uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 335 підписників, посідаючи 2 651 місце в категорії Блоги та 2 347 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 335 підписників.

За останніми даними від 26 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -104, а за останні 24 години на -8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 35.99%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.61% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 158 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 808 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 30.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 27 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 335
Підписники
-824 години
-327 днів
-10430 день
Архів дописів
አቶ ዮሐንስ ቧያለው ▬▬▬▬▬▬▬ ➔ከመንግሥት በሚያገኘው ጥቅም ተደልሎ የሕዝብን ሕመም መርሳት ስላልቻለ፣ ➔የሕዝብ አገልጋይ እንጂ የበላይ አካል ተላላኪ አልሆንም ስላለ፣ ➔በሙሰኞች ከተሞላ ድርጅት
አቶ ዮሐንስ ቧያለው ▬▬▬▬▬▬▬ ➔ከመንግሥት በሚያገኘው ጥቅም ተደልሎ የሕዝብን ሕመም መርሳት ስላልቻለ፣ ➔የሕዝብ አገልጋይ እንጂ የበላይ አካል ተላላኪ አልሆንም ስላለ፣ ➔በሙሰኞች ከተሞላ ድርጅት ውስጥ ሙሥና ስላልተቀበለ፣ ➔በግልጽ ቋንቋ የመንግሥትን ድራማዎች ስላቃለለ፣ ➔ከአሞራና ጩሉሌ መሃከል ንሥር ለመሆን ስለከጀለ... በ2 መስመር ወረቀት ‹‹ተሰናብተኻል›› የተባለ… እናም… ↪️ሕዝብን ባለመርሳቱ እንደተሰናበተ ሁሉ እሱን ባለመርሳት የትኛውንም አይነት ድጋፍ ልናደርግለት ይገባል፡፡ ↪️ከትናንት ያነሰ ሕይወት እንዲኖር ባለመፍቀድ ለግለሰብ ከመታመን ይልቅ ለሕዝብ መታመን እንደሚበልጥ ማስረዳት ይገባናል፡፡ ↪️አለኝታዎች ሆነን በመገኘት ከግርድና ፍልስፍና የተላቀቁ አመራሮች መፍጠር ግድ ይለናል፡፡ ↪️በሙያው ተሰማርቶ ቤተሰብ ለማስተዳደር የሚያጠፋውን ጊዜ ለሕዝብ እንዲያውለው ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡

ፎቶ ሾፕ መስሎኝ ነበረ። ከገጹ ውስጥ ገብቼ ቼክ ሳደርግ ግን የኦሮሚያ ብልጽግና ፖርቲ በትክክለኛ አካውንቱ Like ማድረጉን ተረዳሁ። በሌላ መልኩ ደግሞ በባልደራስ ሥም በተከፈተ የሐሰት አካውንት እ
+1
ፎቶ ሾፕ መስሎኝ ነበረ። ከገጹ ውስጥ ገብቼ ቼክ ሳደርግ ግን የኦሮሚያ ብልጽግና ፖርቲ በትክክለኛ አካውንቱ Like ማድረጉን ተረዳሁ። በሌላ መልኩ ደግሞ በባልደራስ ሥም በተከፈተ የሐሰት አካውንት እጅግ አስቀያሚ ጽሑፍ ሲሰራጭ ውሏል። እናም እነዚህን ነገሮች ስናገጣጥማቸው በዛሬው ጥፋት ቅጣት የተበየነበት ፓርቲ ግልጽ የሆነ ይመስላል። እንዲህ ያለ የወረደ የፖለቲካ ጨዋታ ግን ማንንም አይጠቅምም‼️

በመንግሥት ፍላጎት እና ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ የሚካሄዱ ጥቃቶች መለያ ባሕሪያት‼️ አሳዬ ደርቤ ↪️አንድ ጥቃት ያለ መንግሥት ፍላጎት ከተከሰተ፦ ▬▬▬▬▬ ➔ጥቃቱን በአፋጣኝ የመቆጣጠርና ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ የመከላከል ሥራ ይሠራል፡፡ ➔ጥቃቱ ከመከሰቱ በፊት መከላከል በሚገባቸው የጸጥታ ኃይሎችና አመራሮች ላይ ተገቢውን እርምጃ ይወሰዳል፡፡ ➔ጥቃቱን በፈጸሙትና ባቀነባበሩት አካላት እንዲሁም በጥቃቱ ዓላማ ዙሪያ ፈጣን ምርመራ ተካሂዶ ኃላፊነት በሚሰማው መልኩ ለሕዝብ ይገለጻል፡፡ ➔በአጥፊው አካል ላይ ምርመራ ተደርጎ ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል፡፡ ➔የተፈጸመው ጥቃት ድጋሜ እንዳይከሰት ጥፋቱን እና አጥፊውን የሚያወግዙ የአደባባይ ሰልፎችና የሚዲያ ዘመቻዎች ይሰናዳሉ፡፡ ➔የተፈጠረው ጥቃት የአገርን አንድነት እና የሕዝብን አብሮነት በሚሸረሽር መልኩ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ እንዳያልፍ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ ተግባራት ይፈጸማሉ፡፡ ↪️ለፖለቲካዊ ትርፍ ተብሎ በመንግሥት አካላት የሚቀነባበር ጥቃት፦ ▬▬▬▬▬▬ ➔ከሕዝብ የሚመጣን ጥቆማ መሠረት አድርጎ ወንጀሉን በመከላከል ፈንታ የማቀጣጠል ተግባር ይፈጸማል፡፡ ወይም ደግሞ በቸልታ ይታለፋል፡፡ ➔የደረሰው ጉዳት ተቃልሎ እንደ ኦነግ ሸኔ ጥቃት እንዲድበሰበስ ወይም ደግሞ በተጋነነ መረጃ ጥቃቱ እንዲባባስ ይደረጋል፡፡ ➔በአጥፊው አካል ላይ በሚወሰድ ሕጋዊ እርምጃ ፈንታ የሆነን ሕዝብ አጥፊ፣ የሆነን ሕዝብ ጠፊ በሚያደርጉ ቅስቀሳዎች ምንም በማያውቁ አካባቢዎች ላይ የአጸፋ እርምጃ ሲካሄድ ይታያል፡፡ ➔ወንጀሉን መከላከል ባይቻለው እንኳን ወንጀለኛን አድኖ ለሕግ ማቅረብና ለሕዝብ ማሳወቅ የሚገባው መንግሥት ቸልተኛ ወይም ደግሞ ወገንተኛ ሆኖ ይከሰታል፡፡ ➔ግጭት አባባሽ ሚዲያዎችን እና የጥላቻ ንግግሮችን የመከላከል ተግባር ኃላፊነት በሚሠማቸው ዜጎች እጅ ይወድቃል፡፡ ➔በጥቃቱ በተሳተፈው ሃይል እና ጥቃቱን መከላከል ባልቻለው አመራር ላይ ሕጋዊ እርምጃ በመውሰድ ፈንታ የተጀመረው ምርመራ ተቋርጦ የፍትሕ ሂደቱ በጅምላ ፍረጃ ይጠናቃቀል፡፡ ➔በሆነ አካል ክስረትና እልቂት ላይ ፖለቲካዊ ትርፉ ከተሸመተ በኋላም ቂም በቋጠሩ ወጣቶች ፈንታ በሽማግሌዎች መሃከል የእርቅ ሥነ ስርዓት ይካሄዳል፡፡ (ጨምሩበት) Share

"ለመላው የእስልምና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በሙሉ ፥ እንኳን ለ1443ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ" እያልኩ በዓሉ በደስታና ሰላም የተሞላ ይሆን ዘንድ እመኛለሁ።
"ለመላው የእስልምና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በሙሉ ፥ እንኳን ለ1443ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ" እያልኩ በዓሉ በደስታና ሰላም የተሞላ ይሆን ዘንድ እመኛለሁ።

የኔ አማራ ይሄንን ይመስላል!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ አማራዬ ላንተ ጊዜዬን እና ሐሳቤን ቀርቶ ሕይወቴን ለመስጠት የማልሳሳው ለዚህች ‹‹መናኛ አገር›› ወርቅ አበድረህ እብቅ ስትቀበል ስለማይ እንጂ ካንተ የተፈጠርኩ የአማራ ተወላጅ ስለሆንኩ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ያህል፡- ባንድ ወቅት ባንተ እገዛ ስልጣን የያዙ ኃይሎች ወልቃይትን እና ራያን ቀሙህ፡፡ አንተ ግን በዜግነትህ እንጂ በማንነትህ ማሰብ የማትወድ ሰፊ ሕዝብ በመሆንህ ‹‹ከኢትዮጵያ ወደ ኢትዮጵያ›› በተወሰደው የራያ እና ወልቃይት መሬት በላይ ለብስጭት የዳረገህ ኢትዮጵያ ያለ ባሕር በር መቅረቷ ነበር፡፡ ከዓመታት ባንዱ ዓመትም መሬትህን እና ማንነትህን የቀሙህ ኃይሎች ‹‹መሬታችን ተወረረ›› ብለው እንደ አሸን የምትረግፍበትን ጦር ሜዳ ባድሜ ላይ አዘጋጁልህ፡፡ አንተም የእርዳታ ስንዴ ጭኖ በመጣ ኤነትሪ ተጭነህ ‹‹እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም›› እያልክ ባድሜ ላይ በመገኘት በአጥንትህ እርከን እስኪሠራ ድረስ ሕይወትህን ገበርክላት፡፡ ኢትዮጵያ ተበታትነህ የምትኖርባት አገርህ ብቻ ሳትሆን ተሰባስበህ የምትሞትላት መቃብርህ መሆኗን ገለጽክላት፡፡ ከዚያስ ምን አተረፍክ? ➔በኦሮሞ ዘንድ የተጠላህ ትሆን ዘንድ የአኖሌን ሃውልት ተክለው ጠበቁህ፡፡ ➔‹‹ጨፍላቂ፣ አሀዳዊ፣ ትምክህተኛ፣›› በሚል ማለቂያ አልባ ፍረጃ የብሔር ብሔረሰቦች ማስፈራሪያ ጭራቅ አደረጉህ፡፡ ➔ሰፋሪ›› በሚል ቃል አገርህን ቀምተው ብሔርህን አስታወሱህ፡፡ ➔ዜግነትህን ለመግፈፍ ሲጥሩ ያለህን ብቻ ሳይሆን የነጠቁህን ማንነት አስታወሱህ፡፡ ‹‹አማራን እንዳይነሳ አድርጌ ቀብሬዋለሁ›› ሲል የኖረው ሥርዓትም ስለ ወልቃይት ስታወራ የሰማ ቀን ቅስምህን የሚሰብር ሠራዊት ወደ ጎንደር አዘመተ፡፡ በኮሎኔል ደመቀ ጥይትም ደርዘኑን ሠራዊት ከምድር ላይ አጋድመህ በጥልቅ ሲታደስ የከረመው ሥርዓት መበስበሱን ይፋ አደረግክ፡፡ ‹‹የኦሮሞ ደም የኔ ደም ነው›› በሚል አቋምም ጥላቻን በፍቅር ድል ካደረግክ በኋላ በኦሮማራ ጥምረት አሮጌውን ሥርዓት አሽቀንጥረህ፣ ለለውጡ መሪ ድጋፍህን ችረህ ወደ ጎጆህ ተመለስክ፡፡ ከዚያስ ምን ሲደረግ አየህ? ➔የቲም መሪ የነበሩት ፕሬዝዳንት ስለ ዲሞግራፊ ሲያወሩ፣ እሳቸውን የተኩት ፕሬዝዳንት መስቀል አደባባይ ላይ ቆመው የአጼውን ሥርዓት እንደ እንጨት ሲሰባብሩ፣ ➔አንተን ባዕድ ሌላውን ዘመድ በሚያደርግ ንግግር 'የቡራዩና የሱልልታ ሰዎች መሪያችን ተነካ' ብለው ወደ አራት ኪሎ ሲያመሩ፣ ኦሮማራን ሲመሩ የነበሩ አክቲቪስቶች ህውሓት ስትራቴጂክ አጋራችን ናት እያሉ ሲያወሩ… ➔ወገኖችህን መጤ ተብለው በጅምላ ሲቀበሩ፣ የትግል መሪያችን ተከበበ ብለው የተቆጡ ኃይሎች ከማታውቀው ቤተ-መንግሥት አስገብተው ‹‹ዳውን ዳውን አማራ›› እያሉ ሲፎክሩ፣ በሌላ መልኩ ደግሞ ከፌደራል ከተባረረ ጊዜ ጀምሮ ‹‹አንተን በጠላትነት በሚፈርጅና የኤርትራ ሕዝብ ወንድም ሕዝብ መሆኑን በሚያውጅ መግለጫው ሲያወግዝህ የከረመው ኃይል ሰሜን እዝን መውጋቱን በጠቅላይ ሚኒስትሩ አንደበት ሲተረክ ሰማህ፡፡ ያን ጊዜም ስትገድልህ ለከረመች አገርህ ሟች ሆነህ ተገኘህ፡፡ ለሠራዊቱ ስንቅ ከማቅረብ ባለፈ በእራስህ ትጥቅ ዘምተህ በአንተ ሕልፈት የአገርን ቀጣይነት እውን አደረግክ፡፡ ከዚያስ ምን አጋጠመህ…? ➔የወለጋ እልቂት፣ የአጣዬ ጥቃት ➔ሽልማት የሚገባው ልዩ ሃይልህ በብልጽግና አመራሮች ሤራ ተገድሎ ከሚሴ ላይ አስከሬኑ ሲገተት ➔ሕይወትህን የሰጠኸው መንግሥት ጠላትህን ከባድ መሣሪያ አስታጥቆ ‹‹አፈግፍግ›› በሚል ትዕዛዝ ጦርነቱን ወደ አንተ ምድር ሲገትት… ያን ጊዜም ወገንህን ተጣርተህ ብቻህን መሆንህን ተረዳህ፡፡ ያን ጊዜም የአገርህን ሠራዊት ስትጠብቅ ጦርነት ስቦ የጣለብህ መንግሥት ‹‹በዚህ ዘመን የመስኖ መሳቢያ ጄኔሬተር እንጂ ሚኒሽር ተሸክሞ መዞር አይጠቅምም›› እያለ ሲሳለቅብህ ዐየህ፡፡ ያን ጊዜም ታናናሽ ልጆህን መከላከያ ሠራዊቱን እንዲቀላቀሉ መቀስቀሱን ትተህ ‹‹ፋኖ ሁኑ›› ማለት ጀመርክ፡፡ ከዚያስ ምን ተከሰተ? ➔‹‹ጽንፈኛ አማራን እናከስማለን›› የሚል ዛቻ ➔‹‹ፋኖ የሚባል ኢመደበኛ ኃይል ትጥቅ መፍታት አለበት›› የሚል ዘመቻ ➔አንተን ያላካተተ ድርድርና ሚስጢራዊ ውይይት ➔ሃይማኖትን መሠረት አድርጎ አንድነትህን የሚከፋፍል ጥቃት ➔አንድ ከተማ ላይ በተፈጸመ ድርጊት እንደ ሕዝብ አንተን እና ፋኖን የሚያንቋሽሽ አገራዊ ውግዘት፤ እናስ ብአዴን ሆኜ ካልተፈጠርኩ በቀር የሌላ ብሔር ተወላጅ ብሆን እንኳን በዚህ ሁሉ ጥቃትህ አለመታመም እንዴት ይቻለኛል?

« ለሀገራችን ለመሞት ምሽግ ለመስበር ስንገባ እኮ አንተ ሙስሊም አንተ ክርስቲያን አልተባባልንም። ምሽግ ሰብረንም ደማችንም የፈሰሰውም በአንድ መሬት የሙስሊሙም የክርስቲያኑም ነው። በአንድም ጉድጓድ
« ለሀገራችን ለመሞት ምሽግ ለመስበር ስንገባ እኮ አንተ ሙስሊም አንተ ክርስቲያን አልተባባልንም። ምሽግ ሰብረንም ደማችንም የፈሰሰውም በአንድ መሬት የሙስሊሙም የክርስቲያኑም ነው። በአንድም ጉድጓድ ልጆቻችን ተቀብረዋል፣ የተመታ ቁስለኛም ስናነሳ ሀይማኖቱን ጠይቀን ሳይሆን ወገንነቱን አጣርተን ብቻ ነበር። ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው በረባ ባረባው ፓለቲከኞች ጣልቃ እየገቡ አንድነታችንን ለመሸርሽር የሚፈልጉት❓ እኛ እንደሆን አትልፉ አንድ ነን‼ ላንለያይም ቃል ተጋብተናል‼ » ሸህ ጀነራል ሀሰን ከረሙ!

photo content

በሳል፣ ሚዛናዊ፣ ስሜት የማይንጠው፣ ፈተና የማይገለብጠው፣ አስተዋይ፣ ...‼️ በጣም ነው የማከብርህ‼️
በሳል፣ ሚዛናዊ፣ ስሜት የማይንጠው፣ ፈተና የማይገለብጠው፣ አስተዋይ፣ ...‼️ በጣም ነው የማከብርህ‼️

የአስከሬናችሁ ቁጥር ስድስት መሆኑ ቅር ያሰኛቸው ኃይሎች "የተገደሉት እኮ 41 ነበሩ" እያሉ መቆዘም ጀምረዋል። የእናንተን እጣ ፈንታም ለመላው የአማራ ሙስሊምና ክርስቲያን አከፋፍለው ፖለቲካ ለመሥራ
የአስከሬናችሁ ቁጥር ስድስት መሆኑ ቅር ያሰኛቸው ኃይሎች "የተገደሉት እኮ 41 ነበሩ" እያሉ መቆዘም ጀምረዋል። የእናንተን እጣ ፈንታም ለመላው የአማራ ሙስሊምና ክርስቲያን አከፋፍለው ፖለቲካ ለመሥራት እየዳከሩ ናቸው። ለእኔ ግን "በወገኖቻችሁ እጅ የጠፋችሁ ወገኖቼ" በመሆናችሁ የእናንተ ሕልፈት በባለፈው ወር በኦነግ ሸኔ ከጠፉት ሶስት መቶ ነፍሳት በላይ ሕመም ለቅቆብኛል። በሌላ ክልል ብትረግፉ ኖሮ "አማራዎች" ተብላችሁ ሞታችሁ የሚድበሰበሰው... ቁጥራችሁ የሚቀነሰው... ወገኖቼ በእራሳችሁ ቀዬ መክሰማችሁ ስቃይ ሆኖብኛል። የምታምኑት አምላክ ነፍሳችሁን በጀነት ያኑራት‼️ ከዚህ ጥፋት ጀርባ ያለው ኃይል ተጣርቶ በአስቸኳይ ለሕዝብ ይገለጽ‼️

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ‹‹ላም እሳት ወለደች፡፡ እንዳትጥለው ልጇ ሆነባት፣ እንዳትልሰው እሳት ሆነባት›› ሲባል ሰምተው ያውቃሉ? ኢትዮጵያም እርስዎን ወልዳ ሾመች፡፡ እናም በቃኝ እንዳትልዎ ወንበርዎን የማያስነኩ ብርቱ መንግሥት ሆኑባት፡፡ አሜን ብላ እንዳትገዛ ደግሞ እሳት ሆነው አቃጠሏት፡፡ እጦት ሆነው አራቆቷት፡፡ ጭንቀት ሆነው እንቅልፍና ሰላም አሳጧት፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ መጻፍ ያስፈለገኝ ሕልምዎን እና ከሕዝብ የሚፈልጉትን ነገር ለመጠየቅ ነው፡፡ ‹‹ምን እናግዝዎ?›› በማለት ፈንታ ‹‹ምን እንሁንልዎ?›› ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ለባለፉት አራት ዓመታት ‹‹በፖለቲካው ዓለም ቋሚ ጠላትም ሆነ ቋሚ ወዳጅ የለም›› በሚል የክሕደት ፍልስፍና እየተመሩ ‹‹መንግሥትን በመደገፍ፣ አገር ማትረፍ›› በሚል መርሕ እገዛ ያደረገልዎትን ሁሉ አሽቀንጥረው ሲወረውሩ ስላየሁ ስለ እገዛና ድጋፍ አላወራም፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ቤት ውስጥ ገብታ ያስቸገረችን ዐይጥ ለመያዝ የወጥመዱ ምላስ ላይ አትክልት ማስቀመጥ እንደሚያስፈልግ ሁሉ የእርስዎ መንግሥትም በአትክልት ፈንታ የሰው ልጅ ሕይወትን ከወጥመድ ላይ እያስቀመጠ አስቸጋሪ መስሎ የታየውን አካል ሲያጠምድ ነበር፡፡ በዚህም መሠረት እነ እንቶኔን ወጥመድ ውስጥ ለማስገባት የታሰበ ቀን የ86 አማራዎች ሕይወት ወጥመድ ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ የሰኔ አስራ አምስቱም ሆነ የጥቅምት ሃያ አራቱ ዘመቻ ሲካሄድም የሚፈለገው አካል ይበላቸው ዘንድ ወጥመድ ላይ የተቀመጡ ነፍሶች ነበሩ፡፡ አብዲ ኢሌንም መያዝ ሲፈለግ ከተበሉ በኋላ ‹‹የተከሳሽ ጥፋት›› የሚባሉ ነፍሶች ወጥመድ ላይ ተቀምጠው ነበር፡፡ አሁንም ይሄው ልማድ በመጠናከሩ የተነሳ ፋኖን ለመምታት የሚያስችል ጥፋትና ምክንያት ፍለጋ በርካታ ነፍሶችና እሴቶች እንዲወድሙ እየተደረገ ነው፡፡ ሆኖም ግን አልገባኝ ያለው ነገር መንግሥትዎ በአማራ ሕዝብ ላይ ይሄን ማድረግ የፈለገበት ምክንያት ነው፡፡ ማለትም ከዓመት በፊት ‹‹አገር ተደፈረች›› የሚል ጥሪ ሲያቀርቡ የአማራ ሕዝብም ልክ እንደሌሎች ኢትዮጵያውያን ሁሉ ጥሪዎን ሰምቶ ፈጥኖ በመድረስ ለአገሩም ሆነ ለወንበሩ ቀጣይትነት የሚችለውን እርዳታ አድርጎ ነበር፡፡ እርስዎ ግን በሽልማት ፈንታ ጠላት አምጥተው ከምድሩ ላይ ከዘረገፉበት በኋላ በሬሳ መሃከል ቆሞ ‹‹የአገር ያለህ›› እያለ ሲጣራ በማሳ መሃከል እየተዟዟሩ ‹‹ፈጣሪ ይሁንህ›› የሚል መልዕክት አስተላለፉለት፡፡ ወጣት ልጆቹን በመከላከያ ሠራዊትነት ካስመዘገበ በኋላ ‹‹የአገሬ ሠራዊት የት አለ?›› ብሎ ሲጠይቅ ‹‹የመጣብህ ጠላት በመደበኛ ኃይል የሚመከት ስላልሆነ ጩኸትህን አቁመህ እንደ ሕዝብ የመጣብህን ጠላት እንደ ሕዝብ መክት›› የሚል ትዕዛዝ ሰጡት፡፡ ከዚያም የመከራ ጊዜ ትምህርት ወስዶ በፋኖነት በመደራጀት እራሱን ለመከላከል ሲሞክር ደግሞ በሃይማኖት ተከፋፍሎ የሚባላበትን እና ትጥቅ የሚፈታበትን ሤራ ወረወሩለት፡፡ እኔ እምልዎት ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፦ ፋኖ እራሱንና ክልሉን ከማስከበር ባለፈ የእርስዎን ወንበር የሚመኝ አለመሆኑ እየታወቀ፣ ትጥቁን ለማስፈታት ይሄን ያህል ርቀት መጓዝ ያስፈለገው ለአማራ ሕዝብ ምን ያህል የጅምላ መቃብር ተቆፍሮ ቢጠናቀቅ ነው? ➔በወራሪው ኃይል የተፈጸመው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመትስ ከመንግሥትዎ እቅድ ጋር ሲነጻጸር አፈጻጸሙ በምን ያህል ፐርሰንት ወርዶ ቢገኝ ነው? ➔በሥልጣን ዘመንዎ ማሳካት የሚፈልጉት ሕልም እውን እንዲሆንስ ከአገሩ ሲሳደድ የከረመው የአማራ ሕዝብ ክልሉን ጥሎ ወዴ'ት ይፍለስ? የቀልብዎ እንዲደርስ በጥይትና በርሐብ ስንት ልጆቹን ቀብሮ ያልቅስ? ስንት ቤተ-እምነት እንደ ሻማ ይለኩስ? ➔ከመንግሥት የሚያገኘውን ጥቅም ቀርቶ የተነጠቀውን ሰላም ያገኝ ዘንድ ስንት ዞን ይውደምልዎት? ➔ኢትዮጵያዊነቱ፣ አማራነቱ፣ ሙሥሊምነቱ፣ ክርስቲያንነቱ ሁሉ እልቂት የሚያመጣ ጥፋት ሆኖ ከተገኘ ምን ይሁንልዎት? ከእራሱ ርሐብ በተጨማሪ የመንግስትን ጥጋብና ጭቆና መቻሉ በቂ መስሎ ካልታየዎት የአትላስን ጫንቃ ተውሶ ምን ይሸከምልዎት? በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ እያደነዘዙ በማካቬሌ አስተምህሮ አፈር ድሜ ያስበሏት አገር'ስ አንጀትዎን እንዲትበላዎት ምን ያህል ትንኮታኮትልዎት?

photo content

ከአንድ ወር በፊት ይሄን ስጽፍ "የሌለ ስጋት እየፈጠርክ ለሕዝብ አታከፋፍል" ያሉኝ በርካቶች ነበሩ። ሆኖም ግን ቦታው ቢቀየርም ሤራቸው ግን ተፈጻሚ መሆኑ አልቀረም። በተረፈ የትናንቱ ጥቃት የመጀመሪ
ከአንድ ወር በፊት ይሄን ስጽፍ "የሌለ ስጋት እየፈጠርክ ለሕዝብ አታከፋፍል" ያሉኝ በርካቶች ነበሩ። ሆኖም ግን ቦታው ቢቀየርም ሤራቸው ግን ተፈጻሚ መሆኑ አልቀረም። በተረፈ የትናንቱ ጥቃት የመጀመሪያው እንጂ የመጨረሻው ስላልሆነ የጠላትን ሤራ የሚያሳኩ ውስጣዊ ተውሳኮችን በመመንጠር አንድነታችንን ማጠንከር ግድ ይለናል። ይሄን ማድረግ ካልቻልን ግን ሁላችንም ተሸናፊዎች ብቻ ሳይሆን ጠፊዎች መሆናችን እርግጥ ነው።

እውነትን ለሚፈልጉ ብቻ‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ↪️ጥቃቱን ማን አቀነባበረው? ➔ብልጽግና ሸኔ ↪️ብልጽግና ሸኔ በዚህ ተግባር ውስጥ ለምን ተዘፈቀ? -ከአማራ ኤሊት የሚያገኘው የድምጽና የዶላር ድጋፍ ስለተቋረጠበት -ኢትዮጵያን አፈራርሶ ትንሽዬ አገር የመሥራት ሕልም ስላለው -በሰላም አየር ውስጥ መኖር የማይችል ተልካሻ ድርጅት ስለሆነ ↪️ጥቃቱን ማን ፈጸመው? - በገንዘብ የተገዛ እና በስሜት የሚነዳ መንጋ ↪️ጥቃቱን በማቀጣጠል ላይ የሚገኘው ማን ነው? -ዘረኝነት ጥንብ ናት" የሚለውን አስተምህሮ ችላ ብለው ኡስታዝ በሚል ሥም የተደበቁ ኦነጎች -በኦርቶዶክስ ሥም የሚንቀሳቀሱ የትሕነግ ተከፋዮች -የብልጽግና ሸኔ ተከፋዮች ↪️የጥቃቱ ዓላማ ምንድን ነበር? -አማራን በእምነት ከፋፍሎ መብላት -ፋኖን መምታት -በተረኛው አካል ለተማረሩ ብሔር ብሔረሰቦች "አማራ እኮ እንዲህ ነው" የሚል መልዕክት ማስተላለፍ፤ ↪️በቀጣይ በብልጽግና ሸኔ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ምን ምን ናቸው? -የአገው ሸንጎ የክልልነት ጥያቄ እንዲያነሳ ይደረጋል፡፡ -የጎንደሩ አይነት ጥቃት መልኩን ቀይሮ በወሎ ይጠነሰሳል፡፡ -ድንግርግሩን ተጠቅሞ ትሕነግ ወረራ እንዲፈጽም መንገድ ይጠረግለታል፡፡ -የቅማንት ኮሚቴ የስንቅና ትጥቅ ድጋፍ ይደረግለታል፡፡ -በኦሮሚያ ክልል አማራዎችን የማፈናቀል ተግባር ይፈጸማል፡፡ ↪️በጥቃቱ ተጎጂ የሚሆነው ማን ነው? ሙሥሊም፣ ክርስቲያን፣ ወሎ፣ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋ፣ አገው፣ ቅማንት እያለ እራሱን የሚያዳክመው የአንድ ክልል ሕዝብ ↪️ከጥቃቱ ተጠቃሚ የሚሆነው ማን ነው? ማንም ተጠቃሚ አይሆንም፡፡ ብልጽግና ሸኔም የዘር ማጥፋት ፈጽሞ ዘ-ሄግ ከመቅረብ ውጭ የሚያገኘው ትርፍ አይኖርም፡፡ #Share

ዛሬ በጎንደር ከተማ የተከሰተው አስነዋሪ ተግባር ቃላት አልባ እስክሆን ድረስ ከመጠን በላይ አሳዝኖኛል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ለሕዝብ የሚጨነቁና ከጠላት ሤራ የሚጠብቁ አመራሮች የሌሉት ክልል ገንዘብ
ዛሬ በጎንደር ከተማ የተከሰተው አስነዋሪ ተግባር ቃላት አልባ እስክሆን ድረስ ከመጠን በላይ አሳዝኖኛል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ለሕዝብ የሚጨነቁና ከጠላት ሤራ የሚጠብቁ አመራሮች የሌሉት ክልል ገንዘብ ያለው ሁሉ ገብቶ ከሚፈነጭበት መሸታ ቤት የሚለይ ባለመሆኑ... አንዳንድ ኃይሎች ወራሪ ጦር አዝምተው በጅምላ ሲያጠቁት እንደነበረው ሁሉ... አንዳንዶች ደግሞ ያለምንም ሠራዊት በእምነት ወይም በጎጥ ከፋፍለው እርስ በእርስ ቢያጫርሱት የሚገርም አይሆንም። አንድ ነገር ግን እናስታውስ... ባለፈው ሰሜን ሸዋ ድረስ መጥቶ የወረረን ሃይል በእምነት ደረጃ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ ቢሆንም የጥቃት ዱላውን ያሳረፈው ግን በሃይማኖት ከፋፍሎ አልነበረም፡፡ ትናንት ከወለጋ ሲያፈናቅለን የነበረው ሃይልም እምነትን መሠረት አድርጎ ምሕረት ሲያደርግ አልታየም። እናም ጠባቂ አመራር ባይኖረን እንኳን ከትናንት መከራችን ተምረን አንድነታችንን ማጠንከር ሲኖርብን በቀብር ድንጋይ በተነሳ ጠብ የጋራ መቃብራችንን መቆፈራችን በእጅጉ ያሳዝናል። የሟች ወገኖቼን ነፍስ ፈጣሪ ይማር!! በሕይወት ያሉትም እረኛ አልባዎች ናቸውና እርሱ ይጠብቃቸው።

አማራ‼️ አሳዬ ደርቤ (ጽንፈኛው)😆 ▬▬▬▬ ➔የወንበር ምኞት ከእሱ የራቀች ትሆን ዘንድ ‹‹እኔን መገርሰስም ሆነ ያለፈውን ሥርዓት መመለስ አይቻልም›› በሚል ጩኸት ዙፋን ላይ ባለ ኃይል የሚሳደድ ሕዝብ…. አማራ‼️ ➔ሥልጣን መያዝ የሚፈልጉ ኃይሎች ሁሉ ካልገባበት ቤተ-መንግሥት አስገብተው ‹‹የነፍጠኛው ሥርዓት ይውደም›› እያሉ የሚዘምቱበት ሕዝብ… አማራ‼️ ➔‹‹የምዕራባውያን እና የግብጻውያን ተላላኪ ሆኜ ኢትዮጵያን ሳፈርስ ከምገኝ 'እሷ ተርፋ፣ እኔ ልጥፋ›› የሚል አቋም በመያዙ የተነሳ መላላክን ሙያቸው ባደረጉ ኃይሎች ከሰማንያ ብሔሮች ሁሉ ተመርጦ ዓመቱን ሙሉ የሚታመስ ሕዝብ--- አማራ‼️ ➔ኢትዮጵያን ማድቀቅ፣ ሕዝቧን መጨፍለቅና ሐብቷን መስረቅ የሚሹ ሃይሎች ሁሉ ሥልጣን በያዙ ማግስት፣ ጸረ አማራ አቋም ያራምዱ ዘንድ በጥቅም የገዟቸውን ሃይሎች አደራጅተው የስፍራው የሚለኩሱትን ጥቃት ለመከላከል ሲሞክር ‹‹ከማን ጋር ይሆን የምትስማማው?›› የሚል ጥያቄ የሚቀርብለት ሕዝብ---- አማራ‼️ ➔ለእራሱ ቀርቶ ለሌላው መትረፍ ሲችል በሕዝብ ሥም የግል ጥቅም በሚያግበሰብሱ ቀፈታም ልጆቹ እጅ እና እግሩ ታስሮ ለጨረታ የሚቀርብ ሕዝብ---- አማራ‼️ ➔በደሉን እና ርሐቡን ችሎ ሊያኖራት ሲያስብ ጥጋብ ባናፈላት 'ባልቴት አገር' መቀመጫ ያጣ ሕዝብ---- አማራ‼️ ➔በላባቸው ያፈሩትን የአማራዎች ቤት እየወረሰ የቀበሌ ቤት ሲያደርግ ከነበረው ከደርግ መንግሥት አንስቶ እስከ ብልጽግና ድረስ ከግማሽ ክፍለ ዘመን ለሚበልጥ ጊዜ በአማራዊ ማንነቱ ተመርጦ ሲዘመትበት በግላዊ ብቃቱ ሰርቫይቭ አድርጎ የሚገኝ ሕዝብ----- አማራ‼️ ➔‹‹ትፍረስ›› የሚል ዓለም አቀፍ ውሳኔ በተላለፈባት አገር ውስጥ ምሰሶ ሆኖ በመገኘት ፈንታ ብሔርተኝነትን ተላበስ ቢገኝ ኖሮ የተለያዩ ታጣቂዎችን እያደራጁ ሲያዳክሙት የኖሩት ውጫዊ ሃይሎች ሁሉ ‹‹ከልፋት ገላገልከን›› ብለው በስንቅ እና ትጥቅ የሚያንበሻብሹት ሕዝብ…. አማራ‼️

➔በሕዝብ ሥም ለቤተሰብ ጥቅም የሚታገሉ ፖለቲከኞች በሞሏት አገር ውስጥ የእራስህንና የቤተሰብህን ድሎት ትተህ ለሕዝብ እና ለአገር ስትል የሰው ጫንቃ የማይችለውን ግፍ ስትሸከም ኖረኻል። ➔ብልጣ ብልጥ
➔በሕዝብ ሥም ለቤተሰብ ጥቅም የሚታገሉ ፖለቲከኞች በሞሏት አገር ውስጥ የእራስህንና የቤተሰብህን ድሎት ትተህ ለሕዝብ እና ለአገር ስትል የሰው ጫንቃ የማይችለውን ግፍ ስትሸከም ኖረኻል። ➔ብልጣ ብልጥነት እና እስስትነት በሚጠይቅ ፖለቲካ ውስጥ ከባድ መስዋዕትነት የሚያስከፍለውን የእውነት መንገድ ተከትለህ ጽናትን እና ላመኑበት መሞትን ለብዙዎች አስተምረኻል። ➔ስንቶች የሚመኙትን የምዕራቡ ዓለም ንቀህ፣ ብዙዎች የሚጎመዡበትን ቁሳዊ ጥቅም ወርውረህ.. እድሜህን ሙሉ ለእኩልነት እና ለነፃነት ትግል በማዋል በርካታ ዓመታትን እና በዓላትን በእስር ቤት አሳልፈኻል። እናም... ካሰብክበት ቦታ በሰላም ደርሰህ ከዘነጋኸው ቤተሰብ ጋር መልካም በዓል ታሳልፍ ዘንድ እመኝልኻለሁ የኔ ጀግና‼️

ቲሽ‼️ የፋሲካ በዓል በተቃረበበት ሳምንት ኦነግ ሸኔን አዝምቶ የሸዋ አማራዎችን የማስገደልና የማፈናቀል ሕልሙ በፋኖ ትግል የከሸፈበት አካል "ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋራሁ" እያለ ሲቦተረፍ "ቡፍፍ
+3
ቲሽ‼️ የፋሲካ በዓል በተቃረበበት ሳምንት ኦነግ ሸኔን አዝምቶ የሸዋ አማራዎችን የማስገደልና የማፈናቀል ሕልሙ በፋኖ ትግል የከሸፈበት አካል "ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋራሁ" እያለ ሲቦተረፍ "ቡፍፍፍፍፍፍ" የሚል ሳቅ ያመልጠኛል። ከሕዝብ በሚሰበሰው ግብር እና ከእርዳታ ባገኘው ዶላር የሕዝብን ችግር የሚፈቱ ፕሮጀክቶች በመተግበር ፈንታ ሙሥና ለመብላት የሚያመቹ መናኛ ተግባራትን እየፈጸመ ብሎም የሰላም እጦትን እና ድህነትን ለሕዝቡ እያሸከመ... ዳቦ ብርቁ የሆነ መቶ ሚሊዮን ርሐብተኛና በዋሻ ውስጥ መኖር የጀመረ አስር ሚሊዮን አገር አልባ ስደተኛ የፈጠረ "አሳፋሪ ሥርዓት" ጭብጥ ለማይሞሉ ዜጎች ዱቄትና ዘይት ማከፋፈሉን በሚገልጽ ዜና አድናቆት መሰብሰብ ሲያምረው የንቀት መንፈስ ልቤን ይሞላዋል።

አዲስ አበባን ከአህጉር እና ከአገር ከፍታ አውርዶ የአንድ ብሔር ለማድረግ 24/7 የሚጋጋጠውን..... ሰሜን ኢትዮጵያን በወረፋ ማውደም ምዕራብ ኢትዮጵያን እንደ መጥቀም የሚቆጥረውን.... በአንዱ አካባቢ ለሚኖረው ገበሬ ትራክተርና ኮምባይነር እያሠራጨ፣ እኩሉ ገበሬ በበሬ አርሶ እንዳይበላ የከለከለውን.... ኦነግ ሸኔን እያስታጠቀ ፋኖን የሚያሳድደውን... ቋንቋን መሠረት ባደረገ መልኩ ተገልጋይ እና ተበዳይ ሕዝብ የፈጠረውን... "ዘረኛ ሥርዓት" የሚመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አሁን በቲቪ ምን ቢሉ ጥሩ ነው? "እኛ ብልጽግናዎች አርበኞች እንጂ ብሔርተኞች አይደለንም!" 😆 አር-በኛ መሆን ዘጋኝ‼️

የጠቅላይ ሚኒስትሩን ትጥቅ የማስፈታት እቅድ ለማሳካት ለእርምጃ የሚያበቃ ምክንያት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ ትጥቅ እንዲፈቱ በተወሰነባቸው አካባቢዎች ጥቃት እና እልቂት ማቀጣጠል ግድ ይላል፡፡ ሆኖም ግን በግጭት ጠማቂው መንግሥት ‹‹ጽንፈኛው›› ተብሎ የተፈረጀው አካል ‹‹አትንኩኝ›› በሚል መርሕ እራሱን ከመከላከል ባለፈ ወደ ሌሎች ቀዬ ሄዶ የሚተናኮል ባለመሆኑ "አቃፊው" የሚሉትን የኦነግ ሃይል ወደ ጽንፈኛው አካል ለማዝመት ተገድደዋል፡፡ ስለሆነም ትናንትና እና ዛሬ ሸዋ ላይ የተሰነዘረው ወረራ አማራውን ትጥቅ ለማስፈታትና በሃይል አንበርክቦ ለመግዛት ከሚደረጉ መንግሥታዊ ሙከራዎች አንዱ ነው፡፡ መፍትሔው ደግሞ…. በተራ የሚሰነዘረውን ወረራና ጥቃት በጋራ መመከት‼️

በኦሮሚያ ፖለቲከኞች ዘንድ "የተሻልኩ ጨፍጫፊ እኔ ነኝ" የሚል ውድድር መንገሱ የአማራዎችን ሕይወትና የኢትዮጵያን ዘላቂነት አደጋ ውስጥ ከትቶታል።እስኪ አማራን በማውደም ፈንታ ሕዝባችሁን በመጥቀም ተወዳደሩ!