uk
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Відкрити в Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Показати більше
1 161
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
1.14 KB

2/4/2015 ዓ.ም (፪/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ። ወእነግር ኲሉ ስብሐቲከ። እትፌሣሕ ወእትሐሠይ ብከ። መዝ. 9፥1 🕯 ትርጉም አቤቱ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ። ተኣምራትህንም ሁሉ እነግራለሁ። ባንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትንም አደርጋለሁ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

photo content
+2

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፪ 2 ቀን። ❤ እንኳን ለሠለስቱ ደቂቅ ለአናንያ፣ ለአዛርያና ለሚሳኤል እግዚአብሔር ኃይል ላደረገላቸው ለመታሰቢያ በዓላቸው፣ ለቅዱስ አውክያኖስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከላይኛው ግብጽ ከሚኖሩ ሰዎች ወገን ለሆነ ለቅዱስ አባት ለአባ ሖር ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱስ ፋሲለደስ አገልጋዮቹና ዘመዶቹ ከሆኑ ከሰባት ሺህ ሠላሳ ሦስት ከሆኑ ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው፣ ከአብላፍታን፣ ከዐረብ ወገን ከሆነ ከሰማዕት አንበስና ከመነኰስ ናትናኤል ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ ምልጣን ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ወረደ ገብርኤል እምሰማያት ወዘበጠ ለነበልባለ እሳት ወአድኃኖሙ ለሰማዕት እለ ተወከሉ በክርስቶስ እምእሳት ወጽኡ ወበሰላም አተዉ"። ትርጉም፦ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደ ነበልባሉን መታው (አጠፍው) በክርስቶስ የታመኑትን ሰማዕታት (ሠለስቱ ደቂቅን) አዳናቸው ከእሳት ውስጥ በሰላም ወተው ገቡ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ የዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፪ "ይቤሉ እስራኤል ኢርኢነ ወኢሰማእነ ዘዕውሩ ተወልደ ወተከሥተ አዕይንቲሁ በሰንበት ለእመ እምኀበ እግዚአብሔር ኢኮነ እመ ኢገብረ ዘንተ ወይቤልዎ ምንተ ትብል በእንተ ዘአሕየወከ ዘአሕየወኒ ይቤለኒ ኢንግር ወእምዝ ዘየአኪ ኢይርከብከ። ትርጉም፦ እስራኤል አላየንም አልሰማንም አሉ፣ ዕውር ሆኖ የተወለደው በሰንበት አይኖቹ ተከፈቱ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ካልሆነ በቀር ይህን ማድረግ ይችላል አሉ፣ ስላዳነህ ምን ትላለህ አሉት፣ ከዚህ የከፋ እንዳያገኝህ ይህን ለማንም አትናገር አለኝ አላቸው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ ሠለስቱ ደቂቅ፦ በዚች ቀን ናቡከደነፆር ከአባታቸው ጋር ለማረካቸው ሦስቱ ለሆኑ ለይሁዳ ንጉሥ ለኢዮአቄም ልጆች እግዚአብሔር ኃልን አደረገላቸው። እሊህም አናንያ አዛርያ ሚሳኤል ናቸው በቤቱም ውስጥ አሳድጎ በባቢሎን አገሮች ውስጥ ሾማቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ናቡከደነፆር የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉትን ሁሉ በዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ እሊህ ቅዱሳን ግን መስገድን እምቢ አሉ በወነጀሏቸውም ጊዜ ከቀድሞው ሰባት እጅ ወደ አነደዱት የእሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሯአቸው ዘንድ ንጉሥ አዘዘ። በእሳቱ መካከል ረጅም ጸሎትን ጸለዩ የእግዚአብሔር መልአክም ቅዱስ ገብኤልም ወርዶ እንደ ቀዘቀዘ ነፋስ አደረገው። ❤ ንጉሥ ናቡከደነፆርም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ አደነቀ ለእግዚአብሔርም በመገዛት ሰገደ እነርሱንም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ አወጣቸው እጅግም አከበራቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ቅዱሳን በሠለስቱ ደቂቅ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅዱስ አውክያኖስ፦ እርሱም ሃይማኖቱን ጠብቆ ሰዎች አባለ ዘሩን እስከ ቆረጡት ድረስ ተጋድሎውን የፈጸመ ነው እግዚአብሔርም አመሰገነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውክያኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ሖር፦ ይህም አባት ደግነት ያለው መነኰስ በመሆን ጽኑዕ ገድልን ተጋደለ በአምልኮቱና በተጋድሎው ከቅዱሳን ሁሉ ተለይቶ በብዙዎች ላይ ከፍ ከፍ አለ ለብቻ መኖርን ስለወደደ ወደ በረሀ ወጥቶ በገድል ተጠምዶ ብዙ ዘመናት ኖረ። የበጎ ሥራ ጠላት የሆነ ሰይጣንም ቀንቶበት በግልጥ ታየውና "በበረሀ ውስጥ ግን አንተ ድል ትነሣናለህ በዚህ ሰው የለምና ጽኑ ኃይለኛ ከሆንክ ወደ እስክንድርያ ከተማ ና" ብሎ ተናገረው። ❤ አባ ሖርም ይህን በሰማ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኃይል ተማምኖ ወደ እስክንድርያ ከተማ ሒዶ ለእሥረኞችና ለችግረኞች ደካሞች ውኃ የሚቀዳ ሆነ በአንዲት ዕለት ሦስት ፈረሶች በከተማው ውስጥ እየዘለሉ ሲያልፉ አንዱ ፈረስ አንዱን ሕፃን ረገጠውና ወዲያውኑ ሞተ ሰይጣንም በሰዎች ልብ አደረና "ይህን ሕፃን ያለዚህ አረጋዊ መነኵሴ የገደለው የለም" ብለው አሰቡ አባ ሖርም መጣና ሕፃኑን አንሥቶ ታቀፈው በልቡም በመጸለይ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር ማለደ በመስቀል ምልክትም በላዩ አማተበ የሕፃኑም ነፍስ ተመለሰች ድኖም ተነሣ ለአባቱም ሰጠው ወደ ከተማ ውጭ ሸሽቶ በመሔድ ወደ በዓቱ ገባ ፈልገውም አላገኙትም ጽድቅንና ትሩፋትንም በመሥራት ብዙ ዘመናት በገድል ተጠምዶ ኖረ። ❤ የሚሞትበት ጊዜ ሲቀርብ ብዙዎች ቅዱሳንን ሲጠሩት አያቸው እጅግም ደስ አለው ልጆቹንም ሰብስቦ በምንኵስና ሥርዓት ጸንተው ትሩፋትን እንዲሠሩ አዘዛቸው ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እርሱ እንደሚሔድ ነገራቸው እርሱም እጅግ አዘኑ ጥቂት ቀንም ታሞ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ሖር ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ2 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለሖር በምንሀብ ፍቱን። እስከ ተለዓለ ጥቀ ላዕለ ብዙኃን። ሶበ ተንሥኡ ላዕሌሁ በምክረ ጸላኢ ሰይጣን። ከመ ኢቀተሎ እስከ አእመሩ አብዳን። በኃይለ ጸሎቱ አንሥኦ ለምውት ሕፃን"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 2። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ። ወእነግር ኲሎ ስብሐቲከ። እትፌሣሕ ወእትሐሠይ ብከ"። መዝ 9፥1-2 ወይም መዝ 65፥12-13። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 6፥35-39 ወይም ማቴ 19፥10-15። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ደቂቀ እጓለ እምሕያው እስከ ማዕዜኑ ታከብዱ ልበክሙ። ለምንት ታፈቅሩ ከንቶ ወተኀሡ ሐሰተ። አእምሩ ከመ ተሰብሐ እግዚአብሔር በጻድቁ"። መዝ 4፥2-3 የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 2፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 5፥1-6፣ የሐዋ ሥራ 5፥31-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

መዝሙር ዘመፃ በ፪ ብ ይቤሉ እስራኤል @EOTCW

መዝሙር በ2 ሃሌታ- ይቤሉ ፳ኤል፤ኢርኢነ ወኢሰማዕነ ዘዕውሩ ተወልደ፤ወተከስተ አዕይንቲሁ በሰንበት፤ለእመ እምኀበ እግዚአብሔር ኢኮነ፤እመ ኢገብረ ዘንተ፤ወይቤልዎ ምንተ ትብል በእንተ ዘአሕየወከ፤ማ፦ዘአሕየወኒ ይቤለኒ ኢትንግር፤ወእምዝ ዘየዓኪ ኢይርከብከ @EOTCW https://t.me/Eotcw     # Join & share #

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ! ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ. 4:25-33 "ወይቤሎሙ አማን እብለክሙ"- "ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ በኤልያስ ዘመን ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ሰማይ ተዘግቶ ሳለ በምድር ሁሉ ብርቱ ራብ በነበረ ጊዜ፥ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ፤ ኤልያስም በሲዶና አገር ወዳለች ወደ ሰራፕታ ወደ አንዲት መበለት እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱ አልተላከም። በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም። በምኵራብም የነበሩ ሁሉ ይህን ሰምተው ቍጣ ሞላባቸው፥ ተነሥተውም ከከተማ ወደ ውጭ አወጡት፥ይጥሉትም ዘንድ ከተማቸው ተሠርታባት ወደ ነበረች ወደ ተራራው አፋፍ ወሰዱት፤ እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ። ወደ ገሊላ ከተማም ወደ ቅፍርናሆም ወረደ። በሰንበትም ያስተምራቸው ነበር፤ ቃሉ በሥልጣን ነበርና በትምህርቱ ተገረሙ።በምኵራብም የርኵስ ጋኔን መንፈስ ያደረበት ሰው ነበረ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.26 KB

1/4/2015 ዓ.ም (/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ወገሠጸ ነገሥት በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ፡፡ መዝ. 104፥14 🕯 ትርጉም የቀባኋቸውን አትዳስሱ። በነቢያቴም ክፉ አታድርጉ። ብሎ ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ 9:46-56 "ወሐለዩ በበይናቲሆሙ እንዘ ይብሉ" - "ከነርሱም፡ማን፡እንዲበልጥ፡ክርክር፡ተነሣባቸው። ኢየሱስም፡የልባቸውን፡ዐሳብ፡ዐውቆ፡ሕፃንን፡ያዘ፤በአጠገቡም፡አቁሞ፦ ማንም፡ይህን፡ሕፃን፡በስሜ፡የሚቀበል፡እኔን፡ይቀበላል፤ የሚቀበለኝም፡ሁሉ፡የላከኝን፡ይቀበላል፤ከሁላችሁ፡የሚያንስ፡እርሱ፡ታላቅ፡ነውና፥አላቸው። ዮሐንስም፡መልሶ፦አቤቱ፥አንድ፡ሰው፡በስምህ፡አጋንንትን፡ሲያወጣ፡አየነው፥ከእኛ፡ጋራም፡ስለማይከተል፡ከለከልነው፡አለው። ኢየሱስ፡ግን፦ የማይቃወማችሁ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ነውና፥ አትከልክሉት፡አለው። የሚወጣበትም፡ወራት፡በቀረበ፡ጊዜ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ለመሄድ፡ፊቱን፡አቀና፥ በፊቱም፡መልክተኛዎችን፡ሰደደ።ሄደውም፡ሊያሰናዱለት፡ወደ፡አንድ፡ወደሳምራውያን፡መንደር፡ገቡ፤ ፊቱም፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡እንደሚሄድ፡ስለ፡ነበር፥አልተቀበሉትም። ደቀ፡መዛሙርቱም፡ያዕቆብና፡ዮሐንስ፡አይተው፦ጌታ፡ሆይ፥ኤልያስ፡ደግሞ፡እንዳደረገ፡እሳት፡ከሰማይ፡ወርዶ፡ያጥፋቸው፡እንል፡ዘንድ፡ትወዳለህን፧አሉት። እርሱ፡ግን፡ዘወር፡ብሎ፡ገሠጻቸውና፦ምን፡ዐይነት፡መንፈስ፡እንደ፡ሆነላችሁ፡አታውቁም፤ የሰው፡ልጅ፡የሰውን፡ነፍስ፡ሊያድን፡እንጂ፡ሊያጠፋ፡አልመጣም፡አለ።ወደ፡ሌላ፡መንደርም፡ሄዱ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.21 KB

1/4/2015 ዓ.ም (፩/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ። ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ። ወቀፃዕክዋ በጾም ለነፍስየ። መዝ. 68፥9 🕯 ትርጉም የቤትህ ቅንአት በልታኛለችና። የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቋልና። ፍሴን በጾም አስመረርኋት። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

photo content
+1

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለኤልያስ ነቢይ ቴስብያዊ ኮሬባዊ ታቦራዊ ሰማየ ዘለጐመ ወከልአ ዝናመ፤ ቃለ ጸሎቱ ዘተሰምዐ ውስተ ዕዝኑ ለአዶናይ ወአውረደ እሳት እምሰማይ እስከ በልዖ ለማይ፤ ዘዐደወ ብሔረ ተድላ ተጽኢኖ ዘእሳት ሠረገላ። ትርጉም፦ ቴስቢያዊ (የቴስቢያ ሰው)፤ ኮሬባዊ (ወደ ኮሬብ ተራራ የወጣ)፤ ታቦራዊ (በታቦር ተራራ የተገኘ) ፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን የለጐመ ለኾነ፤ የጸሎቱ ቃልም በአዶናይ ዦሮ ውስጥ ለተሰማ፤ ውሃውን እስካበላ ደርሶ እሳትን ከሰማይ ያወረደ ለኾነ፤ በእሳት ሠረገላ ተጭኖ ወደ ተድላ ደስታ ቦታ ለገባ ለነቢዩ ለኤልያስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ በአንዲትም ዕለት መሥዋዕት አዘጋጅቶ እርሱ ሲቀድስ ቁመው የነበሩ ሕዝብ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር በቅዳሴ ቊርባን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስም አልገሠጻቸውም የእግዚአብሔርም መልአክ አይቶ ወደታች ሊወረውረው ወዶ ከመካከላቸው አንሥቶ ያዘው ግን ታግሦ ተወው እርሱ እነርሱን መገሠጽ አፍሮ አክብሮአቸዋልና። ❤ የከሀዲው መርቅያን ዘመን በተፈጸመ ጊዜ ወደ ፍልስጥዔም ምድር ተመልሶ አብያተ ክርስቲያናትን አጠናከረ ከግብጻዊ አባ ኢሳይያስም ጋር ተገናኘ ዜናውም በንጉሥ ዘይኑን ዘንድ በተሰማ ጊዜ ንጉሡም ሊያየው ወደደ እርሱ ግን አልወደደሜ ከዚህ ከኃላፊው ክብር እጅግ ይሸሽ ነበርና። ❤ ከዚህም በኋላ ጋውር ከሚባል አገር ዳርቻ ደርሶ በዚያ ተቀመጠ የተመሰገነ የሰማዕታት ፍጻሜ የሆነ የሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስ በዓሉ በደረሰ ጊዜ የቊርባንን ቅዳሴ ሠራ ቅዱስ ጴጥሮስም ተገለጸለትና "ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ ትመጣ ዘንድ ይጠራሃል" አለው። ከዚችም ቀን ወዲህ የዕረፍቱ ጊዜ እንደ ደረሰ አውቆ ሕዝቡን ጠራቸውና በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኋላ እጆቹን ዘርግቶ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጴጥሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑረሰ ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ዮሐንስ፦ ይህም አባት ለእስክድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ሠለሳኛ ነው። ይህም የከበረ ቀሲስ የሆነ የገምኑደመ ሰው ነው በዘመኑም የቅዱሳን ሰማዕታት የሰርጊስና የባኮስ ቤተ ክርስቲያናቸው ተሠራች ዳግመኛም የአቡቂርና የዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን በምስር መሰብሰቢያ ቅጽር አጠገብ ተሠራች ያነጻቸውሜ ስሙ እንድርያስ የሚባል እግዚአብሔርን የሚፈራ ያዕቆባዊ አንድ የግብጽ ሰው ነው። እርሱም ለመርዋን ልጅ ለገዢው ንጉሥ አብደል ጸሐፊው ነው። ❤ ይህም አባ ዮሐንስ የወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስን ቤተ ክርስቲያን በእስክንድርያ አገር በታወቀ ቃምስ በሚባል ቦታ የሠራ ነው። በዚህ በንጉሥ አብደል ዘመንም ሦስት ዓመት ያህል ጽኑ ረኃብ ሆነ ይህም አባት ለድኆች ለጦም አዳሪዎችና ለችግረኞች የሚያስብ ሆነ በየሳምንቱም አራት ጊዜ ወርቅና ብር እንጀራም ይሰጣቸዋል አብዝቶ የሚራራ መመጽወትን የሚወድ በጎ ሥራዎችን የሚሠራ ነውና። በዘመኑም ንጉሥ ይዜድ ሙቶ በርሱ ፈንታ መርዋን ነገሠ ይህም አባት በቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዘጠኝ ዓመት ኖረ በዚች ቀንም በሰላምም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሐንስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ አትናቴዎስ፦ እርሱም ጳውሎስ የተባለ የቂስ መክረም ልጅ የከሊል ልጅ ነው። እርሱም ለእስክንድርያ አገር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ ስድስተኛ ነው። ምንጭ፦ የታኅሣሥ1 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለናቡቴ በፍቅረ አሐቲ ዐፀዱ። ለንጉሥ አክዓብ ሶበ ኢተአዘዘ ለፈቃዱ። እስከ አቅተሎ በግፍዕ እስመ ከመዝ ልማዱ። አጽርዓት ግፍዐ ደሙ በፍትሐ ፈጣሪ አሐዱ። መንግሥተ ምልክና እምኵሉ ትዝምዱ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ1። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ። ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ። ወቀጻዕክዎ በጾም ለነፍስየ"። መዝ68፥9-10። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ9፥47-56። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወገሠፀ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢትሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ 104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 11፥1-13፣ ያዕ 5፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥19-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 4፥25-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ የቅዱስ ኤልያስ የልደት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ የተባረከ የታኅሣሥ ወር የቀኑ ሰዓት ዘጠኝ ሲሆን ከእንግዲህም ይጨምራል። ❤ ታኅሣሥ ፩ (1) ቀን ❤ እንኳን ለርእሰ ባሕታዊ ለታላቁ ነቢይ ለቴስብያዊ ለቅዱስ ኤልያስ በእስራኤል ፊት ለተገለጠበት ለልደቱ ዓመታዊ በዓል፣ ለእስራኤላዊ ለቅዱስ ናቡቴ ለዕረፍት በዓል፣ ለጋዛ አገር ኤጲስቆጶስ ለቅዱስ አባት ለአባ ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓል፣ ለእስክንድርያ አገር ሠላሳኛ ሊቀ ጳጳሳት ለቅዱስ አባት ለአባ ዮሐንስና ሰባ ስድስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ለአባ አትናቴዎስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ጴጥሮስ፣ ከያዕቆብ፣ ከመነኰስ ኤልያስ ከንጉሥ ሰሎሞን እናት ከቤርሳቤህ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ጸለየ ጸሎተ ወአውረደ ዝናማተ ኤልያስ ክቡር ቴስብያዊ መስዋዕተ ስብሐት ለአምላኩ አዕረገ በሠረገላ ዘእሳት ሰማያተ ዓርገ"። *ጸለየ ጸሎተ ወአውረደ ዝናማተ ኤልያስ ክቡር ቴስብያዊ መስዋዕተ ስብሐት ለአምላኩ አዕረገ በሠረገላ ዘእሳት ሰማያተ ዓርገ። ትርጉም፦ ቅዱስ ኤልያስ ቴስብያዊ ጸሎቱን ጸለየ ዝናምን አዘነመ (አወረደ) ለአምላኩ የምስጋና መስዋዕትን አሳረገ በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ዐረገ (ወጣ)። ሊቁ ቅዱስ በድጓው ያሬድ። + + + ❤ ነቢዩ ቅዱስ ኤልያስ፦ ይህ ቀናኢ ኤልያስ ከሌዊ ወገን የሆነ የአባቱ ስም ኢያስኑዩ የእናቱም ስሟ ቶና ነው። ስለርሱም እንዲህ ተነገረ በተወለደ ጊዜ ብርሃንን የለበሱ አራት ሰዎች ሲሰግዱለትና ሕፃናት በሚጠቀለሉበት ጨርቅ ፈንታ በእሳት ሲጠቀለሉበት አባቱ አየ። እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ይህን ለካህናቱ ነገራቸው እነርሱም "ማደሪያው በብርሃን ውስጥ ይሆን በቃሉም የሚቆርጥ ይሆን ወይም እስራኤልን በሰይፍና በእሳት እየቀጣ ይገዛቸው ይሆን" ተባባሉ። ❤ በእስራኤለሰ ንጉሥ በአክዓብና በሚስቱ በኤልዛቤል በልጁም በአካዝያስም ዘመን ያደረገው የተአምራቱ ዜና በመጽሐፈ ነገሥት ተጽፎአል። ወደ ሰማይ ያረገበት ዜናው ግን በጥር ወር በስድስት ቀን ተጽፎአል። በኋላ ጊዜም ስለሚሆነው ሞቱ ራእይን በሕይወቱ ያየ ዮሐንስ ከኄኖክ ጋር እንደሚመጣና ሐሳዊ መሲሕን እንደሚቃወሙት ተአምራትንም እንደሚያደርጉ ተናግአል። "ሁለቱ የዘይት ዕንጨቶች በምድር ላይም የተሾሙ በእግዚአብሔር ፊት የማያበሩ ሁለት መብራቶች ናቸው" አለ። ❤ "ከጠላቶቻቸው ወገን ሊጣላቸው የወደደውን እሳት ከአፋቸው ወጥታ ታጠፋቸውዋለች የሚጣሏቸው እንዲህ ይጠፋሉ። ትንቢት በሚናገሩበት ወራት በምድር ላይ ዝናም እንዳይዘንም ይዘጓት ዘንድ በሰማይ ላይ ሥልጣን አላቸውና ዳግመኛም ደምን ያደርጉት ዘንድ በውኃው ላይ ሥልጣን አላቸው የፈለጉትን ያህል በመቅሠፍቱ ሁሉ ምድርን ያስጨንቋታል። ምስክርነታቸውንና ትንቢታቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከባሕር የወጣው አውሬ ከሳቸው ጋር ይጣላል ድል ነስቶም ይገድላቸዋል። አስከሬናቸውም ፍጥሞ በምትባል በታላቂቱ አገር ያስጥለዋል ይችውም በምስጢር ሰዶም ግብጽ የተባለች ጌታቸው የተሰቀለባት ናት። አስከሬናቸውንም ሕዝብና አሕዛብ በአገርም ያሉ ነገዶች ሦስት ቀን ተኩል ያዩታል አስከሬናቸውንም በመቃብር ይቀብሩት ዘንድ አያሰናብቱም። ❤ በምድር ላይ የሚኖሩ ሰዎች በእነርሱ ሞት ደስ ይላቸዋል እርስበርሳቸውም በደስታ እጅ መንሻ ይሰጣጣሉ እሊህ ሁለቱ ነቢያት በምድር በሚኖሩ ሰዎች መከራ አጽንተውባቸዋልና ይላሉ። ከሦስት ቀን ተኩል በኋላ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሕይወት መንፈስ መጥታ ታድርባቸዋለች ተነሥተውም በእግራቸው ይቆማሉ በሚያዩዋቸው ላይም ጽኑ ፍርሀት ይሆናል። ከወደ ሰማይ ቃል መጥቶ ወደዚህ ውጡ ይላቸዋል ከዚህ በኋላ ጠላቶቻቸው እያዩአቸው በደመና ያርጋሉ። በዚያችም ሰዓት ጽኑ መነዋወጥ ይሆናል የዚችም አገር ዐሥረኛ እጅዋ ይጠፋል በዚያም መነዋወጥ ሰባት ሽህ ሰዎች ይሞታሉ የቀሩት ግን ደንግጠው የሰማይ አምላክ ፈጽመው ያመሰግናሉ"። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ነቢይ በቅዱስ ኤልያስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ እስራኤላዊው ቅዱስ ናቡቴ፦ ይህ ናብቴ በሰማርያው ንጉሥ በክዓብ ቤት አጠገብ የወይን አትክልት ቦታ ነበረው። አክዓብም ናብቴን ለቤቱ ቅርብ ነውና "የተክል ቦታ ይሆነኝ ዘንድ ይህን የወይን ቦታህን ስጠኝ ከሱ የሚሻል ሌላ የወይን ቦታ እሰጥሃለሁ ዋጋውንም ትሻ እንደሆነ የዚህን የወይን ቦታህን ሽያጭ ወርቅ እሰጥሃለሁ የተክል ቦታ ይሁነኝ" አለው። ናብቴም አክዓብን "የአባቶችን ርስት እሰጥህ ዘንድ እንዲህ ያለ ነገር እግዚአብሔር አያምጣብኝ" አለው። ❤ አክዓብም አዝኖ ሔደ ፊቱንም ተከናንቦ በመኝታው ተኛ እህልም አልበላም። ሚስቱ ኤልዛቤልም ወደርሱ ገብታ "እህል የማትበላ ምን ሆንክ የሚያሳዝህስ ምንድን ነው?" አለችው። "የኢይዝራኤል ሰው ናብቴን የወይንህን ቦታ በዋጋ ሽጥልኝ ትወድም እንደሆነ ስለርሱ ፈንታ ሌላ ቦታ እሰጥሃለሁ ብዬ ብናገረው የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም ብሎኛልና ስለዚህ ነው ያዘንሁት" አላት። ሚስቱ ኤልዛቤልም "ዛሬ እንዲህ የምታደርግ አንተ የእስራኤል ንጉሣቸው ነህን አሁንም ተነሥተህ እህል ብላ ራስህንም አፅና ልቡናህም ደስ ይበለው የኢይዝራኤል ሰው የናብቴ ቦታ እኔ እሰጥሃለሁ" አለችው። ❤ በአክዓብ ስም ደብዳቤ ጽፋ በማኅተመም አትማ ያቺን ደብዳቤ ከናቡቴ ጋር ወደሚኖሩ ወደዚያ አገር አለቆችና ወደዚያች አገር ሽማግሌዎች ላከቻት። የዚያችም ደብዳቤ ቃል እንዲህ የሚል ነው "ጾምን ጹሙ ናቡቴንም በሕዝቡ ፊት አስቀምጡት የሐሰት ምስክሮችንም ሁለት ሰዎችን አስነሡበት እግዚአብሔርን ሰደብከው ንጉሥንም ረገምከው ብለው ይመስክሩበት ከከተማም ወደ ውጭ አውጥታችሁ በደንጊያ ውገሩትና ይሙት" የሚል ነበር። እንዲህም በግፍ ኤልዛቤል አስገደለችው ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ናቡቴ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ የጋዛ አገር ኤጲስቆጶስ አባ ጴጥሮስ፦ ይህም ሮሃ ከሚባል አገር ክብር ካላቸው ወገን ነው ይሾመውም ዘንድ ወላጆቹ ለንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሰጡት እርሱ ግን ሹመትንና ክብርን ይጠላ ነበር በንጉሡም አዳራሽ ውስጥ በጾም በጸሎት በሰጊድ ተጠምዶ ኖረ ከርሱም ጋር የፋርስ አገር ሰማዕታት ሥጋ አብሮት አለ በዚያም ጊዜ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ከገዳማት ወደ አንዱ ገዳም ሔዶ መነኰሰና ጽኑ ተጋድሎንም ተጋደለ የቅድስናውና የተጋድሎው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ፈቃዱ ወስደው ጋዛ በምትባል አገር በአውራጃዋም ሁሉ ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። ስለርሱም የቊርባንን ቅዳሴ በሚቀድስ ጊዜ ኅብስቱን ሲፈትት ጻሕሉን እስቲመላ ድረስ ብዙ ደም እንደሚፈስ ተነገረ። የቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድን ሥጋ ወደርሱ ወስዶ ከኢየሩሳሌም ገዳማት በአንዱ ገዳም ኖረ በከሀዲው መርቅያን ዘመንም ወደ ግብጽ አገር ሸሸ የቅዱስ ያዕቆብም ሥጋ ከእርሱ ጋር አብሮ ነበር በዚያም ጥቂት ጊዜ ኖረ።

photo content

ሌሎች አስተማሪ እና አዳዲስ ጥያቄዎችን ማግኘት ከፈለጉ ከላይ ያለውን forwarde 👆 በመንካት ወደ ቻናላችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን 215. ከሙሴ ስር ጽላቱ በተሰበረ ጊዜ እግዚአብሔር ምን አለው??
Anonymous voting

photo content