Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Відкрити в Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Показати більше3 587
Підписники
Немає даних24 години
+27 днів
+2430 день
Архів дописів
የተጫራቾች ምዝገባ ለማከናወን የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር. ECWCT/EOI/PG-0059/2015
---------------
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ለ 2015 በጀት ዓመት በሚከተሉት የግዥ መደቦች የተሰማሩ ዕቃ አቅራቢ እና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን በአቅራቢ ዝርዝር ውስጥ በሚመለከታቸው ምድብ መዝግቦ በመያዝ ቀልጣፋ እና አሳታፊ በሆነ መልኩ በውስን ጨረታ ለሚፈፀሙ ጥቅል ግዥዎች እና በዋጋ ማቅረቢያ /proforma/ ለሚፈፀሙ ተናጠል ግዠዎች የተመዘገቡ ድርጅቶችን በመጋበዝ ወይም በማሳተፍ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ከታች የተጠቀሱትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ማቅረብ የምትፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት በሰም በታሸገ ፖስታ መረጃዎች አደራጅቶ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡
1. ከሚመዘገቡበት ዘርፍ ጋር ተዛማጅ የሆነ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሰርቲፊኬት እና ከሀገር ውስጥ ገቢ ቢሮ የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ (ታክስ ክሊራንስ)፤ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር በማቅረብ ይህ የጥሪ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ዘወትር በስራ ሰዓት መመዝገብ ይችላሉ፡፡
2. የድርጅታችሁን ገቢ ወጪ እንቅስቃሴ የሚያሳይ የቅርብ ሁለት ዓመት የተጣራ ካሽ ፍሎ እንድታቀርቡ፤ እንዲሁም ድርጅታችሁ ከተመሰረተ ከአንድ አመት በላይ ያስቆጠረ ከሆነ ደግሞ በውጭ ኦዲተር የተሰራ የቅርብ ሁለት አመታት ኦዲት ሪፖርት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
3. ተመዝጋቢ ድርጅቶች ለሰጣችሁት አገልግሎት ወይም ላቀረባችሁት ዕቃ ከተመዘዘገባችሁበት ዘርፍ ጋር ቀጥተኛ የሆነ መልካም አፈጻጸም የሚገልጽ ምስክር ወረቀት ፤ የገባችሁት ውል እና ልዩ ልዩ የድርጅታችሁን አፈፃፀም የሚገልፁ ማስረጃዎች ቢቀርብ የበለጠ ተቀባይነት ይኖረዋል፤
4. ተመዝጋቢዎች ኮርፖሬሽኑ የሚፈልጋቸውን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች በተፈለገው ጊዜ፤ ቦታ፤ ሁኔታ፣ ብዛት እና ጥራት ለማቅረብ ፈቃደኞች እና ኃላፊነት የሚወስዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተመዝጋቢዎች ለምዝገባ ምንም አይነት ኮርፖሬሽኑ ክፍያም ሆነ የማስከበሪያ ዋስትና አይጠይቅም፡፡
6. አምራች ድርጅቶች እና ከአምራቹ ህጋዊ ውክልና የተሰጣቸው አስመጪዎች እና ጅምላ አከፋፋዮች የበለጠ ተቀባይነት ያላቸው ሲሆን ይህንን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
7. እንዲመዘገቡ እድል የሚሰጣቸው ድርጅቶች ያልታገዱ (debarred) መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
ዝርዝር ፍላጎት
1. ቀላል የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች (ሚክሰር ፤ ጄኔሬተር ፤ የውሃ ፓምፖች…)
2. የቢሮ መገልገያ ዕቃዎችና ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች
3. የምግብ መገልገያ ዕቃዎች
4. ዩኒፎርምና አልባሳት
5. የጽህፈት መሳሪያዎች
6. ኮምፒውተርና ተዛማጅ መገልገያ ዕቃዎች
7. የሳኒታሪና የጽዳት ዕቃዎች (የእጅ መታጠቢያ ሲንኮች፤የመጸዳጃ ሲንኮች፤መሞቂያዎች፤የሳሙና ማስቀመጫዎች፤ፈሎር ደሬኖች፤ወተር ክሎሴቶች፤ ወተር ፕሩፊንግ ዕቃዎችና የመሳሰሉት)
8. የኤሌክትሪክ ዕቃዎች (የኤልክትሪክ ፓምፖች፤የኤሌክትሪክ ገመዶች፤ፓወር ክብሎች፤ዲስትሪቡሽን ቦርዶች፤የኤሌክትሪክ ፖሎች፤ፋየር ሬሲስታንስ ኬብሎች፤ፋየር ሆዞች፤ፊቲንጎችና የመሳሰሉት)
9. ፓይፕ፤ፒቪሲና የቧንቧ ዕቃዎች
10. አሸዋ ፤ ጠጠር ፤ ድንጋይ ፤ ሰሌክት ማቴሪያልና የመሳሰሉት
11. ሴራሚክ ፤ እብነበረድ ፤ ግራናት እና መሳሰሉት
12. አሉሚኒምና መስታወት አቅርቦትና የገጠማ አገልግሎት
13. የማጠናከሪያ ብረት
14. ባለክዳንና ኤጋ ቆርቆሮዎች ፤ ክብ ፤ ማዕዘንና ዝርግ ብረቶች ፤ ሚስማሮችና የመሳሰሉት
15. ሲሚንቶና የተዘጋጀ አርማታ(የተለያዩ ብሎኬቶች፤ጡቦችና የመሳሰሉት)
16. የፊኒሺንግ ዕቃዎች (የወለልና የግድግዳ ፊኒሺንግ ዕቃዎች፤ ስከርቲንግ፤ዞኮሎ፤ ሲሊንግ ማቴሪያልስ እና የመሳሰሉት)
17. ቀለሞች (ሲንቴቲክ ኢናሜል፤ ኳርትዝ፤ፕላስቲክ ቀለም፤ኦይል ቀለም፤አንቲረስት፤ስቱኮ እና የመሳሰሉት)
18. ብሎ
19. የላቦራቶሪና የጂኦቴክኒካል ምርመራ አገልግሎት
20. የህትመት ፤ የፊልም ፕሮዳክሽንና የኤቨንት ኦርጋናይዚንግ አገልግሎት
21. ችግኞች የግብርና መሳሪዎችና መገልገያ ቁሳቁሶች (ምርጥ ዘር ፤ የኬሚካል መርጫ ፤ ማጭድ ፤ አካፋ ፤ መኮትኮቻ ፤ እና የመሳሰሉት)
22. የትክኖሎጂና የደህንነት ዕቃዎች (የእሳት መከላከያ እና የመሳሰሉት)
23. የእንጨትና የእንጨት ውጤቶች
24. የመኪና ጌጣጌጥ
25. የስፖርት አልባሳትና ቁሳቁሶች
26. አስፓልት
27. የተለያዩ መጠን ያላቸው ጎማዎችና ባትሪዎች
28. የኢንጂነሪንግ ፤ የኬሚካልና የላቦራቶሪ ዕቃዎች
29. መድኃኒት ፤ የህክምና ዕቃዎችና ቁሳቁሶች
30. ኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች (ሊፍት፤የማሞቂያና የአየር መቆጣጠሪያ ዕቃዎች አቅርቦትና ገጠማ)
የምዝገባ ሂደት
ተመዝጋቢዎች ከላይ የተዘረዘሩ መረጃዎችን አሟልተው በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማሸግ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና መምሪያ በመገኘት ቅዳሜን ጨምሮ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን አንስቶ ባሉት 20 ተከታታይ የስራ ቀናት ድርጅቱ በሚገኝበት ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ህንጻ 100 ሜትር ገባ ብሎ እስከ ቀኑ 09፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ከተጠቀሰው የማስረከቢያ ቀን እና ሰዓት ውጪ የሚመጡ ማንኛውም ካምፓኒ ፕሮፋይል ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ ተመዝጋቢዎች ከዚህ በታች በተገለፀው አድራሻ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን
ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና መምሪያ
ፖስታ ሳጥን ቁጥር 21952/1000
የስልክ ቁጥር 0118 13 45 27
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን
ጨረታ
አዲስ ዘመን ህዳር 5 ቀን 2015 ዕትም ላይ የተወሰደ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
ጨረታ
አዲስ ዘመን ህዳር 5 ቀን 2015 ዕትም ላይ የተወሰደ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የግንባታ ጨረታ | bid
በየቀኑ ለሚወጡ ጨረታዎች
ማስታወቂያ በቋሚነት ከስር ያለውን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የኮንስታራክሽን ዘርፍ ባለሞያዎች
http://t.me/unitysupplydb1
" የቀድሞ የአቅራቢነት ምዝገባ ከህዳር 30 በኃላ አገልግሎት አይሰጥም " - የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በመንግስት ግዥ ለሚሳተፉ አቅራቢዎች ባሰራጨው ደብዳቤ የቀድሞው የአቅራቢነት ምዝገባ ከህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም በኋላ አገልግሎት እንደማይሰጥ አሳውቋል።
በዚህም ፤ ከዚህ በፊት በባለስልጣን መ/ቤቱ ድረ-ገጽ (https://www.ppa.gov.et/) ላይ የተመዘገቡ አቅራቢዎች ምዝገባቸው ተቀባይነት የሚኖረው የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን (e-GP) መጠቀም ባልጀመሩ ተቋማት ብቻ እስከ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አስገንዝቧል።
በመሆኑም በ https://egp.ppa.gov.et/ ላይ በመግባት ተገቢውን ምዝገባ በማከናወን በመንግስት ግዥ ላይ መሳተፍ እንደሚችሉ አሳውቋል::
የቴሌግራም ዌብሳይታችንን ይከታተሉ!
https://t.me/unityconsupply
የዲዛይን ስራ አገልግሎት ብሄራዊ
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብከመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተልማት ጽ/ቤት በ2015 በጀት አመት ለሚያሰራው የተለያዩ የግንባታ ስራዎች የሚሆን የዲዛይን ዝግጅት ስራ ማለትም፡-
ሎት 1 ጌጠኛ መንገድ ፤የግሪን ኤሪያ አጥር እና በቴራዞን የማስዋብ ስራ ፤ የድጋፍ ግንብ ስራ ፤የቄራ አጥር እና ሴፍቲ ታንክ ስራ፤ የተፋሰስ እና የመሸጋሪያ ድልድይ ዲዛይን ስራ
ሎት-2 የከተማ አቀፍ የተፋሰስ ኔት-ወርክ (መስመር) ፕላን አገልግሎት ስራ ለማሰራት በዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶች /አማካሪዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለሆነም በሥራው ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ፡
በጠቅላላ ስራዎች አማካሪ ድርጅቶች ደረጃቸዉ 5 እና ከዚያ በላይ የሆኑ
ለስራው በማማከር ስራ ህጋዊ አግባብነት ያለዉ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉና ያሳደሱ! የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው/የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና TIN ያላቸው፤ቢያንስ ከ3 (ሶስት) አመት በላይ በዘርፉ የስራ ልምድ ያላቸው።
የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ከተማ ኣስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 33 በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ 21 (ሃያ አንድ) ተከታታይ ቀናት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በስራ ቀንና ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ (ሎት) የማይመለስ የኢትዮ. ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
ተጫራቾች በየሎቱ ለየብቻው የጨረታው የፋይናንሽያል ሰነድ ዋና እና ኮፒ በማድረግ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ በአብክመ ከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሃያ ሁለተኛዉ ቀን /22ኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ ማስገባ ይችላሉ።
በዚሁ ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ ፡4:30 ሰዓት ላይ ከላይ የተዘረዘሩትን የዲዛይን ዝግጅት አገልግሎት ስራ የጨረታ ሰነድ ይከፈታል።
ጨረታው በሃያ ሁለተኛዉ ቀን (22ኛ)ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 22ኛው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም የበአል ቀን ከሆነ ቀጣይ ባለዉ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ይከፈታል።
6.ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሎት 1 እና ለሎት 2 ለእያንዳንዳቸዉ ብር 13,000 (አስራ ሶስት ሽህ) ብር በጥሬ ገንዘብ ወይንም በተረጋገጠ በባንክ ትእዛዝ /CPO/ ማስያዝ አለባቸው።
የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል።
መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም
በስልክ ቁጥር፡- 033 554 0255 ደውለው መረዳት ይችላሉ።
በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር
ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት
የቴሌግራም ዌብሳይታችንን ይከታተሉ!
https://t.me/unityconsupply
የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ
በዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የዶርሚቶራ ቀለም ስራ ላይ የተሰማሩ የጥቃቅን እና አነስተኛ ግንባታ ማህበራትን አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት ፡-
1.በከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒሰቴር የተመዘገቡ እና በ2015 ዓ/ም የንግድ ፈቃድ ያሳደሱ
2.ከመንግስት የሚፈለግበትን የግብርና የታክስ እዳ አለመኖር የሚያገለግል የስምምነት ደብዳቤ ከታክስ አስተዳድር ቢሮ ማቅረብ የሚችል ፡፡
3. ወርሀዊ የታክስ ማስታወቂያ በማቅረብ የሰበሰቡትን የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢ ማድረጋችውን ሚገልጽ ከሚመለከታችው ገቢዎች ጽ/ቤት የተሰጠ የማረጋገጫ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል
• በዞኑ የግንባታ ስራ ላይ ተሳትፎስራዎች ያላስተጎጎሉላል ውል ያላቆረጡ ማህበራትን እየጋበዘ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ማህበራት የማይመለስ ብር 100.00/አንድ መቶ/ ብር ብቻ በፕሮጀክቱ ስም በዲላ መምህራን ኮሌጅ ፋይናንስ ገቢ በማድረግና ደረሰኝ በመውሰድ የማስረጃዎቻቸው ኦርጂናል ይዘው በመቅረብ እና በመመዝገብ ኮፒውን በማስያዝ የጨረታው ሰነድ ከዲላ መምህራን ኮልጅ መውሰድ ይችላል፡፡
• ተጫራቾች የጨረታው ሰነዶቻቸው በመሙላት በኤንቨሎፕ በማሸግ በእያንዳዱ ላይ ማህተሙንና ፊርማውን በማስፈር አንድ ኦርጂናልና ሁለት ፎቶግራፊክ ኮፒ ሰነድ እያንዳነዱን በተናጥል በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ እስከ 15ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ድረስ በዲላ መምህራን ኮሌጅ ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖረባቸዋል፡፡
• በኦረጅናል ሰነድ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ሰረዝ ድልዝ በሚነበብ መልክ በድጋሚ መጻፍ ይኖርበታል ፡፡
• እያንዳንዱ ተጫራች የጨረታው ማስከበሪያ 20.000.00(ሀያ ሺህ ብር)በባንክ በተረጋገጠ /CPO/ ሲፒኦ ብቻ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ በጥሬ ገንዘብ ፤ በኢንሹራንስ ወይንም በሌላ አማራጭ ማቅረብ አይቻልም፡፡
• ጨረታው በውክልና የሚመጡትን አይመለከትም፡፡
• በእጅ የተሞሉ ኮፒ ሰነዶችን ማቅረብ ከጨረታው ውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
• ጨረታው የሚዘጋው በ15ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ሲሆን የሚከፈተው ተጫራቾቹ ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የሚመለከታችው ክፍሎች በተገኙበት በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰዓት በዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር --ይሆናል፡፡ ቀኑ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
• ከላይ በተጠቀሱት መስፈርቶች ሳያሟሉ የሚያቀርብ የግንባታ ማህበራት ከጨረታው ውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
• መስሪያ ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆን በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ
በየቀኑ ለሚወጡ የማስታወቂያ ጨረታ
የቴሌግራም ዌብሳይታችንን ይከታተሉ!
https://t.me/unityconsupply
በየቀኑ ለሚወጡ የማስታወቂያ ጨረታ
የቴሌግራም ዌብሳይታችንን ይከታተሉ!
https://t.me/unityconsupply
ኩባንያው ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች ፣ የተለያዩ የተሸከርካሪ አካሎችና ኮንቴይነሮችን እንዲሁም ኩባንያው ሲገለገልባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና ልዩ ልዩ እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Posted by: ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ
ሪፖርተር እሁድ ጥቅምት 27 ቀን 2015 ዓ . ም
የጨረታ ማስታወቂያ (ቁጥር 141/2015)
ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ
ጉዳት/አደጋ ደርሶባቸው ለደንበኞቹ ተገቢውን ካሣ ከፍሎ በውክልና የተረከባቸውን
• ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች ፣
• የተለያዩ የተሸከርካሪ አካሎችና ኮንቴይነሮችን እንዲሁም ኩባንያው ሲገለገልባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና ልዩ ልዩ እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የተሽከርካሪ የስም ማዛወሪያ፣ የጉምሩክ ቀረጥ፣ ግብርና ሌሎች ዕዳዎችና ወጪዎች ቢኖሩ በአሸናፊው የሚሸፈኑ ይሆናል፡፡
የተሽከርካሪ የስም ዝውውር በገዢ ምክንያት ከስድስት ወር በላይ ቢቆይ በዚህ ምክንያት ለሚመጣ ችግር ኩባንያችን ኃላፊነት አይወስድም፡፡
አሸናፊ ተጫራች የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር (TIN No.) ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
ንብረቶቹ የሚገኙበት የኩባንያው አድራሻ፡-
• ገላን ሪከቨሪ ፡ ገላን ኖክ ነዳጅ ማደያ ፊት ለፊት
• ዋናው መስሪያ ቤት ፡ ጎተራ
ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ንብረቶቹ በሚገኙበት አድራሻ በሥራ ሰዓት ሄዶ በማየት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድና የጨረታ ማቅረቢያ ቅጽ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) ከፍሎ መውሰድ ይችላል፡፡
የጨረታ መነሻ ዋጋ 15% ቫት ያላካተተ መሆኑን እየገለጽን፤ ማንኛውም ተጫራች የሚጫረትበትን የእያንዳንዱን ምድብ እቃ ዋጋ (ቫት ሳይጨምር) በጨረታ ማቅረቢያ ቅፅ ላይ በመሙላት ለእያንዳንዱ ምድብ እቃ የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የመነሻ ዋጋውን 20% (ሃያ ከመቶ) በኩባንያው ስም በተዘጋጀ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የኢንሹራንስ ቦንድ ጋር በኤንቨሎፕ በማሸግ እስከ ህዳር 02 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ የኩባንያው ዋና መ/ቤት በሚገኝበት ጎተራ ምድር ቤት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላል፡፡
ማሳሰቢያ፡- አሸናፊ ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ 15% ቫት የሚጨመር መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ጨረታው ህዳር 03 ቀን 2015 ዓ.ም ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጎተራ በኩባንያው ዋና መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ለተሸናፊዎች ሙሉ በሙሉ የሚመለስ ሲሆን ለአሸናፊዎች ግን ከሚገዙበት ዋጋ ጋር ይታሰባል፡፡ ተጫራቾች ለተጫረቱበት ንብረት አሸናፊነታቸው ከተገለፀበት ዕለት ጀምሮ በአሥር ቀናት ውስጥ ክፍያውን አጠናቀው ንብረቱን ባያነሱ ያስያዙት ገንዘብ በመቀጫ መልክ ለኩባንያው ገቢ ሆኖ አሸናፊነታቸው ይሰረዛል፡፡
ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በስልክ ቁጥር 011-442-14-99 | 09-11-82-05-76 በመደወል መጠየቅ ይችላል፡፡
ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
Deadline: 2022-11-12 ( ህዳር 03 ቀን 2015 ዓ.ም)
ጨረታ
ሪፖርተር ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዕትም ላይ የተወሰደ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
ጨረታ
አዲስ ዘመን ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዕትም ላይ የተወሰደ
አድራሻ፦ጉርድ ሾላ ሆሊ ሲቲ ሴንተር
ፎቅ አጠገብ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የጨረታ ማስታወቂያ
ገናናው ፋውንዴሽን በሰም
በታሸገ ኤንቬሎፕ ከ GC-6 ወይም BC-6 እና ከዚያ በላይ የ2015 በጀት ዓመት የሚያገለግል ፍቃድ ያለው እና ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የተመዘገቡበትን የስራ ተቋራጮች በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ገነተ ማርያም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአንድ ብሎክ ግንባታና ማጠናቀቂያ ሥራ፣ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከገናናው ፋውንዴሽን መግዛት ይችላሉ።
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን (ኦሪጅናል እና ኮፒ) በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ከጨረታ ማብቂያው ገደብ በፊት ለገናናው ፋውንዴሽን ገቢ ማድረግ አለባቸው።
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከጠቅላላ ዋጋ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ በገናናው ፋውንዴሽን ስም ማስያዝ አለባቸው።
ተጫራቾች ተመሳሳይነት ባላቸው ፕሮጀከቶች ላይ ያላቸውን ልምድ የሚያሳይ የኩባንያቸውን ፕሮፋይል፣ የማበረታቻ ደብዳቤ እና ሌሎች እውቅና ካላቸው ድርጅቶች ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተጠየቁትን አስፈላጊ ዝርዝሮች በሙሉ መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በ25ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ገነተ ማርያም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አዳራሽ ይከፈታል።
ገናናው ፋውንዴሽን ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ
ገናናው ፋውንዴሽን ስልክ ቁጥር +251 91 262 9220
ገነተ ማርያም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት-+251 91 224 7191
ገናናው ፋውንዴሽን
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
ጨረታ
አዲስ ዘመን ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዕትም ላይ የተወሰደ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
ማስታወቂያ
ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ
ደረጃ-5/6 እንፈልጋለን?
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር:
Tel.✆+251-989-999-001
Tel.✆+251-984-865-338
በቀጥታ የቴሌግራም አድራሻ/Inbox
➢ t.me/UnitySupplydbot ☜|]
➢ t.me/unitysupplyoffical //
መልዕክት መቀበያ ቦት/ያማክሩን!
ጆሞ2 በአካል ቢሮ መምጣት ይችላሉ
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የሚሸጥ 22 kw ክሬሸር
ማጠቢያ እና ማድረቂያ
አዲስ ነው
+251912631227 ነቢል
+251921763931 ከድር
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የዩኒቲ ኮን.ስራ ሰፕላይ ኦፊሻል ድርጅት አገልግሎት ለማግኘት የእጅ ስልኮዎን በመጠቀም አገልግሎታችንን ማግኘት ይችላሉ ወይም ጆሞ ቁ.2 የሚገኘው ቢሮችን በመምጣት የሚፈልጉትን አይነት አገልግሎት በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ!
Tel.✆+251-989-999-001
Tel.✆+251-984-865-338
በInbox /የቴሌግራም አድራሻችን፦
➢ t.me/UnitySupplydbot ☜|]
ላይ ያናግሩን, መልክቶ ይደርሰናል
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 08/2015
የአማራ ህንፃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት 3B +G+14 Tikur Abay Office Building Construction Project "Design and construction of shoring wall including excavation work" by supplying all necessary Materials, equipment & Labor ብቃት ካላቸው ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን-በዘርፉ የንግድ ሥራ ፈቃድና ለዘመኑ ስለመታደሱ ማረጋገጫ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ እና የተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ የምስከር ወረቀት VAT Reg. Certificate/፣ የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል።
የጨረታ ሰነዱን አ/አበባ 4 ኪሎ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት መ/ቤት ጀርባ አልማ ህንፃ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ። ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፤ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ብቻ አዲስ አበባ ማስ/ጽ/ቤቱ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በተዘጋጀበት ቀን ከቀኑ 8፡30 ሠዓት አዲስ አበባ በሚገኘው በድርጅቱ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ ይከፈታል።
በውድድሩ አሸናፊ የሚረጠው ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረበው ሲሆን፤ ሥራው ላይ የሚውሉ ማቴሪያሎች ሥራ ላይ ከመዋላቸው በፊት እውቅና ካለው ተቋም የዕቃዎችን ትክክለኛነት ናሙና ተወስዶ ጥራቱ በቴስት ማረጋገጥ ካስፈለገ በማሠራት ወይም በአማካሪ ባለሙያዎች ትክክለኛነቱን ሲያሟላ ብቻ ይሆናል።
.በጨረታው ቅር የተሰኘ ተጫራች የጨረታ ውጤቱ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ በ3 የሥራ ቀናት ብቻ ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል።
የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ45 ቀናት ፀንቶ ይቆያል።
የጨረታ ተወዳዳሪዎች በሌሎች ተወዳዳሪዎች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማቅረብ አይችሉም።
በጨረታ ሠነዱ በእያንዳንዱ ገጽ እና ፖስታው ላይ የድርጅቱ ፊርማና ማህተም ሊኖር ይገባል።
ድርጅቱ የጨረታ አሸናፊ ከሆነው አቅራቢ የጨረታውን ይዘት ሳይቀይር ከገዛው ዕቃ ጠቅላላ መጠን ላይ ከውል በኋላ 50% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል።
ከጨረታ ሳጥን መዝጊያ ቀንና ሰዓት ዘግይቶ የቀረበ ተጫራች ተቀባይነት አይኖረውም።
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው። ይህም ሲባል ጨረታው በመሰረዙ ተጫራቾች በጨረታው ለመወዳደር ላወጡት ወጪ ድርጅቱ ኃላፊነት አይወስድም።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በአካል በመገኘት ወይም ከዚህ በታች በተጠቀሱት አድራሻዎች ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ስልክ ቁጥ፡ 01 11 26 51 45/ 09 18 70 50 36/09 18 80 03 64 ፋክስ ቁጥር፡ 01 11 26 53 38
የአማራ የህንፃ ሥራዎች ኮንስትራክን
ድርጅት አዲስ አበባ ማስ/ጽ/ቤት
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
ያገለገለ ሆንዳ መኪናን ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ (ቁልጭ የወጣቶች ሥነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት)
Deadline: ሰባተኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት (2022-11-10)
አዲስ ዘመን ሐሙስ ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ . ም
ያገለገለ ሆንዳ መኪናን ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁልጭ የወጣቶች ሥነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት አንድ ያገለገለ ሆንዳ መኪና በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾችን ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት እንዲሳተፉ ድርጅቱ ይጋብዛል።
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን መካኒሳ መካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም 2ኛ ፎቅ ላይ ከሚገኘው ቢሮአችን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሰባት (7) የሥራ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 3፡00 -11፡00 ሰዓት በመምጣት መግዛትና መኪናውን ማየት ይችላሉ።
ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባለው ሰባተኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ በ 4 ፡ 00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ከጠዋቱ በ 5 ፡ 00 ሰዓት ላይ በዝግ ጨረታ ይከፈታል።
የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር 1,000,000.00 ሲሆን ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የመጫረቻ ዋጋውን 10% በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
የጨረታ አሸናፊ የጨረታው ውጤት ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ንብረቱን በራሱ ወጪና ኃላፊነት ማንሣት ይኖርበታል።
ድርጅቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- መካኒሳ መካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም ሕንፃ 2 ኛ ፎቅ
ስልክ፡ +251 93 388 4838 ወይም +251 91 382 9572
ቁልጭ የወጣቶች ሥነ ተዋልዶ ጤናና ልማት ድርጅት
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
Invitation to Tender
Bid Announcement No. SSNT-T 342
Ethiopian Airlines Group intends to invite qualified Category 1 Contractors (GC/RC-1) for the Design-Build of Semera Airport Airfield Expansion Project. Any legally established bidders in Ethiopia with renewed Trade License for the current year, Valid Tax clearance, VAT registration certificate, Tax Payer Identification Certificate (TIN) & Tax clearance certificate stating the bidder is eligible to participate in any public tender and valid at least at the deadline for submission of bids can get the tender document.
Bidders should deposit non-refundable ETB 100.00 (One Hundred Birr) to the nearby Commercial Bank of Ethiopia (CBE) referring this tender number SSNT-T342 to Ethiopian Airlines Group Account Number 1000006958277(E99). Bidders shall email the scanned copy of the deposit slip to the below address and will get the Tender document by return Email.
Bidders must submit Birr 500,000.00 /Five hundred thousand Birr/ as a bid security in the form of CPO or unconditional and irrevocable bank guarantee from any certified financial institution in the name of Ethiopian Airlines Group. Bidders are required to bring both an Original and Copy of their Technical and Financial Bid Proposals and Original unconditional irrevocable bank guarantee or CPO in a separate sealed envelope. The bid will be closed on November 18, 2022, at 2:30 PM and will be opened on the same date at 3:00 PM at Ethiopian Airlines Group Employees' Main Cafeteria in the presence of bidders or their representatives.
For more information; please contact us at the below address.
Ethiopian Airlines Group
Bole International Airport Addis Ababa, Ethiopia Strategic Sourcing N-Technical
Tel. 011-517-4028
E-mail: Aynalem Ay@ethiopianairlines.com
Ethiopian Airlines Group reserves the right to cancel or modify the tender partially or entirely.
የቴሌግራም ዌብሳይታችን ይከታተሉ
https://t.me/unityconsupply
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
