኳቸውና በምድር ላይ ተኙ ነፍሳቸውንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ በዚያቺም ዋሻ ውስጥ ቀበሩአቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የእሊህም ቅዱሳን በረከት ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ነካሮ፦ ይህም ቅዱስ ሰው ሳያውቀው በሥውር የሚጋደል ሆነ እርሱም ከምንጣፉ በታች እሾህ ይጐዘጒዛል ጤና አግኝቶ እንዳይተኛ ነው በቀንና በሌሊትም ለጸሎት ይተጋ ነበር። ከትሑትነቱም የተነሣ የበር ጠባቂ አደረጉት። በዚያም ገዳም በመንፈስ ቅዱስ የተሠወሩ ነገሮችን የሚያይ ባሕታዊ መነኰስ አለ በአንዲትም ሌሊት በሕልሙ በከፍታ ቦታ ላይ ቁሞ አየ ከበታቹም ፍሬው በየዓይነቱ የሆነ አትክልት አለ ወንዞችም ከበውታል አባ ነካሮም በመካከላቸው ሁኖ በወዲያና በወዲህ ያጠጣቸው ነበር። ያ መነኰስም "ወንድሜ ነካሮ ሆይ ይህ አትክልት የማን ነው" አለው አባ ነካሮም "እኔ የተከልኳት ናት" ብሎ መለሰለት መነኰሴውም "ከፍሬዋ ትሰጠኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው አባ ነካሮም ሦስት የሮማን ፍሬ ቆርጦ ሰጠው በልሱም ቋጠረው።
❤ በነቃም ጊዜ እነዚያን የሮማንፍሬዎች አገኛቸው ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሔደ ከበር ቁሞ አገኘውና "ወንድሜ ነካሮ ሆይ በዚች ሌሊት አይተኸኛልን" አለው እርሱም "አዎን አይቼሃለሁ ሦስት የሮማን ፍሬዎችን ሰጥቼህ የለምን" አለው። በዚያንም ጊዜ ያ መነኵሴ ወደ ገዳሙ ሔዶ የሆነውን ሁሉ ለአበምኔቱና ለመነኰሳቱ ነገራቸው እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አሳያቸው መነኰሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሣ አደነቁ ያን ጊዜም የበጋ ወራት ነበርና የሮማንም ጊዜው አልበረምና።
❤ በዝቅተኛ ማዕረግ ላይ ስለአደረጉት መነኰሳቱ አዘኑ በከፍተኛም ማዕረግ ሊያደርጉት ሽተው ወደርሱ በሔዱ አጡት ታላቅ ኀዘንንም አዘኑ ከዚህም በኋላ በዚች ዕለት እንዳረፈ። መጻተኞች ነገሩአቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ነካሮ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 13 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "መኑ አምላክ ዐቢይ ከመ አምላክነ። አንተ እግዚአብሔር ባሕቲትከ ዘትገብር መክረ። አርአይኮሙ ለሕዝብከ ኃይለከ"። መዝ 76፥13-14። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 4፥43-46።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ነጽረኒ ወስምዐኒ እግዚኦ አምላኪየ። አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢይኑማ ለመዊት። ወከመ ኢይበሉኒ ጸላእትየ ሞዕናሁ"። መዝ 12፥3። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 10፥1-14፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10-22 እና የሐዋ ሥራ 2፥22-33። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 2፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ እግዚአብሔር አብ በዓልና የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
1 161
✴️✴️✴️✴️✴️✴️✴️✴️✴️✴️
ስርዓተ ማህሌት ዘጥር እግዚአብሔር አብ
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
ሥርዓተ ነግሥ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
@EOTCW
@EOTCW
ነግስ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኩሉ ዓለም
ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም
ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም
ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም
ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ፦
ነአምን በአሀዱ አምላክ እግዚአብሔር አብ አኃዜ ኩሉ፤ ገባሬ ሰማያት ወምድር፤ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ
@EOTCW
@EOTCW
ዘጣዕሙ፦
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።
@EOTCW
ዚቅ፦
ቅዱስ እግዚአብሔር እማርያም ተወልደ ቅዱስ እግዚአብሔር በዮርዳኖስ ተጠምቀ
@EOTCW
መልክዐ እግዚአብሔር አብ፦
ሰላም ለዝክረ ስምከ ስቡሕ ወውዱስ፤ዘትሴባሕ ወትረ በአፈ ኩሉ ዘነፍስ፤እግዚአብሔር እስመ አልብከ ተጽናስ፤እምቅድመ ዘመን ዘመናዊ ወድኅረ ዘመናት ሐዲስ፤እንዘ ለዘመናት አንተ ሕገ ዛኅን ወመርስ።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ፦
ስቡሕ በውስተ ቅዱሳን በመንክር ኃይለ ስብሐቲከ፤ዘትገብር መድምመ
@EOTCW
@EOTCW
መልክዐ እግዚአብሔር አብ፦
ሰላም ለቀራንብቲከ ወለአዕይንቲከ ብሩሃት፤ዘኢይትጋወሮን ጽልመት፤እግዚአብሔር አብ አበ ብርሃናት፤አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢይኑማ ለመዊት፤እስመ ለከ ኀይል ወለከ ስብሐት።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ፦
ንስግድ ለአበ ብርሃናት ወለወልዱ ዋህድ፤ወእመንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ ሥሉስ ዕሩይ
@EOTCW
@EOTCW
መልክዐ እግዚአብሔር አብ፦
ሰላም ለልብከ ጻድቅ ወየዋህ፤ወለሕሊናከ ዓዲ ማእምረ ዘመን ነዋኅ፤እግዚአብሔር አብ በአፈ ኩሉ ስቡሕ፤እስመ ሣህልከ ወምሕረትከ ብዙኅ፤የማንከ ለምሕሮ ኩለሄ ስፋሕ።
@EOTCW
ዚቅ፦
ዓይነ ኩሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ፤ አንተ ትሁቦሙ ሲሳዮሙ በጊዜሁ፤ትሰፍሕ የማነከ፤ወታጸግብ ለኩሉ እንስሳ ዘበሥርዓትከ
@EOTCW
ዓርኬ፦
እግዚአብሔር አብ አኃዜ ዓለም በእድ፤ እግዚአብሔር አብ አቡሁ ለወልድ፤ እግዚአብሔር አብ ዘዓረፍተ ቤትከ ነድ፤ ፈቃድከ ይኩን እግዚኦ ለዘይመጽአ ነገድ፤ እስመ መልዓ ስብሐቲከ በዛቲ አጸድ
@EOTCW
ዚቅ፦
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዓረፍተ ጽርሑ ዘነድ ወጸፍጽፈ ቤቱ በረዱ፤ኅቡር ህላዌሁ ዘኢይትበዓድ ሎቱ ለባህቲቱ ይደሉ ሰጊድ
@EOTCW
@EOTCW
ምልጣን፦
ኅቡር መንበሩ ምስለ አቡሁ ዘዕሩይ ምስለ ወላዲሁ ዘእምቅድመ ዓለም መንግስቱ ሰፋኒት ለቅዱሳን እዘዝ፤እንዘ ነአምን ወንገኒ ከመ ውእቱ ረዳኢ ወመድኅን አማን እደ መዝራዕቱ ለእዱ ለልዑል
@EOTCW
@EOTCW
አመላለስ፦
አማን በአማን እደ መዝራዕቱ/2/
እደ መዝራዕቱ ለልዑል/4/
እስመ ለዓለም፦
አመ ሣልስት ዕለት ከብካብ ኮነ፤በቃና ዘገሊላ፤ዘረሰዮ ለማየ ወይነ፤ወሀለወት ህየ እሙ ለኢየሱስ፤ወትቤሎ እሙ ወይንኬ አልቦሙ፤ወትቤሎ ሐልቀኬ ወይኖሙ፤ወይቤሎሙ ቅዱሑ ማየ ወምልዕዎን ለመሳብክት እስከ አፉሆን፤ቀድሑ ወወሀብዎ ለሊቅ ምርፋቅ፤ማ፦ ጥዒሞ አንከረ ሊቀ ምርፋቅ በረከት ዘአምላክ ገብረ፤ እስመ በረከተ ይሁብ መምህረ ሕግ
https://t.me/Eotcw
#Join & share
1 161
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ስርአተ ዋዜማ ዘጥር በዓለ እግዚአብሔር አብ
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️
ሃሌሉያ
ግሩም እምግሩማን ዘመጽአ ውስተ ዓለም፤መንክር ላህዩ ይሤኒ እምሰብአ፤ልህቀ ህፃን ወጸንዓ በኃይል፤ማ፦ ፈጺሞ ሕገ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ
@EOTCW
@EOTCW
አመላለስ፦
ፈጺሞ ሕገ ዮርዳኖስ ተጠምቀ/2/
ፈጺሞ ሕገ በዮርዳኖስ ተጠምቀ/4/
@EOTCW
@EOTCW
ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ፦
በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፈጺሞ ሕገ ወአስተርአየ ገሃደ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ
@EOTCW
@EOTCW
እግዚአብሔር ነግሠ፦
ልደቱ መንክር አስተርእዮቱ ምሥጢር ለዋህደ ለወልደ እግዚአብሔር በልደቱ ተርኅወ ሰማይ ወበጥምቀቱ መለኮቱ
@EOTCW
ይትባረክ፦
ርእዩከ ማያት እግዚኦ፤ ርእዩከ ማያት ወፈርሑ፤ ደንገጹ ቀላያተ ማያት ማያቲሆሙ።
@EOTCW
@EOTCW
ሰላም
ሃሌ ሃሌ ሉያ ሰላም ዘአብ ወፍቅር ዘወልድ፤ሃይማኖት ዘመንፈስ ቅዱስ፤ ይኅድር ማዕከሌክሙ፤አምላከ ሰላም የሃሉ ምስሌክሙ
አመላለስ፦
ሰላም ዘአብ ወፍቅር ዘወልድ/2/
ሃይማኖት ዘመንፈስ ቅዱስ ይኅድር ማዕከሌክሙ/4/
https://t.me/Eotcw
#Join & share
1 161
✞ጥምቀተ ክርስቶስ✞
በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱
ክፍል አምስት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሚዜዎችን 'ኵሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ፤ ያዘዛችሁን ዂሉ አድርጉ፤' ማለቷ "አንቺ ሴት ከአንቺጋር ምን አለኝ? የሚለው የጌታችን መልስ እሺታን (ይኹንታን) የሚገልጽ ቃል መኾኑን ያስረዳል፡፡
ጌታችንም "ውኃ ቅዱና ጋኖችን ምሏቸው"ባላቸው ጊዜ በታዘዙት መሠረት ውኃውን ቀድተው ጋኖችን ሞሏቸው፡፡ ውኃውንም ክብር ይግባውና በአምላካዊ ችሎታው ወደ ወይን ጠጅ ለወጠው፤ ለአሳዳሪውም ሰጠው፡፡
አሳዳሪው የወይን ጠጅ የኾነውን ውኀ ቀምሶ አደነቀ፤ ከወዴት እንደ መጣ ግን አላወቀም፡፡ ድንቅ በኾነ አምላካዊ ሥራ እንደ ተለወጠም አልተረዳም፡፡ ያን ምሥጢር የሚያውቀው ባለ ሰርጉ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ውኀውን የቀዱ ሰዎች ናቸውና፡፡
ታዳሚዎችም "ሰው ዂሉ የተሻለውን ወይን አስቀድሞ ያቀርባል፤በኋላም ተራውን የወይን ጠጅ ያቀርባል፡፡ አንተስ መናኛውን ከፊት አስቀድመህ ያማረውን ከኋላ ታመጣለህን?"በማለት አደነቁ፡፡
ቀድሞም የአምላክ ሥራ እንደዚህ ነው፤ ብርሃን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ጨለማን ፈጥሯል፤ ከጨለማ ቀጥሎ "ብርሃን ይኹን!" በማለት ብርሃንን ፈጥሯል፡፡ መጀመሪያ ብርሃን ተፈጥሮ ኋላ ጨለማ ቢፈጠር ይከብድ ነበርና መጀመሪያ ፳፩ ፍጥረታት ፈጥሯል፡፡
በመጨረሻም በአርአያውና በአምሳሉ የሰው ልጅን ፈጥሯል፡፡ ናትናኤልንም፤- "ከእንግዲህ ወዲህ ከዚህ የሚበልጥ ታያለህ" ብሎታል፡፡ ይህንን ማለቱም የእግዚብሔር ሥራ እየቆየ ውብ፣ ያማረ መኾኑን ያመለክታል፤ ሰው ግን 'የወደዱትን ቢያጡ ያጡትን ይቀላውጡ' እንዲሉ ጥሩ ነው የሚለውን ነገር ያስቀድማል፤ ያ ሲያልቅበት ደግሞ የናቀውን መፈለግ ይጀምራል፡፡
ተራውን ከፊት፣ ታላቁን ከኋላ ማድረግ የእግዚአብሔር ልማዱ ነው፡፡ ለሰው ልጅ በመጀመሪያ የተሰጠው የሚያልፈው ዓለም ነው፤ በኋላም የማያልፈው መንግሥተ ሰማያት ይሰጠዋል፡፡
ሰው መጀመሪያ ይሞታል፤ በመጨረሻ ትንሣኤ አለው፡፡ ሰው መጀመሪያ ሲወለድ ርቃኑን ነው፤ በኋላ የጸጋ ልብስ ይለብሳል፤ ሀብታም ይኾናል፡፡
ሰው ወደዚህ ዓለም ሲመጣ ዓለምን የሚያገኛት፣ የሚተዋወቃት በልቅሶ ነው፤ በኋላ ግን ይደሰታል፡፡ ተመልሶ በኀሣር፣ በልቅሶ ወደ መቃብር ይወርዳል፡፡ በደስታ "መቃብር ክፈቱልኝ? መግነዝ ፍቱልኝ?" ሳይል ይነሣል፡፡ ይህን የአምላክ ሥራም አድንቆ መቀበል እንጂ መቃወም አይችልም፡፡
፪.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
"ወሀለወት ህየ እሙ ለእግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ የጌታ እናት ከዚያ ነበረች፤" እንዲል፡፡ የተገኘችውም እንዲያው ዝም ብሎ አይደለም፡፡ በደግ ሰው ልማድ ተጠርታ እንጂ፡፡
ይህም እመቤታችን በማኅበራዊ ሕይወት የነበራትን ተሳትፎ እና በሰዎች ዘንድ የነበራትን ክብር ያመለክታል፡፡
በሌላ መልኩ በቤተ ዘመድ ልማድ ማንኛውም ዘመድ እንደ ተጠራው ዂሉ እርሷም በገሊላ በነበሩት ሰዎች ዘንድ ታላቅና ቤተ ዘመድ በመኾኗ በዚህ ሰርግ ተጠርታ ነበር፡፡ የተገኘችበት ሰው ሰውኛው ምክንያት ይህ ቢኾንም በዚያ ሰርግ ቤት ማንም ሊሠራው የማይችል የሥራ ድርሻ ነበራት፡፡
ይህ በሰዎች ዘንድ የማይታወቅ በእግዚአብሔርና በእርሷ መካከል ያለ አማላጅነት ነው፡፡ ይኸውም የጎደለውን መሙላት ለሚችል ውድ ልጇ የጎደለውን እንዲሞላ ማማለድ ነው፡፡
እመቤታችን ከሰው ልጆች የተለየች ክብርት፣ ቅድስት፣ ንጽሕት፣ ልዩ በመኾኗ የምታውቀው ምሥጢርም ከሰው የተለየ ነው፡፡ "ወእሙሰ ተዐቀብ ዘንተ ኩሎ ነገረ ወትወድዮ ውስተ ልባ፤ ማርያም ግን ይህንንዂሉ ትጠብቀው፣ በልቧም ታኖረው ነበር፤"ሉቃ.፪፥፲፱
የሚለው ቃልም ድንግል ማርያም አምላክን በመውለዷ ከሰው ልጆች የራቀ ምሥጢር እንደ ተገለጠላት ያስረዳል፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም "ጸጋን የተሞላሽ"በማለት የገለጠው ለእርሷ የተሰጠው ባለሟልነት ልዩ መኾኑን ለማስረገጥ ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ በሰርጉ ቤት የምትሠራውን ሥራ በውል ታውቅ ነበር፡፡
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
መምህርን ጠርቶ ደቀ መዝሙርን መተው ተገቢ አይደለምና፤ ደቀ መዛሙርቱ ከመምህራቸው ከክርስቶስ ጋር አብረው በሰርግ ቤት ተገኝተው ተአምራቱን ተመልክተዋል፤ በተደረገው ተአምርም አምላክቱን አምነዋል፡፡
ሐዋርያት ከዋለበት የሚውሉ፤ ከአደረበት የሚያድሩ፤ ተአምራት የማይከፈልባቸው፤ ወንጌሉን ለማስተማር የተመረጡ ናቸውና፡፡ ምክንያቱም አየን ብለው እንጂ ሰማን ብለው ቢያስተምሩ
አይታመኑምና፡፡
የሐዋርያት በሰርጉ ቤት መገኘትም ካህናት በተገኙበት ዕለት ሥርዓተ ጋብቻን መፈጸም ተገቢ መኾኑን ያስገነዝባል፡፡
በሰርግ ቤት የካህናት መገኘት እና ቡራኬ መስጠት አስፈላጊ ነውና፡፡ በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፳፬ የተገለጸውም ይህ ትምህርት ነው፤ "ወማዕሰረ ተዋሰቦሶ ኢይትፌጸም ወኢይከውን ዘእንበለ በሀልዎተ ካህናት ወጸሎት ዘላዕሌሆሙ፤ የጋብቻ አንድነት ካህናት ቢኖሩ እንጂ ያለእነርሱ አይጸናም፡፡ እነርሱ ጸሎት ሲያደርጉ እንጂ ያለ ጸሎት አይፈጸምም፤"እንዲል፡፡
በጥንተ ፍጥረት "ሰው ብቻውን ይኾን ዘንድ መልካም አይደለም ረዳት እንፍጠርለት፤"ዘፍ.፪፥፲፱
በማለት የተናገረ አምላክ ጋብቻ በካህናት ቡራኬና ጸሎት መከናወን እንደሚገባው ሲያስተምረን በቃና ዘገሊላው ሰርግ ቅዱሳን ሐዋርያትን ይዞ ተገኝቷል፡፡
በአጠቃላይ የቃና ዘገሊላ ሰርግ እና በሰርጉ ላይ የታዩ ተአምራት ምልጃዎች ዂሉ ሌላ ምሥጢርንም ያዘሉ ናቸው፡፡ እመቤታችን "የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም" በማለት መናገሯ ሕዝብህን (ምእመናንን) "ደምህን አፍሰህ፣ ሥጋህን ቈርሰህ አድናቸው" ማለቷ ሲኾን፣ ይህም "ወይን" በተባለው የልጇ የክርስቶስ ደም ቤዛነት ዓለም ይድን ዘንድ እመቤታችን ያላትን የልብ መሻት ያስገነዝባል፡፡
"ጊዜዬ ገና አልደረሰም" የሚለው የጌታ ምላሽም ደሙ በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ የሚፈስበት ጊዜ ገና መኾኑን ያመላክታል፡፡ በሰርግ ቤት የተገኘው በሥጋው መከራ ከመቀበሉ አስቀድሞ ነውና፡፡
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት በረከት አይለየን፡፡
ከበዓለ ጥምቀቱ ረድኤት፣ በረከት ይክፈለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡አሜን!!!
ለአባታችን ለሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ቃለሕይወት ያሰማልን አሜን!!!
~~~~ ተፈጸመ ~~~~
https://t.me/Eotcw
1 161
05/05/2015 ዓ.ም
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ የቅዳሴ የሚባል ምስባክ
መዝ ፹፫፥፮
እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ፤
ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል፤
ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን።
#ትርጕም፦
የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና፤
ከኃይል ወደኃይል ይሄዳል፤
የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል።
https://t.me/Eotcw
1 161
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ማኅሌት ዘቃና ዘገሊላ
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።
@EOTCW
መልክአ ሥላሴ
ሥላሴክሙ ሥላሴ ይረስየኒ መካነ፤ ድኅረ ተዋሃድኩሰ ዘሥላሴሁ ብርሃነ፤ ዮርዳኖስክሙ ዝየ እስመ ኲለንታየ ኮነ፤ ኢየኃሥሥ እምዮርዳኖስ ሰማዕተክሙ ምዕመነ፣ ወኢይትሜነዮ ለታቦር እስመ ታቦር አነ።
@EOTCW
ዚቅ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ፤ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ፤ እማርያም ዘተወልደ አፍቂሮ ኪያነ፤ መጽአ ኀቤነ ዘነቢያት ሰበኩ ለነ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመ ይፌጽም ኲሎ ሕገ፤ ወአስተርአየ ገሃደ።
@EOTCW
መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤ ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤ ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤ ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤ አልቦ ብእሲ ዘየኀድግ ሱታፎ።
@EOTCW
ዚቅ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዘበተዋሕዶ ይሤለስ፤ እምኀበ ትጉሃን ይትቄደስ፤ እሳተ ሕይወት ዘኢይትገሠሥ፤ ወዘኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ፤ ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ፤ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ።
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሃላ ዘኢይሔሱ፤ ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሱ፤ አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቌጸል በርእሱ፤ አሕጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ።
@EOTCW
ዚቅ
ወዘምሩ ለስሙ፤ ሀቡ አኮቴተ ለስብሐቲሁ፤ በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ።
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለክሣድክ ግብረ መንፈስ ቅዱስ ኬንያ፤ አዳም ስና ወመንክር ላህያ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢይ ወሐዋርያ፤ አመ ወጽአ ስሙዓቲከ በአድያመ ኲሉ ሶርያ፤ ብጹአት አእይንት ኪያከ ዘርእያ።
@EOTCW
ዚቅ
ምድረ ዛብሎን ወንፍታሌም፤ ፍኖተ ባሕር ማዕዶተ ሦርያ ዘገሊላ፤ ሕዝብ ዘይነብር ውስተ ጽልመት ርእዩ ብርሃነ፤ እስመ ብርሃን ሠረቀ ሎሙ፤ ይትፌሣሕ ሰማይ ወትትሐሠይ ምድር፤ እስመ ኢየሱስ ክርስቶስ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ንዑ ናንሶሱ በብርሃኑ።
@EOTCW
ወረብ
ኢየሱስ ክርስቶስ መጽአ ውስተ ዓለም/፪/
በብርሃኑ ንዑ ናንሶሱ/፬/
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለመከየድከ አሐዱ አሐዱ፤ ውስተ ቤተ መቅደስ ለምሕሮ እለ ገይሠ ለመዱ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመዓዛ ፍቅርከ ዕቊረ ናርዱ፤ አኃዊከ ሰማዕታት ቆላተ ህማማት ወረዱ፤ ወጻድቃኒከ ገዳማተ ዖዱ።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ሠራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም፤ ይቀውሙ ቅድሜሁ ለመድኃኔዓለም፤ ወይኬልልዎ ለመድኃኔዓለም፤ ሥጋሁ ወደሙ ለመድኃኔዓለም፤ ወንብጻሕ ቅድመ ገጹ ለመድኃኔዓለም፤ በአሚነ ዚአሁ ሰማዕታት ከዓዉ ደሞሙ በእንቲአሁ።
@EOTCW
ወረብ
ሠራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም ይቀውሙ ቅድሜሁ ለመድኃኔዓለም/፪/
በአሚነ ዚአሁ ሰማዕታት ከዓዉ ደሞሙ/፪/
@EOTCW
@EOTCW
አንገርጋሪ
እንዘ ሥውር እምኔነ ይእዜሰ፤ ክሡተ ኮነ ማየ ረሰየ ወይነ፤ ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒነ፤ በቃና፤ ዘገሊላ ከብካብ ኮነ።
@EOTCW
አመላለስ
በቃና ዘገሊላ/፪/
ዘገሊላ ከብካብ ኮነ/፬/
@EOTCW
ወረብ
ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒነ/፪/
በቃና 'ዘገሊላ'/፪/ ከብካብ ኮነ/፪/
@EOTCW
እስመ ለዓለም
ዘበዳዊት ተነበየ፤ ወበዮሐንስ ጥምቀት ኃርየ፤ በቃና ዘገሊላ ማየ ወይነ ረሰየ፤ መዓዛ ቃልከ ይትወከፍ ጸሎትየ።
@EOTCW
አመላለስ፦
በቃና ዘገሊላ ማየ ወይነ ረሰየ፤
መዓዛ ቃልከ ይትወከፍ ጸሎትየ።
@EOTCW
ዕዝል፦
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤ ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
ምልጣን፦
እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤ ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
አመላለስ፦
እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤
ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
አቡን፦
በ፭ ወእንዘ ሀለው ውስተ ከብካብ፤ ቅረቡ ኃቤሁ ኩሎሙ አርዳኢሁ ፤አንክርዎ ለማይ አእኰትዎ ለኢየሱስ፤ በእንተ ማይ ዘኮነ ወይን
@EOTCW
@EOTCW
ምልጣን፦
አንክርዎ ለማይ አንክርዎ አእኰትዎ ለኢየሱስ፤ አንክርዎ ማይ አንክርዎ
@EOTCW
አመላለስ፦
አንክርዎ ለማይ አንክርዎ፤
አእኰትዎ ለኢየሱስ አእኰትዎ ለኢየሱስ።
ዓራራይ፦
ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ ለመድኃኒነ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራጽዮን፤ ፆፍ ፀዓዳ፤ ንጉስ አንበሳ እምዘርዓ ዘመጽአ
@EOTCW
@EOTCW
ሰላም
ተሣሐልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ፤ ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ ወበእንተ ጥምቀቱ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
ምልጣን
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ/፪/
ማዕከለ ባሕር ቆመ ማዕከለ ባሕር/፪/
👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@EOTCW👈
👉@EOTCW👈
👉@EOTCW👈
🇪🇹👆👆👆👆🇪🇹
@EOTCW
#Join & share
# መልካም አገልግሎት
1 161
✞ጥምቀተ ክርስቶስ✞
በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱
ክፍል አራት
"ጌትነቱን ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ፤"
ዮሐ. ፪፥፲፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የበዐላት አከባበር ቀመር ከበዓለ ልደት፣ ግዝረት እና ጥምቀት ቀጥሎ ቃና ዘገሊላ ይከበራል፡፡
ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ልዩ ልዩ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል፡፡
ከእነዚህ መካከልም በቃና ዘገሊላ በሰርግ ቤት ተገኝቶ ያደረገው ተአምር ተጠቃሽ ነው፡፡
ይህንንም ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ እንዲህ ጽፎታል፤"በሦስተኛው ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ኾነ፡፡" ምን በተደረገ በሦስተኛው ቀን የሚል ጥያቄ በኹላችንም አእምሮ እንደሚመላለስ አያጠያይቅም፡፡
ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማየ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ጥር ፲፩ ቀን ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ዕለቱን ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት ጾሞ፤ ዲያብሎስን ድል ነስቶ፤ መዋዕለ ጾሙን ፈጽሞ፤ ለእኛም ዲያብሎስን ድል የምንነሳበትን መንገድ አሳይቶ ከገዳመ ቆሮንቶስ መልስ ደቀ መዛሙርቱን መረጠ፡፡
ከጥር ፲፩ እስከ የካቲት ፳ ቀን ያለው ጊዜ ፵ ቀን ይኾናል፡፡ ጌታችን መዋዕለ ጾሙን የካቲት ፳ ቀን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን በገሊላ አውራጃ ቃና በተባለች መንደር ሰርግ ኾነ፡፡
በዚህ ሰርግ ብዙ ሰዎች መታደማቸውን ወይን ጠጁ ማለቅ ያስረዳናል፡፡ የተጠሩት ሰዎች ብዙ ለመኾናቸው ባሻገር ብዙዎችን መመገብ የሚችል አምላክ በሰርግ ቤት መጠራቱ ልዩ ዕለቱን ያደርገዋል፡፡ በዚህ ሰርግ ከሰዎች በተጨማሪ ሦስት አካላት ተጠርተዋል፡፡
፩.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
"ወጸውዕዎ ለእግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ጌታ ኢየሱስንም ጠሩት"
ዮሐ.፪፥፪
ተብሎ እንደ ተጻፈ እናትን ጠርቶ ልጅን መተው ተገቢ አይደለምና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጠርተው ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም ጠርተውታል፡፡
ይህም ፍጹም ሰው መኾኑን
ያስረዳል።ጌታችን እንደ ሰውነቱ ወደ ሰርግ ቤት ተጠራ፤ እንደ አምላክነቱ ተአምራቱን በማሳየት ጌትነቱን፣ አምላክነቱን ገለጠ፡፡
ከሚደሰቱት ጋር መደሰት፤ ከሚያዝኑት ጋር ማዘን ተገቢ መኾኑን መድኀኒታችን ክርስቶስ በተግባር አስተማረን፡፡
በቃና ዘገሊላ ከሰርግ ቤት እንደ ሔደው በአልዓዛር ቤት ለለቅሶ መገኘቱን ልብ ይሏል፡፡ ወደ ሰርግ ቤት የሔደው በደስታ ነበር፡፡ "ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አሕዛብ፤ ኢየሱስ በአሕዛብ ፊት ተአምራትንና ድንቆችንእያደረገ በደስታ ወደ ሰርግ ሔደ፤"በማለት ቅዱስ ያሬድ እንደ ገለጠው፡፡
ጌታችን ወደ አልዓዛር ቤት ሲሔድ ግን በኀዘን ውስጥ ኾኖ ነበር፡፡"ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እርሷ (ማርታ) ስታለቅስ ባየ ጊዜ በልቡ አዘነ፤ በራሱም ታወከ (ራሱን ነቀነቀ – የኀዘን ነው) ዕንባውን አፈሰሰ፡፡ አይሁድም ‹ምን ያህል ይወደው እንደ ነበር እዩ› አሉ፤"
እንዳለ ወንጌላዊው ዮሐ.፲፩፥፴፫-፴፰
ጌታችን "አምላክ ነኝና ከሰርግ ቤት አልሔድም፤ ከልቅሶም ቤትም አልገኝም፤" አላለም፡፡ ከዚህም ጌታችን ከኀጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ እንደ ሠራ፤ የሰውን የተፈጥሮ ሕግ እንዳከበረ እና እንደ ፈጸመ እንረዳለን፡፡
በመደሰት እና በማዘን ፍጹም ሰው መኾኑን፤ በሰርጉ ቤት ውኀውን የወይን ጠጅ በማድረግ፤ እንደዚሁም አልዓዛርን ከአራት ቀናት በኋላ ከሞት በማስነሣት ደግሞ ፍጹም አምላክ መኾኑን አስረዳን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ነውና በሰርግ ቤት የጎደለውን መላ፡፡ አምላክ ነውና የሞተውን አልዓዛርን "መግነዝ ፍቱልኝ? መቃብር ክፈቱልኝ? ሳይል" ከሞት እንዲነሣ አደረገ፡፡
"ወሶበ ኀልቀ ወይኖሙ ወትቤሎ እሙ ወይንኬ አልቦሙ፤ የወይን ጠጅ ባለቀባቸው ጊዜም እናቱ (እመቤታችን) 'የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም' አለችው።ዮሐ ፫፥፫
እርሱም "አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም፤" አላት፡፡
ይኸውም "ያልሽውን ልፈጽም ነው ሰው የኾንኩት፤ ያልሽኝን እንዳልፈጽም ከአንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ?"ማለት ነው፡፡ ‹ጊዜዬ ገናአልደረሰም› የሚለው ቃልም ጌታችን ሥራውን ያለ ጊዜው እንደማይፈጽመው ያሳያል፡፡
"ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ አለው፤" እንዲል
መዝ.፻፲፰፥፻፳፮
በሌላ መልኩ "ጊዜዬ ገና አልደረሰም" የሚለው ቃል እግዚአብሔር አምላካችን ይህን አድርግ ብሎ በግድ ማንም ሊያዝዘው የማይቻለውና በራሱ ፈቃድ የወደደውን ዂሉ የሚያደርግ፤ ቢፈልግ የሚያዘገይ፣ ሲፈልግ ደግሞ በዐይን ጥቅሻ በፈጠነ መልኩ መፈጸም የሚችል፤ በራሱ ፈቃድ እንጂ በሰምች ፈቃድ የማይመራ አምላክ መኾኑን ያስተምረናል፡፡
"ፈቃድህ በሰማይ እንደ ኾነችእንዲሁ በምድር ትኹን" ብላችሁ ለምኑኝ ያለውም ለዚህ ነው፡፡
የወይን ጠጁም ሙሉ ለሙሉ አላላቀም ነበር፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ያለውን ቢያበረክተው ተአምራቱን አናደንቅም የሚሉ ይኖራሉና ፈጽሞ ጭልጥ ብሎ እስከሚያልቅ ድረስ መጠበቅ እንደሚገባ ሲያስረዳ 'ጊዜዬ ገና አልደረሰም' አለ፡፡
ሰው ቢለምን፣ ቢማልድም እግዚአብሔር በእርሱ ፈቃድ ጊዜው ሲደርስ ነው የሚፈጽመው፡፡ ምልጃው አልተሰማም፤ ተቀባይነት አላገኝም ማለት ግን አይደለም፡፡ ተቀባይነት ያገኘ መኾኑ የሚታወቀው በመደረጉ ነውና፡፡
ተማላጅነት የአምላክ፤ አማላጅነት ደግሞ የፍጡራን መኾኑን ጌታችን በዚህ ሰርግ ቤት አስተምሯል፡፡ ጌታችን በሰርግ ቤት ባይገኝላቸው ኖሮ ሰዎቹ ምን ያህል ኀፍረት ይሰማቸው ይኾን? የእርሱ እንደዚሁም የእናቱ በሰርጉ ቤት መገኘት ለባለ ሰርጉና ለታዳሚዎች ሙላት ነበር፡፡
እርሱ ባይኖር የሰርጉ ቤት ከደስታ ይልቅ በኀዘን ሊሞላ ይችል እንደ ነበር ምንም ጥርጥር የለውም፡፡
አማላጅ ያስፈለገውም እርሱ የማያውቀው ምሥጢር ኖሮ፤ ሥራውን የሚሠራውም በስማ በለው ኾኖ አይደለም፡፡
ለሰው ልጆች ያለው ፍቅር ይታወቅ ዘንድ እና የሰው ልጆችን ከችግር የሚያወጣበት መንገዱ ብዙ መኾኑን ለማስረዳት ነው እንጂ፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሚዜዎችን 'ኵሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ፤ ያዘዛችሁን ዂሉ አድርጉ፤' ማለቷ "አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?" የሚለው የጌታችን መልስ እሺታን (ይኹንታን) የሚገልጽ ቃል መኾኑን ያስረዳል፡፡
ጌታችንም "ውኃ ቅዱና ጋኖችን ምሏቸው"ባላቸው ጊዜ...
ክፍል አምስት ይቀጥላል...
ይቆየን
https://t.me/Eotcw
1 161
ጥምቀተ ክርስቶስ
በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
ጥር ፲ ቀን፳፻፱
ክፍል ሦስት
ጌታችን ጥምቀቱን በውኀ ያደረገው በሌላ ያላደረገው ስለምንድን ነው ቢሉ ትንቢቱ፣ ምሳሌው ሊፈጸም፤
ትንቢት፦"ወእነዝኃክሙ በማይ ወትነጽሑ፤ ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ፤ እናንተም ትጠራላችሁ፤"ተብሎ ተነግሯል ሕዝ.፳፮፥፳፭፡፡
ምሳሌ፦ ውኀ ለዅሉ አስፈላጊ ነው፡፡ ያለ ውኀ መኖር የሚችል የለም፡፡ ጥምቀትም ለዅሉም የሚገባ ሥርዓት ነው፡፡ ያለ ጥምቀት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አይቻልምና፡፡ ውኀ መልክ ያሳያል፤ መልክ ያለመልማል (ያጠራል)፡፡ ጥምቀትም መልክዐ ነፍስን ያሳያል፤ መልክዐ ነፍስን ያለመልማልና (ያጠራልና)፡፡
መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥበት አየ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል መውረዱም ምሥጢር አለው
ርግብ ኃዳጊተ በቀል ናት፤ መንፈስ ቅዱስም ኃዳጌ በቀል ነውና፡፡ ርግብ በኖኅ ጊዜ 'ሐጸ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ፤ የጥፋት ውኀ ጎደለ' ስትል ቆጽለ ዕፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች፡፡ መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበሥራልና፡፡
ጥምቀቱን በቀን ያላደረገው በሌሊት ያደረገው ስለ ምን ነው ቢሉ
በቀን አድርጎት ቢኾን መንፈስ ቅዱስ በቁሙ ርግብ ነው በተባለ ነበርና፤ አሁንስ ርግብ አለመኾኑ መንፈስ ቅዱስ መኾኑ በምን ይታወቃል ቢሉ ጌታ የተጠመቀው ከሌሊቱ በዐሥረኛው ሰዓት ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ተሐዋስያን ወፎች (ርግቦች) ከየቦታቸው አይወጡምና መንፈስ ቅዱስ መኾኑ በዚህ ይታወቃል፡፡
መንፈስ ቅዱስም መውረዱ ከውኀው ከወጣ፣ ከዮሐንስ ከተለየ በኋላ ነው፡፡
ከውኀው ውስጥ ሳለ ወርዶ ቢኾን ለቀድሶተ ማያት ነው የወረደው ባሉት ነበርና፡፡ ከዮሐንስ ጋርም ሳለ ወርዶ ቢኾን ለክብረ ዮሐንስ ወረደ ባሉት ነበርና፡፡
ረቦ ወርዷል ያሉ እንደ ኾነ አብ ምሉዕ ነው፤ አንተም ምሉዕ ነህ፤ እኔም ምሉዕ ነኝ ሲል፡፡ አሰይፎ ወርዷል ያሉ እንደ ኾነ የብሉየ መዋዕል የአብ ሕይወት ነኝ፤ የአንተም ሕይወት ነኝ፤ እኔም ብሉየ መዋዕል ነኝ ሲል፡፡
ወርዶ ራሱን ቆንጠጥ አድርጎ ይዞታል ቢሉ አብ አኃዜ ዓለም ነው፤ አንተም አኃዜ ዓለም ነህ፤ እኔም አኃዜ ዓለም ነኝ ሲል፡፡ ምሥጢሩም እናንተም ብትጠመቁ መንፈስ ቅዱስ ይወርድላችኋል ለማለት፣ አብነት ለመኾን ነው፡፡
"ወናሁ መጽአ ቃል እምሰማይ ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ፤" ለተዋሕዶ የመረጥኩት በእርሱ ህልው ኾኜ ልገለጥበት የወደድኩት የባሕርይ ልጄ ይህ ነው፤ የሚል ቃል ከወደ ሰማይ ተሰማ፡፡
ይህም አብ የተናገረበት ቃል ያው የሚጠመቀው አካላዊ ቃል ነው እንጂ ሌላ ቃል አይደለም፡፡ የሥላሴ ልብ፣ ቃል፣ እስትንፋስ አንድ ነውና፡፡ አብ ልብ፤ ወልድ ቃል፤ መንፈስቅዱስ እስትንፋስ በመኾን አንድ አምላክ ነውና፡፡ "አብኒ ልቡናሆሙ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ ወልድኒ ቃሎሙ ለአብ ወለመንፈስቅዱስ ወመንፈስቅዱስኒ እስትንፋሶሙ ለአብ ወለወልድ፤ አብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ልቡናቸው ነው፡፡ ወልድም ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም ለአብ ለወልድ ሕይወታቸው ነው፤"በማለት ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት እንደ ተናገረው፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀውም በሠላሳ ዓመቱ ነው" ሉቃ. ፫፥፳፫፡፡
በሠላሳ ዓመቱ የተጠመቀበት ምሥጢርም
አዳም የሠላሳ ዓመት፤ ሔዋን የዐሥራ አምስት ዓመት ሰው ኾነው ተፈጥረው አዳም በዐርባ ቀን፣ ሔዋን በሰማንያ ቀን ከሥላሴ የተቀበሉትን ልጅነት በምክረ ከይሲ ዕፀ በለስን በልተው አስወስደው ነበረና በሠላሳ ዓመቱ ተጠምቆ መልሶላቸዋል፡፡
በሠላሳ ዓመት የመጠመቁ ምሥጢር ይህ ሲኾን እኛ ዛሬ ወንዶች በዐርባ ቀን፣ ሴቶች በሰማንያ ቀን በዕለተ ዓርብ ከቀኝ ጎኑ በፈሰሰው ማየ ገቦ ተጠምቀን ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ሁለተኛ የምንወለድበት ምክንያትም አዳም በዐርባ ቀኑ፣ ሔዋን በሰማንያ ቀኗ ከሥላሴ ያገኙትን ልጅነት መሠረት በማድረግ ነው።
ኩፋ. ፬፥፱
የምንጠመቀውም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው፡፡ "ወእንዘ ታጠምቅዎሙ በሉ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ስታጠምቋቸውም በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው፤"እንዲል ማቴ. ፳፰፥፲፱
ዛሬም ታቦታቱን ወደ ጥምቀተ ባሕር በማውረድ በዓለ ጥምቀቱን ለሚያከብሩ ክርስቲያኖች በሙሉ ከታቦታቱ ሁለት ሺሕ ክንድ ርቀው መከተል እንዲገባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተብሎ ተገልጿል፤ "ሕዝቡን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡ በእናንተና በታቦቱ መካከል ያለውርቀት በስፍር ሁለት ሺሕ ክንድ ይኹን፡፡ በዚህ መንገድ በፊት አልሔዳችሁበትምና፤ የምትሔዱበትን መንገድ እንድታውቁ ወደ ታቦቱ አትቅረቡ፤።"
ኢያ.፫፥፩–፲፯
ይህ ኃይለ ቃል ዛሬ ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው ለማደራቸው መነሻ ትምህርት ነው፡፡ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀትም ጌታችን ከተጠመቀበት ከ፴ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ሲከበር ይኖራል፡፡
"ጌትነቱን ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ፤"
ዮሐ. ፪፥፲፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የበዐላት አከባበር ቀመር ከበዓለ ልደት፣ ግዝረት እና ጥምቀት ቀጥሎ ቃና ዘገሊላ ይከበራል፡፡
ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት ልዩ ልዩ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከእነዚህ መካከልም....
ክፍል አራት ይቀጥላል
ይቆየን
https://t.me/Eotcw
1 161
እፎ ሀሎክሙ ተለውተ ክርስቶስ ኩልክሙ። ዮም አነ እጽሕፍ ለክሙ በይነ ጥምቀት።
* ተለውተ ክርስቶስ --> የክርስቶስ ተከታዮች
* በይነ ጥምቀት --> ስለ ጥምቀት
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፲ወ፪ ወይብል ከመዝ
``... እምቃለ ቅዱስ ቄርሎስ (ከቅዱስ ቄርሎስ ድርሰት)
° ወተጠምቀ እም ዮሐንስ።
(ከዮሐንስ ተጠመቀ።)
° በወርኀ ፅርዕ ጦቢ አመ ፲ወ፩ ለጥር። ወበወርኀ ሮሜ ቅድመ ሰመንቱ።
(በፅርዕ ቋንቋ ጦቢ በሚባል በጥር በዐሥራ አንድ ቀን። በሮም አቆጣጠር በስምንተኛው ቀን ዋዜማ ከሌሊቱ በዐሥር ሰዓት።)
° ወበግእዝ አመ ፲ወ፩ ለጥር በዐሠርቱ ሰዓት ዘሌሊት።
(በኢትዮጵያ አቆጣጠር በጥር በዐሥራ አንድ ቀን በዐሥረኛው ሰዓት ሌሊት ተጠመቀ።)
° አሜሃ ሖሩ ክልኤሆሙ ውስተ ዮርዳኖስ።
(ያንጊዜ ሁለቱ ጌታና ዮ።ሐንስ ወደ ዮርዳኖስ ሄዱ።)
° ወፈልሑ ማያት ከመ ዘሞቀ።
(ውኃው በእሳት እንዳፈሉት ፍልቅልቅ አለ።)
° ወሶቤሃ ተርኅወ ሰማይ። ወወረደ መንፈስ ቅዱስ በአርአያ ርግብ ወነበረ ዲቤሁ።
(ሰማይ ተከፈተ። መንፈስ ቅዱስም በአምሳለ ርግብ ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ።)
° ወተጠሚቆ ወፅአ ወቃልሂ እምሰማይ ተሰምዐ ከመ ፀዓይ ዓቢይ። እንዘ ይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ፍቁር ዘቦቱ ሠመርኩ።
(ተጠምቆ ከወጣ በኋላ የምወደው የምወልደው ለተዋሕዶ ለመሥዋዕትነት የመረጥኩት ልጄ ይህ ነው የሚል ቃል ከሰማይ እንደ መብረቅ ተሰማ።)
° ወውእቱ ኢየሱስ አመ ፴ ዓመቱ ተጠምቀ እምዮሐንስ።
(ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሠላሳ ዘመኑ ከዮሐንስ ተጠመቀ።) ...
#_ናሁ_ፈጸምነ_ዘይእዜ_ትምህርተ_እግዚአብሔር_ያስተራክበነ_ለይመጽእ_ጊዜ_በሰላም_ወበጥዒና።
@Eotcw
ሠናይ ሶቤ✋
1 161
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ማኅሌት ዘቃና ዘገሊላ
🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።
@EOTCW
መልክአ ሥላሴ
ሥላሴክሙ ሥላሴ ይረስየኒ መካነ፤ ድኅረ ተዋሃድኩሰ ዘሥላሴሁ ብርሃነ፤ ዮርዳኖስክሙ ዝየ እስመ ኲለንታየ ኮነ፤ ኢየኃሥሥ እምዮርዳኖስ ሰማዕተክሙ ምዕመነ፣ ወኢይትሜነዮ ለታቦር እስመ ታቦር አነ።
@EOTCW
ዚቅ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ፤ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ፤ እማርያም ዘተወልደ አፍቂሮ ኪያነ፤ መጽአ ኀቤነ ዘነቢያት ሰበኩ ለነ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመ ይፌጽም ኲሎ ሕገ፤ ወአስተርአየ ገሃደ።
@EOTCW
መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤ ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤ ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤ ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤ አልቦ ብእሲ ዘየኀድግ ሱታፎ።
@EOTCW
ዚቅ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዘበተዋሕዶ ይሤለስ፤ እምኀበ ትጉሃን ይትቄደስ፤ እሳተ ሕይወት ዘኢይትገሠሥ፤ ወዘኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ፤ ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ፤ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ።
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሃላ ዘኢይሔሱ፤ ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሱ፤ አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቌጸል በርእሱ፤ አሕጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ።
@EOTCW
ዚቅ
ወዘምሩ ለስሙ፤ ሀቡ አኮቴተ ለስብሐቲሁ፤ በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ።
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለክሣድክ ግብረ መንፈስ ቅዱስ ኬንያ፤ አዳም ስና ወመንክር ላህያ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢይ ወሐዋርያ፤ አመ ወጽአ ስሙዓቲከ በአድያመ ኲሉ ሶርያ፤ ብጹአት አእይንት ኪያከ ዘርእያ።
@EOTCW
ዚቅ
ምድረ ዛብሎን ወንፍታሌም፤ ፍኖተ ባሕር ማዕዶተ ሦርያ ዘገሊላ፤ ሕዝብ ዘይነብር ውስተ ጽልመት ርእዩ ብርሃነ፤ እስመ ብርሃን ሠረቀ ሎሙ፤ ይትፌሣሕ ሰማይ ወትትሐሠይ ምድር፤ እስመ ኢየሱስ ክርስቶስ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ንዑ ናንሶሱ በብርሃኑ።
@EOTCW
ወረብ
ኢየሱስ ክርስቶስ መጽአ ውስተ ዓለም/፪/
በብርሃኑ ንዑ ናንሶሱ/፬/
@EOTCW
መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለመከየድከ አሐዱ አሐዱ፤ ውስተ ቤተ መቅደስ ለምሕሮ እለ ገይሠ ለመዱ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመዓዛ ፍቅርከ ዕቊረ ናርዱ፤ አኃዊከ ሰማዕታት ቆላተ ህማማት ወረዱ፤ ወጻድቃኒከ ገዳማተ ዖዱ።
@EOTCW
@EOTCW
ዚቅ
ሠራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም፤ ይቀውሙ ቅድሜሁ ለመድኃኔዓለም፤ ወይኬልልዎ ለመድኃኔዓለም፤ ሥጋሁ ወደሙ ለመድኃኔዓለም፤ ወንብጻሕ ቅድመ ገጹ ለመድኃኔዓለም፤ በአሚነ ዚአሁ ሰማዕታት ከዓዉ ደሞሙ በእንቲአሁ።
@EOTCW
ወረብ
ሠራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም ይቀውሙ ቅድሜሁ ለመድኃኔዓለም/፪/
በአሚነ ዚአሁ ሰማዕታት ከዓዉ ደሞሙ/፪/
@EOTCW
@EOTCW
አንገርጋሪ
እንዘ ሥውር እምኔነ ይእዜሰ፤ ክሡተ ኮነ ማየ ረሰየ ወይነ፤ ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒነ፤ በቃና፤ ዘገሊላ ከብካብ ኮነ።
@EOTCW
አመላለስ
በቃና ዘገሊላ/፪/
ዘገሊላ ከብካብ ኮነ/፬/
@EOTCW
ወረብ
ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒነ/፪/
በቃና 'ዘገሊላ'/፪/ ከብካብ ኮነ/፪/
@EOTCW
እስመ ለዓለም
ዘበዳዊት ተነበየ፤ ወበዮሐንስ ጥምቀት ኃርየ፤ በቃና ዘገሊላ ማየ ወይነ ረሰየ፤ መዓዛ ቃልከ ይትወከፍ ጸሎትየ።
@EOTCW
አመላለስ፦
በቃና ዘገሊላ ማየ ወይነ ረሰየ፤
መዓዛ ቃልከ ይትወከፍ ጸሎትየ።
@EOTCW
ዕዝል፦
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤ ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
ምልጣን፦
እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤ ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
አመላለስ፦
እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አህዛብ፤
ወለማይኒ ረስዮ ወይነ
@EOTCW
አቡን፦
በ፭ ወእንዘ ሀለው ውስተ ከብካብ፤ ቅረቡ ኃቤሁ ኩሎሙ አርዳኢሁ ፤አንክርዎ ለማይ አእኰትዎ ለኢየሱስ፤ በእንተ ማይ ዘኮነ ወይን
@EOTCW
@EOTCW
ምልጣን፦
አንክርዎ ለማይ አንክርዎ አእኰትዎ ለኢየሱስ፤ አንክርዎ ማይ አንክርዎ
@EOTCW
አመላለስ፦
አንክርዎ ለማይ አንክርዎ፤
አእኰትዎ ለኢየሱስ አእኰትዎ ለኢየሱስ።
ዓራራይ፦
ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ ለመድኃኒነ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራጽዮን፤ ፆፍ ፀዓዳ፤ ንጉስ አንበሳ እምዘርዓ ዘመጽአ
@EOTCW
@EOTCW
ሰላም
ተሣሐልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ፤ ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ ወበእንተ ጥምቀቱ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
ምልጣን
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
ወረብ
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ/፪/
ማዕከለ ባሕር ቆመ ማዕከለ ባሕር/፪/
👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@EOTCW👈
👉@EOTCW👈
👉@EOTCW👈
🇪🇹👆👆👆👆🇪🇹
@EOTCW
#Join & share
# መልካም አገልግሎት
1 161
❤ በዚያንም ጊዜ ልብሳቸውን አውልቀው ወደ ወንዙ ወርደው ተጠመቁ ከውኃውም ሲወጡ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃልን ሰሙ "ምስክሮቼ በርቱ ጽኑ አሸናፊዎችም ሁኑ እኔ ከእንተ ጋር እኖራለሁና"። የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ወደ አንጾኪያ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ ጊዜ ሠራዊቱን ከከተማ ውጭ ትቶ ከሁለቱ ወዳጆቹ ከለውንድዮስና ከኒቆሮስ ጋር ገባ ንጉሥም በክብር ተቀብሎ ስለ ጦርነት ወሬ ስለ ሠራዊቱም ጠየቀው እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገረው።
❤ ከዚህም በኋላ ለአጵሎን ስለ መስገድ አወሳ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ንጉሡን ገሠጸው ዘለፈውም እንዲሁም ወዳጆቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ንጉሡን ረገሙት እርሱም ተቆጣ ለውንድዮስንና ኒቆሮስን ወደ ሚዶን አገር ወስደው በዚያ ያሠቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ። ኒቆሮስን የፋርስ አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ስለነበረ ከፋርስ ሰዎች የተነሣ ዲዮቅልጥያኖስ ፈርቷልና በዚያም ለውንድዮስና ኒቆሮስን በአሠቃዩአቸው ጊዜ በዚች ቀን ጥር ዐሥራ ሁለት የሰማዕትነት አክሊል ተቀበሉ።
❤ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎን ግን ከሞል በሚባል ታላቅ እንጨት ላይ አስተኝተው ቊጥራቸው መቶ ኅምሳ ሦስት በሆነ በረጃጅም የብረት ችንካሮች እንዲቸነክሩት አዘዘ። እግዚአብሔርም መልአኩን ቅዱስ ሚካልን ወደርሱ ልኮ በመከራው ሁሉ አጸናው። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና "የመረጥኩ ቴዎድሮስ ሆይ ሰላም ይሁንልህ ይህን ሁሉ መከራ ስለ ስሜ ታግሠሃልና ብፁዕ ነህ ይህን ከሀዲ ንጉሥ ታሳፍረው ዘንድ እሊህን ብረቶች ከሥጋህ ውስጥ አውጥቼ እንዳድንህ ትሻለህ" አለው። ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ጌታችንን "እንግዲህስ ስለ ከበረ ስምህ መሞት ይሻለኛል" አለው።
❤ ሁለተኛም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ወዳጄ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ እነሆ ሦስት አክሊላትን አዘጋጅቼልሃለሁ አንደኛው ስለ ድንግልናህ ሁለተኛው የዚህን ዓለም ክብር ትተህ መከራ ስለመቀበልህ ሦስተኛው ስለ ስሜ ደምህን ስለ አፈሰስክ ነው" አለው። "እኔም ቃል ኪዳንን ሰጠሁህ ስምህን ለሚጠራና መታሰቢያህን ለሚያደርግ በሁሉ ቦታ ከመከራው ሁሉ አድነው ዘንድ፤ ለድኆችም ምጽዋት የሰጠውን፤ ስለ አንተ በቤተ ክርስቲያንህንም የሠራውን ሁሉንም ኃጢአቱን ይቅር ብዬ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ"። ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን ከሰጠው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ ቴዎድሮስም ሦስቱን አክሊሎች ሲሰጡት ሦስትን መላእክት አየ በዚያንም ጊዜ የከበረች ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።
❤ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ከዐረፈ በኋላ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ለጣዖታት ያስግዱአቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ ሠራዊት የጣዖታቱን ካህናት ላከ ሁሉተኛም ንጉሥን የሚወድ ለአማልክት ይስገድ እያለ የሚዞር ዓዋጅ ነጋሪ አዘዘ። የቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሠራዊትም "የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ብለው ሁሉም ጮኹ ንጉሡም ሰምቶ ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ። ቊጥራቸውም ሁለት መቶ ኃምሳ እልፍ ሆነ ለሰማዕታት ራሶች ላይ አክሊልን የሚያኖሩ ብርሃናውያን መላክት አየሩን መሉት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስና በሰማዕታት ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ "ሰላም ለያቆብ ምንዙህ ዘኮነ በረከቱ ብዙኀ እምጠሉ ለሰማይ ወእምስፍሓ ለምድር፤ ዘአስተርአዮ እግዚአብሔር ገጸ በገጽ ወተናገሮ በምድረ ሎዛ፤ ወሰመየ ስሞ እስራኤል"። ትርጉም፦ከሰማይ ጠልና ከምድርም ስፋት ይልቅ በረከቱ የበዛ የኾነ እግዚአብሔር ፊት ለፊት የተገለጸለት (የታየው) በሎዛ ምድርም የተናገረው፤ ስሙንም እስራኤል ብሎ ለሰየመለት ቅምጥል ድልድል ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ሰላም ለከ ቴዎድሮስ ዐጽቅ። ዘብሔረ ምሥራቅ። በመንግሥተ ክርስቶስ ትትዓጸፍ አልባሰ መብረቅ። ዘኢተከድነ ቅንዋተ በአምሳለ ቈጽል ጽፉቅ። እምውስተ ሥጋከ ኢሀሎ ዕሩቅ"። ትርጉም፦ የምሥራቅ አገር ቅርንጫፍ ቴዎድሮስ ሰላምታ ላንተ ይገባል፤ በክርስቶስ መንግሥት የመብረቅ ልብሶችን ትጐናጸፍ ዘንድ፤ ጥቅጥቅ ባለ ቅጠል አምሳል በችንካሮች ያልተከደነ (ያልተወጋ) በሥጋኽ ውስጥ የተራቈተ (ባዶ ቦታ) የለም። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር12።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን። መዝ83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-12።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወምስካይነ አምላኩ ለያዕቆብ። ንዑ ትርአዩ ግብሮ ለእግዚአብሔር። ዘገብረ መንክረ በዲበ ምድር"። መዝ 45፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥1-17፣ ይሁ 1፥9-14 እና የሐዋ ሥራ 10፥34-39። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥44-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ።መልካም የቃና ዘገሊላና የቅዱስ ሚካኤል በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ጥር ፲፪ (12) ቀን።
❤ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ በሠርግ ቤት ተገኝቶ የመጀመርያውን ተአምር ላደረገበት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል እስራኤል ወደ ተባለ ቅዱስ ያዕቆብ ለተላከበት ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ ላዳነበት ለወራዊ በዓሉ፣ ለታላቁ ሰማዕት ለምሥራቅ ሰው ጽኑዕ ኃይለኛ ለሆነ ለቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍት በዓልና ለቅዱስ ይስሐቅም ልጅ ለቅዱስ ያዕቆብ ለልደቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱስ ቴዎድሮስ ማኅበር ለውንድዮስና ኒቆሮስንና ከሁለት መቶ ኃምሳ እልፍ ሠራዊት ሰማዕታት፣ ከቅዱሳን ከሰማዕቱ ከየዩልያኖስና ከመነኵሴው ከአባ ዳንኤል ከመታሰቢያቸው፣ ከቃሮስና ከሰሚኖስ ከመታሰቢያቸው፣ ከአባ ነካሮ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ፦ ሃለ ሉያ "እንዘ ስውር እምኔነ ይእዜሰ ክሡተ ኮነ ማየ ረሰየ ወይነ ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒነ በቃና ዘገሊላ ከብካብ ኮነ"፡፡ ትርጉም፦ ከእኛ ስውር ሲሆን ዛሬስ (ግን) ግልጥ ሆነ ውኃን ወይን አደረገ ምልክትንና ድንቅን አደረገ መድኃኒታችን በገሊላ ቃና ሠርግ ሆነ።
+ + +
❤ የዕለቱ እግ.ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ከብካብ ኮነ ከብካብ ኮነ ወኮነ እሙነ በቃና ዘገሊላ ተጸውዐ ኢየሱስ ውስተ ከብካብ ወሖረ ምስለ አርዳኢሁ። ትርጉም፦ ሠርግ ሆነ ሠርግ ሆነ በእውነት ሆነ በገሊላ ቃና ወደ ሠርግ ኢየሱስ ተጠራ ከደቀ መዛሙቱ ጋር ሄደ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችንና ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት የሠራው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሠሩ። ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና።
❤ በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ ሙሽራውን በጠራው ጊዜ "ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋኋ ዝቅተኛውን ያጠጣል። አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ" አለው። ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት። ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው በዚች ቀን እስራኤል ወደ ተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳወሰም ፈርቶ ሳለ አዳነው። ዮርዳኖስንም አሻግሮት ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ። እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብና ልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው ስለዚህም የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ፦ ይህም ታላቅ ተጋዳይ ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ከመንግሥት ወገን ነው። የአባቱ ስም ሲድራኮስ ይባላል ለንጉሥም የጭፍራ አለቃ ነው የእናቱም ስም በጥርቃ ይባላል ትርጓሜውም እመቤት ማለት ነው።
❤ ንጉሥ ኑማርያኖስም በጦርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ዮስጦስም በጦርነት ውስጥ ነበር መንግሥትም ያለ ንጉሥ ነበረች የቴዎድሮስ አባት ሲድራኮስና ፋሲለደስ ዲዮቅልጥያኖስ ነግሦ ሃይማኖቱን እስከ ካደ ድረስ የመንግሥቱን አስተዳደር ይመሩ ነበር። እርሱም ዲዮቅልጥያኖስ አስቀድሞ ከላይኛው ግብጽ የሆነ የዮስጦስ እኅት የንጉሥ ኑማርዮስ ልጅ ሚስት ሆነችውና አነገሠችው።
❤ ቅዱስ ቴዎድሮስ በአደገ ጊዜ በጦርነት ውስጥ ፈጽሞ ኃይለኛ ሆነ እርሱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሚሔድበት ጦርነት ሁሉ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ያሳድዳቸዋል የፋርስ ሰዎችም ቴዎድሮስ ወደ እናንተ መጣ ሲሏቸው ልባቸው ይሰበራል ይገዙለታልም ከእርሱም ወስጥ "ቴዎድሮስ የሮማውን አምላክ ነው" የሚሉ አሉ።
❤ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም በጦርነት ቦታ ቡናቢስ በሚባል ወንዝ አጠገብ ሳለ ስሙ ለውንድዮስ የሚባል ወዳጁም ሳለ ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት ራእይን አየ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ መሰላል አለ። በላዩም ታላቅ ዙፋን ጌታችን ተቀምጧል በዙሪያውም የብዙ ብዙ አእላፍ መላእክት ያመሰግናሉ ከበታቹም ታላቅ ከይሲ ነበር በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውም ቴዎድሮስም "አቤቱ አንተ ማነህ" አለ ጌታችንም "እኔ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ ለአንተም ስለ ስሜ ደምህ ይፈስ ዘንድ አለህ" አለው። በዚያንም ጊዜ ከቆሙት አንዱ ወሰደውና በእሳት ባሕር ሦስት ጊዜ አጠመቀው ሁለመናውም በመንበሩ ዙሪያ እንደቆሙት ሆነ። ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን ከወዳጄ ከለውንድዮስ መለየት አልሻም" አለው። ጌታም እንዲህ ብሎ መለሰለት እርሱ ብቻ አይደለም ለቊዝ ሠራዊት መኰንን የሆነ ኒቆሮስም ነው እንጂ።
❤ ከዚህም በኋላ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ አየ እነዚያ መላእክትም ለውንድዮስንና ኒቆሮስን አመጠቋቸው ከእሳት ባሕር ውስጥ አጠመቋቸውና እነርሱን ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሰጡት ከእንቅልፋም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለለውንድንስ ነገረው ፈጽሞ ደስ ብሏቸው እርስ በርሳቸው ተሳሳሙ።
❤ ከዚህም በኋላ የቊዝ የሠራዊት አለቃ ኒቆሮስ ወዳለበት የእግዚአብሔር ኃይል ተሸከመቻቸው እርሱም በደስታ ተቀብሎ አስቀድሞ እንደሚያውቃቸው አቅፎ ሳማቸው እነርሱም እንዳዩት ያንን ራእይ ነገራቸው እጅግም አደነቁ ኒቆሮስም ቴዎድሮስ በናድሌዎስን "እኔንና ወንድሜ ለወንድዮስን ለአንተ በእጅህ እንደሰጡን ወንድሜ ሆይ ዕወቅ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ በዚያን ጊዜ ወደ ሠራዊቶቻቸው መጡ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ደማቸውን ሊአፈሱ ተስማሙ። ከንጉሠ ቊዝ እንዴት ዕርቅ እንዳደረገ ሊጠይቀው ያን ጊዜ ንጉሥ ወደ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ላከ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ ጣዖታትን በአመለከ ጊዜ ስለዚህ የቊዝ ሰዎች እጅግ ደስ ብሏቸወልና።
❤ የከበረ ቴዎድሮስ በናድልዮስም ሠራዊቱን "ነፍሱን ከሰይፍ ሊያድን የሚወድ ወደ ፈለገው ይሒድ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ግን መጋደልን የሚሻ ከእኛ ጋር ይኑር" አላቸው። ሁሉም በታላቅ ድምፅ "አንተ የምትሞትበትን ሞት እኛ ካንተ ጋራ እንሞታለን አምላክህም አምላካችን ነው" ብለው ጮኹ የተመሰገነ ቴዎድሮስም ዳግመኛ "ነገራችሁ እውነት ከሆነ ሁላችሁም ወደዚህ ወንዝ ወርዳችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሦስት ጊዜ ተጠመቁ" አላቸው።
1 161
ልክ እንደ መላዕክት ምድር ላይ #ነጫጭ የለበሱ! በገናንም እንደ ዳዊት የያዙ ፣ ከበሮንም የያዙ ፣ #የክርስቶስንም መስቀል በአንገታቸዉ ያሰሩ ሰዎችን ካየህ #ብሮ እነዛ ሰዎች #ኦርቶዶክሳዊያን ናቸዉ ማለት ነዉ ። ❤☦️
እንኳን አደረሳቹ የምወዳቹ #የተዋህዶ ልጆች🙌
1 161
Repost from ሰዋስው ☘☘☘☘
ሰዋስው:
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
ሥርዓተ ማኅሌት ዘጥምቀት
💧💧💧💧💧💧💧💦💦💦💦💦
የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
@EOTCW
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።
@EOTCW
@EOTCW
✨መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአእዛኒክሙ አናቅጸ ጸሎት ሠናይ፤ ምሥጢራተ ሰሚዕ ሥላሴ ዘይተልዎ ርእይ፤ በአብትረ ያዕቆብ በርሀ ሥላሴክሙ ፀሐይ፤ ወተመሰሉ ሰብአ ዓይን አባግዓ ላባ ወማይ፤ ለኀበ አባግዕ ዘዮም ወጥምቀት ዓባይ።
@EOTCW
@EOTCW
🌱ዚቅ
መኑ ይወርድ ውስተ ቀላይ፤ ክርስቶስ ውእቱ ዘወጽአ እማይ፤ እመንፈስ ቅዱስ ሠለስቲሆሙ፤ እለ አሐዱ እሙንቱ ፫ቲሆሙ፤ እለ ይከውኑ ሰማዕተ ፫ቲሆሙ፤ ለሊሁ ወረደ መንፈስ ቅዱስ፤ ከመ ይቀድስ ማያተ፤ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ ጸጋ ወጽድቅሰ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ኮነ።
@EOTCW
@EOTCW
💎ነግሥ
ሰላም ለማየ ዮርዳኖስ ዮሐንስ ዘአተቦ፤ መንፈስ ቅዱስ ከመ አጥበቦ፤ ሶበ መጽአ ቃል እምሰማይ ለተናብቦ፤ ነድ ለማየ ባሕር ከበቦ፤ ማይ ኀበ የሐውር ጸበቦ።
@EOTCW
🌱ዚቅ
ርእዩከ ማያት እግዚኦ፤ ርእዩከ ማያት ወፈርሑ፤ ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምጸ ማያቲሆሙ።
@EOTCW
❣❣ወረብ
ርእዩከ 'እግዚኦ'/፪/ ርእዩከ ማያት/፪/
'ደንገፁ'/፪/ ቀላያተ ማያት ደንገፁ ቀላያተ ማያት/፪/
@EOTCW
@EOTCW
💎ትምህርተ ኅቡዓት
እምሰማያት እምኀበ አብ አይኅዓ፤ በሕማማተ ሥጋሁ ቤዘወነ፤ ወደሞ ክቡረ መንፈሰ ሕይወት፤ ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ፤ ወማየ መንጽሔ ዚአነ።
@EOTCW
@EOTCW
❣❣ወረብ
'ወደሞ ክቡረ'/፪/ መንፈሰ ሕይወት ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ/፪/
ወማየ መንጽሔ ዚአነ/፬/
@EOTCW
❄️❄️አንገርጋሪ
ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ፤ ወለደነ ዳግመ እማይ ወእመንፈስ ቅዱስ፤ እሙነ ኮነ ለፀሐየ ጽድቅ አስተርእዮቱ፤ አማን፤ መንክር ስብሐተ ጥምቀቱ።
🔹አመላለስ፦
አማን በአማን መንክር ፤
መንክር ስብሐተ ጥምቀቱ።
@EOTCW
❣❣ወረብ
ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ ክርስቶስ ተወልደ/፪/
'ወለደነ ዳግመ'/፪/ እመንፈስ ቅዱስ ወማይ/፪/
@EOTCW
💠እስመ ለዓለም
ሖረ ኢየሱስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ፤ ከመ ያጥምቆ በፈለገ ዮርዳኖስ፤ ወወጺኦ እማይ ተርኅወ ሰማይ፤ መጽአ ቃል እምደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ፤ ዘአፈቅር ሎቱ ስምዕዎ።
@EOTCW
🔹አመላለስ፦
መጽአ ቃል እምደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ፤
ዘአፈቅር ሎቱ ስምዕዎ።(4)
❣❣ወረብ
ሖረ ኢየሱስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ/፪/
ከመ ያጥምቆ በፈለገ ፈለገ ዮርዳኖስ/፪/
@EOTCW
💎ዕዝል
ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ቃል፤ ቃለ እግዚአብሔር፤ ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ፤ ወተገሠ በሥጋ፤ መንፈስ ዘኢይትገሠሥ ወዘኢይትለከፍ፤ ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት፤ ወገብረ መንጦላዕተ ሥጋ ሰብእ መዋቲ፤ ወረደ ዲበ ምድር፤ ወአንሶሰወ ውስተ ዓለም፤ በበህቅ ልህቀ በ፴ ክረምት፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ።
@EOTCW
@EOTCW
❄️ምልጣን
ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት፤ ወገብረ መንጦላዕተ ሥጋ ሰብእ መዋቲ።
@EOTCW
🔹አመላለስ
ወገብረ መንጦላዕተ/፪/
ሥጋ ሰብእ መዋቲ/፪/
@EOTCW
💠አቡን
በ፭: እስመ ሰምዓ ይቀውም ሎቱ አብ ናዛዚ በርእየተ ርግብ ውስተ ምጥማቃት እንዘ ይብል፤ ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር፤ ዘኪያሁ ሠምርኩ ይቤ፤ ወበይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ መድኅን እምቅድስት ድንግል፤ ኪያሃ ሠምረ አብ በሥጋ ምጽአቶ።
@EOTCW
@EOTCW
🔸ሰላም
ተሣሐልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ፤ ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ ወበእንተ ጥምቀቱ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
❄️ምልጣን
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።
@EOTCW
@EOTCW
❣❣ወረብ
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ/፪/
ማዕከለ ባሕር ቆመ ማዕከለ ባሕር/፪/
https://t.me/Eotcw
#Join & share
