cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

መርከዝ ዑስማን ኢብኑ ዓፋን

◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈ ⭕️ መርከዝ ዑስማን ዒብኑ ዐፋን⭕️ 🌐 በኦንላይን📱ለመከታተል :👇 ⭕️ በቴሌግራም join ያድርጉ👇 ቻናላችንን በመቀላቀል የሚሰጡ ትምርቶችን ይከታተሉ https://t.me/ausmaebnuafan #ሼር_ሼር ♡ ㅤ   ❍ㅤ    ⎙ㅤ   ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ

Більше
Країна не вказанаАмхарська7 873Релігія і духовність77 558
Рекламні дописи
357
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
-1030 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

۞ الله ۞ الرحمن ۞ الرحيم ۞ الملك ۞ القدوس ۞ السلام ۞ المؤمن ۞ المهيمن ۞ العزيز ۞ الجبار ۞ المتكبر ۞ الخالق ۞ البارئ ۞ المصور ۞ الغفار ۞ القهار ۞ الوهاب ۞ الرزاق ۞ الفتاح ۞ العليم ۞ القابض ۞ الباسط ۞ الخافض ۞ الرافع ۞ المعز ۞ المذل ۞ السميع ۞ البصير ۞ الحكم ۞ العدل اللطيف ۞ الخبير ۞ الحليم ۞ العظيم ۞ الغفور ۞ الشكور ۞ العلي ۞ الكبير ۞ الحفيظ ۞ المقيت ۞ الحسيب ۞ الجليل ۞ الكريم ۞ الرقيب ۞ المجيب ۞ الواسع ۞ الحكيم الودود ۞ المجيد ۞ الباعث ۞ الشهيد ۞ الحق ۞ الوكيل ۞ القوي ۞ المتين ۞ الولي ۞ الحميد ۞ المحصي ۞ المبدئ ۞ المعيد ۞ المحيي ۞ المميت ۞ الحي ۞ القيوم ۞ الواجد ۞ الماجد ۞ الواحد ۞ الأحد ۞ الصمد ۞ القادر ۞ المقتدر ۞ المقدم ۞ المؤخر ۞ الأول ۞ الآخر ۞ الظاهر ۞ الباطن ۞ الوالي المتعالي ۞ البر ۞ التواب ۞ المنتقم ۞ العفو ۞ الرءوف ۞ مالك ۞ الملك ۞ ذو ۞ الجلال ۞ والإكرام ۞ المقسط ۞ الجامع ۞ الغني ۞ المغني ۞ المانع ۞ الضار ۞ النافع ۞ النور ۞ الهادي ۞ البديع ۞ الباقي ۞ الوارث ۞ الرشيد ۞ الصبور 📲በ telegram channal👇📱 @ou_se @ou_se
Показати все...
🌍 የታላቁ አዛኝ የአለም ነብይ ጣፋጭ ታሪክ 🌍 •════•••🌺•••════• ✔️ [ክፍል 1] ✔️ 🕋 የነብዩ የዘር ሐረጋቸው፣ አወላለዳቸው እና የልጅነት ዘመን 🌴 ••┈┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈┈•• 🥀 ሙሐመድ የዐብደላህ ልጅ፣ የአብዱል ሙጦሊብ ልጅ፣ የሃሽም ልጅ፣ የመናፍ ልጅ፣ የፈህር (ቁረይሽ) ልጅ፣ የማሊክ ልጅ፣ የነድር ልጅ፣ የኪናነህ ልጅ፣ የዐድናን ልጅ፣ የአላህ ነብይ እስማዒል ልጅ፣ የአላህ ወዳጅ የኢብራሂም ልጅ። አላህ ከጥሩ ጎሳ መረጣቸው። የመሐይምነት ዘመን ቆሻሻ ወደ ዘር ግንዳቸው አልገባም። 📜 ሙስሊም እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “አላህ ከእስማዒል ልጆች ኪናናን፣ ከኪናናህ ልጆች ውስጥም ቁረይሽን፣ ከቁረይሽ ሃሽምን፣ ከበኒ ሃሽም በኩል ደግሞ እኔን መርጧል።” (📚ሙስሊም ዘግበውታል) 🌐 አወላለዳቸው •🔺┈•✿🌼✿•┈🔺• የተወለዱት የዝሆን አመት (ዓመል ፊል) በመባል በሚታወው ዘመን ነው። ይህም ዓመት አብረሃ ካዕባን ለማፍረስ የሞከረበት ኣመት ነበር። አላህም እጅግ በሚያስደንቅ ጥበብና ተአምር ሐሳቡን አምክኖታል። ይህ በቁርአን ታሪክ ተወስቷል። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በዚሁ አመት በወርሃ ረቢአል አወል 11ኛው ቀን በእለተ ሰኞ እንደተወለዱ ዘገባዎች ያመለክታሉ። 🌐 አስገራሚ ጅምርና ግልጽ በረከት 🔺┈•✿🌼✿•┈┈•✿🌼✿•┈🔺 አባት አልባ ሆነው ተወለዱ። እናታቸው እርሳቸውን የሁለት ወር እርጉዝ እያለች አባታቸው ሞቱ። አያታቸው ዐብዱል ሙጦሊብም የማሳደግ ሐላፊነቱን ወሰዱ። በያኔዎቹ ዐረቦች ባህል መሠረትም ከበኒ ሰዕድ ጎሳ የሆነችና ሐሊመት ቢንት አቢ ዙዓይብ የምትባል እንስት ታሳድጋቸው ዘንድ ተሰጣት። የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚስማሙት ያኔ የበኒ ሰዕድ ቀዬ በድርቅ የተመታበት አመት ነበር። የእንስሳት ጋቶች ነጥፈዋል። አዝርእቱ ደርቀዋል። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በሐሊማ ቤት ካረፉበት እና ጡቷን መጥባት ከጀመሩበት ቅጽበት አንስቶ ግን የሐሊማ ቤት በበረከት ተሞላ። ፍየሎቿ ጠግበውና ጋቶቻቸው በወተት ተሞልቶ ይመለሱ ጀመር። በበኒ ሰዕድ መስክ ላይ እያሉ የተከሰተው የደረታቸው መቀደድ አላህ ለትልቅ ሐላፊነት እንደመረጣቸው የሚጠቁም የነብይነት ምልክት ነበር። አነስ ኢቢን ማሊክን (ረ.ዐ) ዋቢ በማድረግ ሙስሊም እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ በልጅነታቸው ዘመን ከሕጻናት ጋር በመጫወት ላይ እያሉ ጅብሪል (ዐ.ሰ) መጣና ያዛቸው። አጋደማቸውም። ደረታቸውንም ሰነጠቀው። ልቦናቸውንም አወጣ። የረጋ ደም የሚመስል ነገርም ከውስጡ አስወገደ። “ይህ የሰይጣን ድርሻ ነው” አለም። በወርቅ ሳህን ውስጥ አድርጎም በዘምዘም ውሃ አጠበው። ከዚያም እንደነበር ጠገነውና ወደቦታው መለሰው። ልጆችም ወደ ሐሊማ ቤት እየሮጡ ሄደው “ሙሐመድ ተገደለ” በማለት ተናገሩ። ሲመጡ የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት ገርጥቶ አገኙት። አነስ፡- “የዚህን ክስተት ፋና ከነቢዩ ደረት ላይ አይቻለሁ” ሲሉ ተናግረዋል። ከልባቸው ውስጥ የረጋ ደም የሚመስል ነገር መወገዱ እርሳቸውን ከልጅነት አጓጉል ባህሪያት አርቆ፣ ቁም ነገረኛ፣ ጽኑ፣ ሚዛናዊና ውብ ባህሪያት የተላበሱ ለማድረግ ነው። አላህ በጣም እንደሚጠብቃቸው እና እንደሚንከባከባቸው፣ ሰይጣንም እርሳቸውን የመተናኮል አቅም እንዳይኖረው መደረጉን ለማመልከትም ጭምር ነው። (📚ፊቅሁ ሲራ – ዶክተር ረመዷን አል-ቡጢ) ይህ ክስተት ሐሊማ ሕጻኑን ወደ ቤተሰቦቹ እንድትመልስ ምክንያት ሆነ። ያኔ የነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እድሜ አምስት አመት ነበር። ስድስት አመት ሲሞላቸው እናታቸው አሚና ሞተች። አያታቸው ሊያሳድጓቸው ወሰዷቸው። ስምንት ዓመት ሲሞላቸው አያታቸው ሞቱ። የማሳደጉን ሐላፊነትም አጎታቸው አቡ ጧሊብ ወሰዱ። 🌐 የላቀ እጣ ፈንታ •🔺┈•✿🌼✿•┈🔺• አስራ ሁለት አመት ሲሞላቸው አጎታቸው አቡ ጧሊብ ወደ ሻም ለንግድ እርሳቸውን አስከትለው ወጡ። ቅፍለቱ በስራህ በተባለ ቦታ ላይ ሲያርፍ ቡሐይራ የተባለን አንድ መነኩሴ ለመጎብኘት ጎራ አለ። ሰውየው የክርስትና ሐይማኖትና መጽሐፍት አዋቂ ነው። ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) በትኩረት አስተዋላቸው። በጥንቃቄ አጠናቸው። አናገራቸውም። ከዚያም ወደ አቡ ጧሊብ በመዞር፡- “ይህ ልጅ ምንህ ነው?” አላቸው። “ልጄ ነው” አሉት። (አቡ ጧሊብ በጣም ስለሚወዷቸው ልጄ በማለት ነበር የሚጠሯቸው።) ቡሐይራም፡- “ልጅህ አይደለም። የዚህ ልጅ አባት በሕይወት ሊኖር አይችልም” ሲል ተናገረ። አቡ ጧሊብም “የወንድሜ ልጅ ነው” አሉ። “አባቱ ምን ሆነ?” ሲል ጠየቃቸው። “ተረግዞ እያለ ሞተ” አሉ። “እውነት ብለሐል። በአስቸኳይ ወደሀገሩ ይዘኸው ተመለስ። አይሁዶች እንዳያገኙት ተጠንቀቅ። በአላህ እምላለሁ ካገኙት ይተናኮሉታል። ለታላቅ ደረጃ የሚበቃ ልጅ ነው” አላቸው። አቡ ጧሊብም ፈጥነው ወደ መካ መለሱት። 🌐 እንጀራ ፍለጋ •🔺┈•✿🌼✿•┈🔺• የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ለወጣትነት እድሜ ሲደርሱ እንጀራ ፍለጋ መሮጥ ጀመሩ። ፍየል ጥበቃ የጥረታቸው መጀመሪያ ነበር። በኋላ ላይ፡- “ለመካ ሰዎች በቀራሪጥ (መጠነ ትንሽ ክፍያ) ፍየል እጠብቅ ነበር።” ሲሉ ተናግረዋል። ይቀጥላል... ▰▬▬▬▭▬ @ou_se @ou_se ሼር ማድረግ አይርሱ
Показати все...
የታላቁ ነብይ ሙሃመድ ﷺ ታሪክ [ሲራ] ┄┉✽‌»‌🌺»‌✽‌┉┉✽‌»‌🌺»‌✽‌┉┄ ▪️የነብዩ የዘር ሐረጋቸው፣ አወላለዳቸው እና የልጅነት ዘመን ▪️የፉጅጃር ጦርነትና የፈዱል ስምምነት ▪️እመት ኸዲጃን ማግባታቸው ▪️በካዕባ ግንባታ መሳተፋቸው ▪️የነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) በሂራዕ ዋሻ መገለል /ኸልዋ/ ▪️ሚስጥራዊው የዳእዋ ሂደት ▪️ ይፋዊ ጥሪ ▪️ ጥሪውን ለማኮላሸት ጥቅም ላይ የዋሉ ልዩ ልዩ... 📡 @ou_se 📡 @ou_se
Показати все...
የሶሃቦች ታሪክ ከፈለጋችሁ ሊንኩን በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ 👉የሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ታሪክ 👇👇👇👇👇👇👇👇 @ou_se @ou_se @ou_se
Показати все...
❒ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረዲየሏሁ ዐንሁ❒ ┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈ 《 ከቤተሰቡና ከትውልድ ቀየው ርቆ በአላህ መንገድ ጥሪ በማድረግ ላይ እንዳለ በፍልስጤም ምድር ያረፈ ታላቅ ሶሐባ!》 ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረዲየሏሁ ዐንሁ እውነተኛው የህይወት መመሪያ ቁርኣን የዓረቢያን ምድር ማሸብረቅ በጀመረበት ጊዜ የየስሪብ ታዳጊ ወጣት ነበር። ውብ፣ ማራኪና መልካም ፀባይ የተላበሰ። ወጣቱ ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ኢስላምን የተቀበለው ከሂጅራ በፊት በየስሪብመዲና ከተማ የቁርኣንን ጥሪ እንዲያስተምር ከመካ በተላከው በ ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር ረዲየሏሁ ዐንሁ አማካኝነት ነው። ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ከሂጅራ አንድ አመት ቀደም ብሎ ወደ መካ ተጉዘው ከረሱል ﷺ መኖሪያ ቤት በሌላ ጊዜ ደግሞ ከመካ ውጭ በሚና ሸለቆ አቀባ> በተባለ ቦታ ከረሱል ﷺ ጋር ቃል ኪዳን (በይዓ) ከገቡት ሰባ ሁለት የስሪባውያን አንዱ ነው። በበይዓውም የየስሪብ ሙስሊሞች ጥቂት ሴቶችን ጨምሮ ነብያችንን ﷺ ለ መደገፍና ማንኛውንም ዓይነት መስዋትነት ለመክፈል ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል። •••✿❒🌹❒✿••• ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ያኔ በሙሉ ስሜት የረሱል ﷺ እጅ ጨብጠው ወዳጅነታቸውን ከገለፁት አንዱ ነው። ሙዓዝ ረ.ዐ ከመካ ወደ መዲና ሲመለስ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን የአጋሪወች ጣዖታትን ከቤታቸው ለማስወገድ እና ለመደምሰስ አንድ ቡድን አቋቋሙ። በዘመቻው በከተማው እውቅየ የነበረው አምር ኢብን አል-ጁመህ የተባለ ሰው ሊሰልም ችሏል።ታላቁ ነብይ ﷺ መዲና ከደረሱ ጀምሮ ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ በተቻለው መጠን አይለያቸውም ነበር። ቁርኣን እና ሸሪያዊ እውቀትን ከረሱል ﷺ አጥንቷል።ምሁር ለመሆንም በቅቷል ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ በሄደበት ቦታ ሁሉ አወዛጋቢ የሕግ ጥያቄወች ይቀርቡ ለት ነበር።ምሁርነቱን የሚያረጋግጥ ሰርቲፊኬት ያገኘው ከራሳቸው ከነብዩ ሙሀመድ ﷺ ነበር። <ሐላልና ሐራም> ነገሮችን በተመለከተ አቻ የሌለው ምሁር ሙዓዝ ኢብን ጀበል ነው"በማለት ረሱል ﷺ መስክረውለታል። ሙዓዝ ረ.ዐ ለረሱል ﷺ ኡማ ካበረከታቸው ታላቅ አስተዋፅኦወች አንዱ በረሱል ﷺ ዘመን ቁርኣንን ከሰበሰቡ ስድስት ሰወች አንዱ መሆኑ ነው። ሶሀባዎች አዋቂውን ሙአዝ በታላቅ አክብሮት እና ፍቅር ይመለከቱት ነበር። ረሱል ﷺ እና ሁለቱ ተከታታይ ኸሊፋወ ቻቸው ይህንን ትልቅ ተሰጥኦና ኃይል ለኢስላም ግልጋሎት አውለውታል። •••✿❒🌹❒✿••• ከመካ ነፃ መውጣት በኋላ ነገደ ቁረይሽ በነቂስ ኢስላምን ተቀበለ። በዚህ ወቅት ረሱል ﷺ የኢስላምን መሰረቶችና የሕግጋቶቹን ቃላትና መንፈስ ማሳወቅ የሚያስችላቸው መምህር ማስፈለጉን ወዲያውኑ ተረዱት። ከዚያም ዐትታብ ኢብኑ ኡሶይን ረዲየሏሁ ዐንሁ ምክትሉ አድርገው ሙዓዝን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ከእርሳቸው ጋር ቆይቶ መካውያንን ቁርኣን እና የኢስላምን ስርዓት እንዲያስተምር መደቡት። ረሱል ﷺ ወደ መዲና ከተመለሱ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የየመን ነገስታት መጥተው ከሕዝቦቻቸው ጋር ኢስላምን የተቀበሉ መሆናቸውን ለረሱል ﷺ አ ስታወቁ። የሚያስተምሯቸው መምህራን እንዲመድቡላቸውም ጠየቁ። ለዚህ ከፍተኛ ኃላፊነትም በሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ የሚመራ ግብረ-ኃይል ወደ የመን ላኩ። መሪውን ሙዓዝ ኢብኑ ጀበልን ረዲየሏሁ ዐንሁ አድርገው ላኩ። ከመሄዱ በፊት ግን የሚከተሉትን ጥያቄዎች አቅርበውለት ነበር። •••✿❒🌹❒✿••• «በሕዝቦች መካከል ምንን መሰረት በማድረግ ነው የምትፈርደው? » -የአላህን ኪታብ መሰረት በማድረግ" በማለት ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ መለሰ። « ያንን ችግር በተመለከተ በቁርአን ምንም ነገር ካጣህስ?» - በአላህ ነብይ ﷺ ሱና መሰረት"። «በዚህስ ውስጥ እንደዚሁ መፍትሄ ካጣህስ?» - "የራሴን ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት አእምሮየን አሰራዋለሁ (ኢጅቲሀድ) አደርጋለሁ። አለ ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረዲየሏሁ ዐንሁ። ረሱል ﷺ በዚህ መልስ ረክተው "ምስጋና ለአላህ ይገባው የነብዩን ልዩ ልዑክ ነብዩን ወደሚያረካ መልስ የመራው ለሆነ ጌታ" አሉ። ነብዩ ሙሀመድ ﷺ ራሳቸው ለዚህ የብርሃንና የነፃ መውጫ መምሪያ ልዑካን ቡድን አሸኛኘት አድርገውለታል። ከሙዓዝ ረ.ዐ ጎን ለጎን የተወሰኑ ርቀቶችን ተራምደዋል። በመጨረሻም፦ ሙዓዝ ሆይ! ምናልባት ከዚህ ዓመት በኋላ ላታገኘኝ ትችላለህ። ስትመለስ የምታየው መስጊዴን እና መቃብሬን ሊሆን ይችላል አሉት። ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። አብረውትም ያሉት እንደዚሁ አለቀሱ. ከሚወዳቸው ነብይ ﷺ የመነጠል ከፍተኛ የሐዘን ስሜት ልቡን በረበረው። ይህ የነብዩ ﷺ ትንቢት ትክክል ነበር። ከዚያች ጊዜ በኋላ ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ዓይኖቹ ረሱልን ﷺ አላዩም ሙዓዝ ከየመን ተልዕኮውን ጨርሶ ሳይመጣ ረሱል ﷺ አረፉ። ሙዓዝ ረ.ዐ መዲና ሲመለስ ያቺ የተባረከች ከነብዩ ሙሀመድ ﷺ ጋር አብሮ የመሆን እድል እንግዲህ አለመገኘቷን ሲያይ ማልቀሱና መንሰቅሰቁ የሚጠየቅ አይሆንም። •••✿❒🌹❒✿••• በዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ የኸሊፋነት ዘመን ሙዓዝ ረዲየሏሁ ዐንሁ ለበኑ ኪላብ ነገድ ድጎማቸውንና ከሀብታሞች የ ሚመጣውን ምፅዋት ለድሆች ለማካፈል ተልኮ ነበር። ስራውን ካጠናቀቀ በኋላ ባዶ እጁን ወደ ቤቱ ተመለሰ። ሚስቱ "ኮሚሽነሮች ለቤተሰቦቻቸው ይዘዋቸው የሚመለሱት ስጦታወች የታሉ?" ስትል ጠየቀችው። እሱም "ንቁ ተቆጣጣሪ ነበረኝ አጥብቆ የሚቆጣጠረኝ" ብሎ መለሰላት። "በረሱል ﷺ እና በአቡበክር ረዲየሏሁ ዐንሁ የታመንክ ሰው ነበርክ አሁን ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ መጥቶ አንተን የሚከታተል ተቆጣጣሪ አስከተለ? ስትል በመደነቅ ቁጣዋን ገለፀች። ነገሩን ከዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ ቤተሰቦች ለሆኑ ሴቶች በምሬት ስለነገረቻቸው ወሬው ለዑመር ረ.ዐ ደረሳቸው። ዑመርም ሙዓዝን አስጠርተው፦ "እኔ አንተን የሚቆጣጠር ተቆጣጣሪ ልኬብሀለውን" አሉት። እሱም "አይ የለም! አላኩም አሚረል ሙእሚኒን ነገር ግን ያኔ ስትጠይቀኝ ያገኘሁት ምክንያት እሱን ብቻ ነበር።" ብሎ መለሰላቸው። በሁኔታው ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ ሳቁና ይህ እንደሚያስደ ስትህ ተስፋ አደርጋለሁ። ብለው የሆነ ስጦታ ሰጡት። •••✿❒🌹❒✿••• በዑመር ረ.ዐ ዘመነ ኸሊፋ የሶርያው አስተዳዳሪ የዚድ-ኢብን-አቡ ሱፍያን የሚከተለውን መልእክት ለኸሊፋው ላኩ፦ "አሚረል ሙእሚን ሆይ! የሶርያ ህዝብ ብዙ ነው ከተሞቹን አጥለቅልቀዋ ቸዋል። ቁርኣን የሚያቀሩና የኢስላምን ስርዓት የሚያስተምሩ መምህራን ያስፈልጓቸዋል። ከዚህ በኋላ ዑመር ረ.ዐ በነብዩ ﷺ ጊዜ በነበሩና ቁርኣንን የሰበሰቡ አምስት ሰዎችን መረጡ። ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል፣ ዑበይዳህ ኢብን አስ ሳሚት፣ አቡ አዩብ አል አንሷሪ፣ ዑበይ ኢብን ከዕብ እና አቡ ደርዳእ ረዲየሏሁ ዐንሁም ነበሩ ተመራጮቹ። ሰብስበዋቸው በሶሪያ የሚገኙ ወንድሞቻችሁ ቁርኣን የሚያቀሩ እና የኢስላምን ስርዓት የሚያስተምሩአቸው ሰወች በመላክ እንድረዳቸው ጠየቁኝ አላህ ይባርካችሁ እና ሶስት ሰዎችን ከመካከላችሁ ምረጡልኝ ነገሩን ለምርጫ ካላቀረባችሁት ከመካከላችሁ ራሴ ሶስት ሰወችን እመርጣለሁ አለ ዑመር ረ.ዐ። «ምን ለዚህ ምርጫ ያስፈልገዋል?" ሲሉ ተሰብሳቢወቹ ጠየቁ። "አቡ አዩብ ሽማግሌ ነው ዑበይ ደግሞ ታሟል።ይህ ደግሞ ሶስታችን ብቻ ያስቀረናል።" በዚሁ ተስማሙ። ይቀጥላል ሼር ይደረግ ጆይን👉@ou_se
Показати все...
00:48
Відео недоступнеДивитись в Telegram
7.85 KB
00:16
Відео недоступнеДивитись в Telegram
4.46 MB
የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታልን? ~ ~ በመጀመሪያ “ይፈቀዳል” ወይስ “አይፈቀድም” በሚለው ላይ የዑለማዎች ልዩነት እንዳለ ይታወቅ፡፡ እንዲያውም ብዙሃን ዑለሞች እንደማይፈቀድ ነው የሚገልፁት፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት አትችልም ያሉ ምሁራን ሁለት መነሻዎች አሏቸው፡፡ እነሱም፡- አንዱ፡- “የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም” የሚለው ሐዲሥ ሲሆን ሁለተኛው፡- የጀናብተኛን ሁኔታ ቂያስ በማድረግ ነው፡፡ “ሁለቱም ትጥበት ወጅቦባቸዋል፤ ጀናብተኛ መቅራት ካልተፈቀደለት የወር አበባ ላይ ያለችዋም አይፈቀድላትም” የሚል ንፃሬ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት መነሻዎች ጤነኛ ናቸው ወይ? ሌሎችስ ዑለማዎች በዚህ ላይ ምን ይላሉ? ይህ አቋም ሚዛን የሚደፋ እንዳልሆነ በመግለፅ “የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን እንዳትቀራ የሚከለክላት የለም” የሚሉ ዑለማዎች ቁጥር አንድና ሁለት አይደለም፡፡ “አይፈቀድም” በሚሉ ዐሊሞች የቀረቡት ማስረጃዎችንም ጥንካሬ የሚጎድላቸው እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡ እነዚህ ዐሊሞች በዚህ ረገድ ከሚያነሷቸው ነጥቦች ውስጥ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡- 1ኛ፡- ከልካዮች ያቀረቡት የሐዲሥ ማስረጃ ደካማ ነው፡፡ በደካማ ሐዲሥ ተንተርሶ በትክክለኛ ማስረጃ ያልተከለከለን ዒባዳ መከልከል አይቻልም፡፡ ሐዲሡን፡- * ኢማሙ አሕመድ፡- “ውድቅ ነው” ብለውታል፡፡ [ተህዚቡ ተህዚብ፡ 1/283] * ኢማሙል ቡኻሪ፡- ደካማነቱን ገልፀዋል፡፡ * ኢብኑ ተይሚያ፡- ሐዲሡን “በሐዲሥ አዋቂዎች ስምምነት ደካማ ነው” ብለዋል፡፡ [አልመጅሙዕ፡ 21/460] * ኢብኑል ቀይም፡- “በሐዲሥ አዋቂዎች ስምምነት ድክመት ያለበት ሐዲሥ ነው” ብለዋል፡፡ [ኢዕላሙል ሙወቂዒን፡ 3/25] * ኢብኑ ሐጀር፡- “በሁሉም መንገዶቹ ደካማ ነው” ብለዋል፡፡ [ፈትሑል ባሪ፡ 1/323-324] * አልባኒ፡- በብዙ ኪታቦቻቸው ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ለምሳሌ፡- [ዶዒፉ ሱነን ቲርሚዚ፡ ቁ. 98] * ኢትዮጵያዊው ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም በዚህ ርእስ ላይ የሚጠቀሱት ሐዲሦች ለማስረጃነት የሚበጁ አይደሉም ብለዋል፡፡ [ዘኺራ፡ 4/570] ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ዑሠይሚንና ሌሎችም በርካታ ዐሊሞች በተመሳሳይ የሐዲሡን ደካማነት ገልፀዋል፡፡ 2ኛ፡- ከልካይ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ በጉዳዩ ላይ መሰረቱ ፍቁድነት ነው፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት በዚህ ረገድ ከሌሎች ሙስሊሞች የተለየ ብይን የላትም፡፡ እሷን ከሌሎች ለይቶ ከቁርኣን የሚከለክል ሰው ግልፅ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ እንደሚታወቀው የሴቶች የወር አበባ ማየት ከነብዩ ﷺ ዘመን በኋላ የመጣ አዲስ ክስተት ሳይሆን ጥንትም የነበረ ነው፡፡ ሆኖም ግን በዚያን ሰዓት ቁርኣን እንዳይቀሩ አልከለከሏቸውም፡፡ “እንዳልተከለከሉ ምን አሳወቀን?” ከተባለ ልክ የወር አበባ ላይ ሲሆን እንዳይፆሙና እንዳይሰግዱ የሚከለክሉ ትክክለኛ ሐዲሦች እንደደረሱን ቁርኣን እንዳይቀሩ ቢከለከሉ ኖሮም በማያሻማ መልኩ ማስረጃ ይደርሰን ነበር ማለት ይቻላል፡፡ 3ኛ፡- አላህ ቁርኣንን በመቅራት አዟል፡፡ ለሚቀራውም ሰው ትልቅ ሽልማትን ሊሸልም ቃል ገብቷል፡፡ ያለ ተጨባጭ ማስረጃ የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶችን ከዚህ ትልቅ የዒባዳ መስክ መከልከል ልክ አይደለም የሚለው ሌላኛው ይህን ሀሳብ የመረጡ ምሁራን መከራከሪያ ነጥብ ነው፡፡ 4ኛ፡- የወር አበባ ላይ ያለችን ሴት ከጀናብተኛ ጋር ማመሳሰልም ልክ አይደለም፡፡ ጀናባ ያለበት ሰው ምርጫው በእጁ ነው፡፡ ከፈለገ ታጥቦ መቅራት ይችላል፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ግን ደሙ ሲቆም እንጂ ስለፈለገች አትታጠብም፡፡ በዚያ ላይ ከጀናባ በተለየ የወር አበባ ቆይታ ቀናትን የሚፈጅ ነው፡፡ ስለዚህ ከጀናባ ጋር ማመሳሰሉ ጤነኛ ንፅፅር አይደለም፡፡ የወሊድ ደም ሲሆን ደግሞ ቆይታው የበለጠ ይራዘማል፡፡ ኢብኑል ቀይም “የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም” የሚለው ሐዲሥ ለማስረጃነት የማይበቃ ደካማ እንደሆነ በሰፊው ከተነተኑ በኋላ እንዲህ ይላሉ፡- “ሐዲሡ ሶሒሕ ካልሆነ ከልካዮች ዘንድ በጀናብተኛ ከማነፃፀር ውጭ ሌላ ማስረጃ አይቀራቸውም፡፡ በሷና በጀናብተኛ መካከል ያለው ትክክለኛ ልዩነት ሁለቱን አንድ አድርጎ ለመበየን የሚከለክል ነው፡፡ ይህም በብዙ መልኩ ነው፡፡ አንዱ ጀናብተኛ በፈለገ ጊዜ በውሃም ሆነ በአፈር መጥራት (መጧሀራት) ይችላል፡፡ ስለዚህ ከነጀናባው የሚቀራበት ምክንያት የለውም፡፡ የወር አበባ ላይ ያለችው ግን ከዚህ የተለየ ነው፡፡” ሌሎችም መለያዎችን ዘርዝረዋል፡፡ ከፈለጉ ሙሉውን ይመልከቱት፡፡ [ኢዕላሙል ሙወቂዒን፡ 3/25] 5፡- የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን እንዳትቀራ ማለት በየወሩ ለተወሰኑ ቀናት ቁርኣንን እንዳትማር፣ እንዳታስተምር፣ በመቅራት አጅር እንዳታገኝ መከልከል ነው፡፡ በዚያ ላይ ሒፍዝ ላይ ከሆነች ለመርሳት ልትጋለጥ ትችላለች፡፡ በመጨረሻም “ለመሆኑ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታል ያሉ ዑለማዎች እነማን ናቸው?” የሚል ጥያቄ ከተነሳ የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡- ★ የማሊኪያ መዝሀብ መቅራት ትችላለች የሚል ነው፡፡ [ዘኺራ ሊል ቀራ፡ 1/379] ★ የዟሂሪያም አቋም ይሄው ነው፡፡ [አልሙሐላ፡ 1/94] ★ የአሕመድም አንድ ዘገባ ነው፡፡ [አልኢንሷፍ ሊልመርዳዊ፡ 1/249] [አልኢኽቲያራቱል ፊቅሂያ ሊብኒ ተይሚያ፡ 27] ★ ከኢማሙ ሻፊዒይ በዚህ ላይ የሚፈቅድና የሚከለክል ሁለት የተለያዩ እይታዎች የተላለፉ ሲሆን አንዳንዶች የሚፈቅደው የቀድሞ አቋማቸው ነው ብለዋል፡፡ ★ የኢብኑ ጀሪር ምርጫም መቅራት ትችላለች የሚለው ነው፡፡ [ሸርሑ ሶሒሕ አልቡኻሪ ሊብኒ በጧል፡ 1/423-424] ቡኻሪ፣ ኢብኑል ሙንዚርና ሸውካኒም ይህንኑ መርጠዋል፡፡ የኢብኑ ተይሚያና የኢብኑል ቀይም አቋም ይሄው እንደሆነም አሳልፌያለሁ፡፡ ከዘመናችን ታላላቅ ዑለማዎች ውስጥ የጥቂቱን ንግግር ላቅርብ፡- ★ ኢብኑ ባዝ፡-  “የወር አበባ ላይ ላለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታል፡፡ ከዚህ የሚከለክል ግልፅ ማስረጃ ስለሌለ፡፡ ነገር ግን ሙሥሐፍ (ቁርኣን) ሳትነካ ነው፡፡ ‘የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም’ የሚለው ሐዲሥ ደካማ ነው” ብለዋል።  [መጅሙዑ ፈታዋ፡ 16/127] ★ ኢብኑ ዑሠይሚን፡- “የወር አበባ ላይ ላለች ሴት ሐጃ ሲኖር ካልሆነ በስተቀር በአንደበቷ ባትቀራ #በላጭ ነው፡፡ ለምሳሌ አስተማሪ ሆና ተማሪዎችን የምታቀራ ከሆነች ወይም በፈተና ጊዜ ተማሪዋ ለፈተናዋ መቅራት ካስፈለጋትና መሰል ጉዳዮች” ብለዋል። [መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል ኢብን ዑሠይሚን፡ 11/234] ልብ በሉ! ከውዝግብ ለመራቅ ያክል የሰጡት ምክር እንጂ መከልከላቸው አይደለም፡፡ “ባትቀራ #በላጭ ነው” አሉ እንጂ “መቅራቷ ሐራም ነው” አላሉም፡፡ ★ የሳዑዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ዑለማዎች፡- “የወር አበባና የወሊድ ደም ላይ ያለች ሴት ሙስሐፍ ሳትነካ ቁርኣን መቅራቷን በተመለከተ ከሁለቱ የዑለማዎች አቋም ትክክለኛው ችግር የለበትም የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም ይህንን የሚከለክል በተጨባጭ አልተገኘምና” ብለዋል፡፡ [ፈታዋ ለጅነቲ ዳኢማህ፡ ቁ. 3713] ፈትዋዉን የሰጡት ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ቀዑድና ዐብዱረዛቅ ዐፊፊ ናቸው፡፡
Показати все...
★ ሸይኽ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድ፡- “የወር አበባ ላይ ያለችን ሴት ከሒፍዟ ቁርኣን እንዳትቀራ የሚከለከል ማስረጃ አናውቅም” ብለዋል፡፡ [ሸርሑ ሱነን አቢ ዳውድ] ★ ኢትዮጵያዊው ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም እንዲሁ መቅራት እንደምትችል አስፍረዋል፡፡ [ዘኺራ፡ 4/570-571] ★ አልባኒና ፈርኩስም ይህንኑ መቅራት ትችላለች የሚለውን ሀሳብ ከመረጡ ዐሊሞች ውስጥ ናቸው፡፡ ማሳሰቢያ፡- እስካሁን የተወራው ቁርኣንን በእጅ ሳይነኩ በቃል መቅራትን እንጂ ሙስሐፍ መንካትን የሚመለከት አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በጓንት ወይም ጨርቅ በመያዝ ወይም እንደ ሞባይል ካሉ መሳሪያዎች ላይ የሚገኘውን የቁርኣን አፕሊኬሽን ተጠቅሞ መቅራት እንደሚቻል በርካታ የዘመናችን ዑለማዎች ገልፀዋል፡፡ ወላሁ አዕለም። (ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 19/2010)
Показати все...
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿من لم يدَعْ قولَ الزُّورِ والعملَ بِهِ، فليسَ للَّهِ حاجةٌ بأن يدَعَ طعامَهُ وشرابَهُ﴾ “የሐሰት ንግግርን በሐሰት መስራትን እንዲሁም መሀይምነትን (የመሐይማንን ተግባር) ያልተወ ሰው ምግቡንና መጠጡን ከመተዉ አላህ ጉዳይ የለውም፡፡” 📚 ቲርሚዚ ዘግበውታል: 707
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.