uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 337 підписників, посідаючи 2 647 місце в категорії Блоги та 2 350 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 337 підписників.

За останніми даними від 25 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -108, а за останні 24 години на -4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 38.62%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.61% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 538 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 808 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 26 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 337
Підписники
-424 години
-317 днів
-10830 день
Архів дописів
photo content

➔በሌሎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች ▬ኦነግ ወደ አገር ቤት የገባ ቀን 400 ጋሞዎች፣ ጉራጌዎችና አማራዎች ተጨፈጨፉ። ▬በ2013 ዓ.ም በኦነግ የተከበቡ ንጹሐን የመታደግ ዓላማ አንግበው በፖሊስ መኪና ሲጓዙ የነበሩ 20 የፌደራል ፖሊስ አባላት በቦንብ ጋይተው መንገድ ላይ ቀሩ፡፡ ▬በ2013 ዓ.ም ኮንሶ ወረዳን የወረረው የኦነግ ታጣቂ “ሥማችሁ ከአማራ ጋር ይመሳሰላል››በሚል ምክንያት ከ66 በላይ የአማሮ ተወላጆችን ጨፈጨፈ፡፡ ማሳሰቢያ ፡- ▬▬▬▬ ይህ የዘር ፍጅት መረጃ በመንግሥታዊ መዋቅር ታግዘው በድብቅ ከተፈጸሙ እልፍ አእላፍ ጭፍጨፋዎች መሀከል ሾልከው የወጡትንና በኔ ማስታወሻ ላይ የተመዘገቡትን ያካተተ እንጂ በብልጽግና ዘመን የተፈጸመውን ድምጽ የለሽ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ሊገልጽ የሚችል አይደለም፡፡ Share_post

ዘር ፍጅት የታወጀባቸው አማራዎች የጭፍጨፋ ዶሴ ሲገለጥ‼️ (አማራ የሆንክ ሁሉ ይሄንን ማንበብ ግዴታህ ነው) አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔ጃዋር መሐመድ ተከብቤያለሁ ያለ ቀን 86 አማራዎች ተገደሉ፡፡ ➔አርቲስት ሐጫሉ የተገደለ ቀን 350 አማራዎች ተጨፈጨፉ፡፡ ➔በቤኒሻንጉል ክልል በመተከል ዞን በ2013 ዓ.ም ብቻ በኦነግና በጉምዝ ታጣቂዎች 2,980 አማራዎች ሲገደሉ 411 ዜጎችን አካል ጉዳተኛ ሆኑ፡፡ 408 ሕጻናትም ወላጅ አልባ ለመሆን ሲገደዱ፣ 216,980 ዜጎች ደግሞ ተፈናቀሉ፡፡ ➔በ2012 ዓም ወደ ደንቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ያመሩ 17 ሴት ተማሪዎች ወደ ትውልድ ቀያቸው በመመለስ ላይ ሳሉ ተሰወሩ፡፡ ➔በወርሐ ጥቅምት መጀመሪያ 2013 ዓ.ም መከላከያ ሠራዊቱ እንዲወጣ በተደረገ ቅጽበት ለስብሰባ የተጠሩ ከ287 በላይ የጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቃንቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ አማራዎች አንድ እንኳን ለመሀላ ሳይተርፍ ሁሉም ተጨፈጨፉ፡፡ የክልሉ መንግሥትም የተወሰነውን አስከሬን ማንነት ቀይሮ ኦሮሞዎች ቢያደርጋቸውም ጭፍጨፋውን ግን መካድ አልተቻለውም፡፡ ➔ሚያዚያ 6 ቀን 2013 ዓ.ም ያለማንም ከልካይ ወደ ኤፍራታና ግድም ወረዳ ያመራው የኦነግ ታጣቂ አጣዬን አውድሞ ከ265 በላይ አማራዎችን ገደለ፡፡ ➔በወርሐ ሕዳር 2013 ዓ.ም ከባሕር ዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ 7 ሹፌሮች “አሊ ዶሮ” ላይ በኦነግ ታግተው ተገደሉ፡፡ ተሸከርካሪዎቻቸውም ተቃጠሉ፡፡ ➔ከሕዳር 20-21 2013 ዓ.ም፡- በምስራቅ ወለጋ ሊሙ ወረዳ አርቁምቢ መንደር በምሽት ቃጠሎ መነሳቱን የሚገልጽ እሪታ ሰምተው እሳቱን ለማጥፋት ከወጡ አማራዎች መሃከል 38 ንጹሐን ሲገደሉ በርካቶች ቆሰሉ፡፡ ➔ሕዳር 22 ቀን 2013 ዓ.ም በዚሁ ዞን እና ወረዳ ውስጥ በሪሶ ቀበሌ ከ27 በላይ አማራዎች ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ ደብዛቸው ጠፋ፡፡ ➔ጥቅምት 1 እና 2 ቀን 2013 ዓ.ም፡- በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ ከተማ 15 አማራዎች ሲገደሉ፣ ከአንድ ሺህ በላይ ደግሞ ተፈናቀሉ፡፡ በቀጣዩ ወር ታሕሳስ 1 ቀን 2013 ዓም በዚሁ ዞን ውስጥ በጊዳ አያና ወረዳ ድሬ ጎዳ ቀበሌ ከ20 በላይ አማራዎች የሞት ፍርድ ሲፈረድባቸው ከ40 በላይ ንጹሐን ደግሞ ታፍነው ተወሰዱ፡፡ ➔ታሕሳስ 2 ቀን 2013 ዓ.ም፡- በሆሮ ጉድሩ ዞን አባይ ጮመን ወረዳ የፊንጫ ስኳር ፋብሪካን የሸንኮራ እርሻ በእሳት ያጋየው የኦነግ ታጣቂ በአካባቢው ያገኛቸውን የአማራ ተወላጅ የሆኑ 7 አዛውንቶችን በጥይት ደብድቦ ገደለ፡፡ ታሕሳስ 7 ቀን ደግሞ በሆሮ ጉድሩ ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ በከካ በሚባል አካባቢ የአቶ ባይሌና የአቶ እንደሻው ስድስት ቤተሰቦች በጅምላ ሲያልቁ ሌሎች አማራዎችም ተጎዱ፡፡ ➔ከየካቲት 27-28/ 2013 ዓ.ም፡- በሆሮ ጉድሩ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ደቢስ ቀበሌ ሕጻናትን ሳይቀር በቀጠፈ ጭፍጨፋ ከ50 በላይ አማራዎች ተገደሉ፡፡ ይሄውም መረጃ በቁጥር ብቻ ሳይሆን በሥም ዝርዝር ጭምር ተደግፎ ሶሻል ሚዲያ ላይ የወጣ ቢሆንም በመንግሥት በኩል ግን የተባለ ነገር አልነበረም፡፡ ➔በወርሐ መጋቢት 2013 ዓ.ም፡- የኒጀርና የማዳጋስካር ብሔራዊ ቡድኖች ባደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 በመውጣታቸው የተነሳ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጠሪያ ማለፏን የሰሙ ኢትዮጵያውያን በደስታ ሲንሳፈፉ፣ በዚያው ምሽት የኦነግ ታጣቂ በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ ሰዴቃ እና ሎንቺሳ ቀበሌዎች ውስጥ በሰነዘረው ጥቃት ከ170 በላይ አማራዎች ተጨፈጨፉ፡፡ የኦሮሚያና የአማራ ክልል መንግሥታትም የኀዘን መግለጫ አስተላለፉ፡፡ ➔ነሃሴ 12 ቀን 2013 ዓ.ም፡- በኦነግ ሸኔ ጥቃት ከ350 በላይ አማራዎች መገደላቸው በተለያዩ ሚዲያዎች ቢገለጽም ኢሰመኮ ባቀረበው ሪፖርት ግን ከ150 በላይ ንጹሐን መገደላቸውን አረጋግጦ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የዜጎችን ሕይወት እንዲጠብቁ አሳሰበ፡፡ ይሄውም ሪፖርት ከኢሰመኮ የፌስቡክ ገጽ ላይ ይገኛል፡፡ ➔ነሃሴ 9/2013 ዓ.ም፡- በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ የኦነግ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 24 አማራዎች ሲገደሉ 10 አማራዎች ደግሞ ታግተው መወሰዳቸው የወረዳው አስተዳደሪ በሆኑት በአቶ ቡላ ደመረ አማካኝነት ተገለጸ፡፡ ➔በሌላ መልኩ ደግሞ አሸባሪው ትሕነግ ተመትቶ ከተባረረ በኋላ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በደስታ መንፈስ ሲሞላ ኦነግ ሸኔ ግን በወለጋና በሸዋ የአማራ ንጹሐንን ነፍስ ሲበላ ነበር፡፡ በወቅቱም የሚከተሉት የጥቃት ሪፖርቶች ኢሰመጎ ገጽ ላይ ወጥተው ነበር፡፡ ➔መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጅባት ወረዳ፣ ዳርጌ ቀበሌ በስድስት መንደሮች በርካታ ቤቶችና ክምሮች ተቃጥለው በሺህዎች የሚቆጠሩ መፈናቀላቸውን… በ23/4/2014 ዓ.ም በሆሮ ጉድሩ ዞን ጃርቲ ወረዳ ለገበያ የወጡ ሰባት አማራዎች ተገድለው አስከሬናቸው ተሰጥቶ መዋሉን…. በ11/4/2014 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ወረዳ መንቃት ቀበሌ ሌሊት ላይ በተፈጸመ ጥቃት 10 አማራዎች ተገድለው በማግሥቱ በአምቦ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን መቀበራቸውን…..ታሕሳስ 14/2014 ዓ.ም ደራ ከተማ እና አካባቢው ላይ በተሰነዘረ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ አማራዎች ሲገደሉ በከተማው የሚገኙ የአማራ ባለሃብቶች ደግሞ ሲዘረፉ ማደራቸውን….. ጥር 15 ቀን 2014 ዓ.ም በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ በእርሻ ማሳቸው ላይ በነበሩ ገበሬዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት የስድስት ቤተሰብ አባላት የሆኑ 14 አማራዎች መገደላቸውን የሚገልጹ ሪፖርቶች በኢሰመጎ የቴሌግራም ገጽ ላይ ይፋ ሆነው ነበር፡፡ ➔በመጋቢት ወር 2014 ዓም አባይ በረሐ ድረስ የመጣው የኦነግ ታጣቂ አራት ሹፌሮችን ገደለ፡፡ በዚያም ዘመቻው ጎሃ ጽዮን ድረስ ዘልቆ በመግባት ከ20 በላይ አማራዎችን ጨፍጭፎና በርካታ ንብረት ዘርፎ ተሰወረ፡፡ ➔በወርሐ ጥር መጨረሻ 2014 ዓ.ም አሸባሪው ኦነግ በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳማ ወረዳ 168 አማራዎችን ጨፈጨፈ፡፡ ከእነዚህም አማራዎች አስከሬን መሃከል የ87 ንጹሐን አስከሬን ባንድ ቦታ ተከምሮ መገኘቱ በመንግሥት ሚዲያዎች ሳይቀር ተላለፈ፡፡ ፊደል የቆጠሩት የአማራ ልጆችም በሁለት ቀናት ውስጥ በተጨፈጨፈው ወገናቸው ፈንታ በሁለት እግሩ የቆመ የአገው ፈረስና የአንዲት ቆንጆ ልጅ ፎቶ ይዘው “አይገርምም ወይ” ሲባባሉ ነበር፡፡ ➔በእለተ ስቅለት 2013 ዓ.ም በአንድ በአውቶብስ ወደ ጎጃም በማምራት ላይ የነበሩ ከ30 በላይ አማራዎች መንገድ ላይ ታግተው ተረሸኑ፡፡ ➔ታሕሣስ 29 ቀን 2014 ዓ.ም (የገና እለት) ደግሞ በሆሮጉድሩ ዞን የኦነግ ታጣቂ በከፈተው ጥቃት አጎቴን ጨምሮ 26 አማራዎች ባንድ ጎጆ ውስጥ ከተዘጋባቸው በኋላ በእሳት ተቃጥለው አለቁ፡፡ ➔ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም የአማራ ባንክ ሥራ በጀመረበት እለት በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ በብልጽግና ከፍተኛና ዝቅተኛ አመራሮች ድጋፍ ከ1500 አማራዎች በኦነግ ታጣቂዎች ተጨፈጨፉ፡፡ ➔ከሁለት ቀን በፊት ደግሞ በቄለም ወለጋ ሃዋ ገላን ወረዳ ለበተፈጸመ የጅምላ ፍጅት በ8 ሰዓታት ውስጥ ከ350 በላይ አማራዎች ተጨፈጨፉ፡፡

የአንጋሳ ንግግር ➔ከመደመር ፍልስፍና የተቀዳ ተራ ቲያትር ነው። ➔የበሰበሰውን የብልጽግናን ሥርዓት ለመታደግ ታስቦ የተሰናዳ ቁማር ነው። ➔ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከአማራዎች ደም ለማንፃት ታቅዶ የተሠራጬ ተውኔት ነው። ምክንያቱም... ሽመልስን ከአንጋሳ በላይ ጠሚው ያውቀዋል። ኦነግ ሸኔንም ጭምር...‼️

የአብን መግለጫ እና የዲያቆን ዳንኤል ምክር አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ እርግጥ ነው ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚሹ ውጫዊና ውስጣዊ ኃይሎች ‹‹የአገር ምሠሦ የሆነውን የአማራን ሕዝብ በማንኮታኮት የኢትዮጵያን ሕልውና ማጥፋት›› የሚል ዘመቻ ነድፈው ወደ ተግባር ገብተዋል። ይሄውም ሲሆን ሌሎች ወገኖች ኢትዮጵያ ብትፈርስ አገር ሆኖ መቀጠል የሚችል ክልል አለመኖሩን ተረድተው ‹‹አማራን በማዳከም ኢትዮጵያን ማክሰም አይቻልም›› በሚል አቋም ጥቃቱን ማስቆም ሲገባቸው ‹‹ሰሜን እዝን በመደምሰስ ኢትዮጵያን ማፍረስ›› በሚል ፉከራ የተጀመረውን ጦርነት ከአፋር ወንድሙ ጋር አስረክበውት እንደከረሙ ሁሉ… የኦነግን፣ የግብጽን፣ የሱዳን እና የምዕራባውያንን መንግሥታት የጥቃት በትርም ተቋቁሞ በእሱ ሕልፈት ያገርን ቀጣይነት ያረጋግጥ ዘንድ ለብቻው አሸክመውታል፡፡ አንዳንዶቹም ከአብራካቸው የወጣ አሸባሪ ሲጨፈጭፈው ‹‹በለው›› እያሉ ያበረታቱ ይዘዋል፡፡ ይሄም በሆነ ጊዜ አማራው ‹‹ለጊዜው ያለኝ አቅም እራሴን ከመከላከል አልፎ አገሬን ለመታደግ የሚያስችለኝ ስላልሆነ በማንነቴ በምገደልባት ፈንታ በዜግነቴ የምሞትላት አገር እውን እስክትሆን ድረስ የኢትዮጵያ ጉዳይ አያገባኝም›› በሚል አቋም እራሱን የማትረፍ ትግል ውስጥ መግባት የሚገባው ቢሆንም... የዲያቆን ዳንኤል ምክርና የአብን መግለጫ ግን የአማራዎች የጅምላ መቃብር የሆነችውን አገር ለማትረፍ የሚጋጋጥ ሆኗል፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ደህንነታቸው ተጠብቆ በመኖር ላይ የሚገኙትን ክልሎች ይህቺ አገር የአማራ ብቻ አለመሆኗን ማስገንዘብ ሲገባቸው ሰለባውን ሕዝብ ይጀነጅኑት ይዘዋል፡፡ መንግሥት ተብየው አካል የንጹሐንን ሕይወት መጠበቅ ካልቻለ ሥልጣኑን ያስረክብ" የሚል ግልጽ አቋም በመያዝ ፈንታ የጅምላ ፍጅቱን ዓላማ እና የአሸባሪዎችን እቅድ ለአማራ ሕዝብ በማስረዳት ጫንቃውን ያደነድን ዘንድ መምከር መርጠዋል፡፡ እኔ ግን እንደ አንድ አማራ የሚከተለውን እላለሁኝ…. ➔በመላው ኢትዮጵያዊ ገንዘብ የተሠራው የዓባይ ግድብ ለመላው ኢትዮጵያውያን ብርሐን የሚያመነጭ እንጂ ለአማራ ሕዝብ ጨለማ የሚረጭ እንዲሆን አልፈቅድም፡፡ ➔በሱዳንና በግብጽ የሚደገፍ የጉምዝ ታጣቂ በእራሱ ክልል ውስጥ የተሠራውን ግዙፍ ፕሮጀክት ለማደናቀፍ አማራን ሲጨፈጭፍ እያየሁ ‹‹በውሃ መሞላት የሚገባው ግድብ በአማራዎች ደም ይሞላ›› አልልም፡፡ ቤኒሻንጉል አገርህ አይደለም ተብሎ ከመተከል ሲፈናቀል የከረመውን ሕዝብ ‹‹ግድቡ ያንተ ስለሆነ የውሃ ሙሊቱ እስኪጠናቀቅ ጠንክረህ እለቅ›› በማለት አልመከርም፡፡ ➔አገር መውደዱ አገራዊ ጥላቻ አምጥቶበት በየስፍራው ደሙ ሲፈስስ እየተመለከትኩ በጥልቅ ትንታኔ ወደ ጥልቅ መቃብሩ ልሸኘው አልሻም፡፡ ➔አገር ሊያፈርስ ወንበር ላይ የተቀመጠ መንግሥት የአማራን የአገር ፍቅር እንደ ድክመት ተጠቅሞ አራት ዓመት ሙሉ ‹ሲቆምር መኖሩን እያወቅኩ፣ እንዲሁም ‹‹አማራ ይወደም፣ ኦሮሚያ ትቅደም›› በሚል የጠላት አስተሳሰብ አገር ሲመራ እያየሁ… ‹‹በአማራዎች ደም ኢትዮጵያ ትቅደም›› የሚል መፎክር አላቀነቅንም፡፡ ➔ከሕዝብ ጉያ ተደብቆ በወለጋ ጫካዎች ውስጥ አማራዎችን የሚጨፈጭፈውን አሸባሪ ወደ ግብጽ ሸኝቼ የካይሮን መንግሥት ተጠያቂ አላደርግም፡፡ ➔‹‹አገር ማለት ሰው ነው›› እንደሚባለው ቅድሚያ ወገኔን አትርፌ አገሬን ቀጣይ አጀንዳ አደርጋለሁ እንጂ በአገራቸው ሕልውና ላይ የሚደራደሩ አሸባሪዎች በውጫዊ ኃይሎችና በመንግሥት ድጋፍ ሲጠናከሩ እያየሁ… ስለ አገራዊ ታማኝነት አላወራም፡፡ ‹‹የአባይ ውሃ እንዳይፈስስ የአማራ ደም ይፍሰስ›› የሚል ውሳኔ አላስተላልፍም፡፡ ➔ይልቅስ ለጉምዝ ታጣቂዎች፣ ለኦነግ እና ለትሕነግ አሸባሪዎች የበጀት ድጋፍ በማድረግ አማራን የምታስጨፈጭፈው በአሜሪካ የምትታገዘው ግብጽ ከሆነች…… አማራዎች እሪሪ ሲሉ ኢትዮጵያ እልልታዋን ካቀለጠች….. እንዲሁም ደፋሪዋን አበርትታ- ዳር ድንበር ጠባቂዋ ላይ ከዘመተች…. ‹‹ተላላኪውን ትተህ ላኪው ጋር አንተም ተደራደር›› እላለሁ እንጂ ‹‹የዘር ፍጅት ላወጀችብህ አገር ታማኝ ሆነህ በጅምላ ተቀበር›› የሚል ብይን አላስተላልፍም፡፡ ‹‹ሩቅ አሳቢ›› መሆኔን ለማሳየት ስል ‹‹ቅርብ አዳሪ›› ይሆን ዘንድ የተፈረደበት ሕዝብ ላይ አልፈላሰፍም፡፡ ይሄው ነው‼️

ይሄ ሰውዬ!! ******** ➔ኦነግን ከእነ ትጥቁ አስገብቶ ተጨማሪ ወጣቶችን የሪፑብሊክ ጋርድ ጠመንጃ ያስታጠቀ፤ ➔ያደራጀውን የሽብር ድርጅት ሥም "ሸኔ" በሚል ባለቤት አልባ ሥም የደበቀ፤ ➔የሮዋን
ይሄ ሰውዬ!! ******** ➔ኦነግን ከእነ ትጥቁ አስገብቶ ተጨማሪ ወጣቶችን የሪፑብሊክ ጋርድ ጠመንጃ ያስታጠቀ፤ ➔ያደራጀውን የሽብር ድርጅት ሥም "ሸኔ" በሚል ባለቤት አልባ ሥም የደበቀ፤ ➔የሮዋንዳን የጭፍጨፋ ታሪክ በኢትዮጵያ ምድር ለመድገም የሚያስችል ሞት የማለማመድ ተግባር ውስጥ የተዘፈቀ፤ ➔የአማራዎችን ሕይወት ከአትክልት በታች ያወረደ፤ ➔አገር የማፍረስ ተልዕኮ ይዞ ወደ ሥልጣን የመጣ፤ ➔በአማራ ላይ የጥላቻ ስብከትን በግልጽ የሚያስተላልፉ ኃይሎችን ከመፍጠር አልፎ፣ እራሱም የጥላቻ መምህር ሆኖ ባስተላለፈው ስብከት አማራዎችን ለእልቂት የዳረገ፤ ➔አገሪቷን ቀርቶ አንደበቱን መቆጣጠር የማይችል፤ ➔ስንቱን የአማራ ክልል አመራር አሽቀንጥሮ ሲጥል የሽመልስ አብዲሳን ካቢኔ የማይሻር አድባር ያደረገ፤ ➔ብአዴን የተባለውን ድርጅት በሆዳሞች ሞልቶ ያለ ጠባቂ የሚጨፈጨፍ ሕዝብ የፈጠረ፤ ➔ስልጣኑን መልቀቅ ብቻ ሳይሆን በዘር ማጥፋት ወንጀል መጠየቅ የሚገባው፤

በወለጋ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከመሪ እስከ ተመሪ ባለው ፍጡር ስምምነት የሚፈጸም ነው!
+1
በወለጋ የሚካሄደው ጭፍጨፋ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከመሪ እስከ ተመሪ ባለው ፍጡር ስምምነት የሚፈጸም ነው!

ሰበር ዜና ጠብቅ‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ባለፈው ወለጋ፥ በአረመኔ አፈሙዝ፥ ሺህ ነፍስ ሲረግፍ ልማድ በመሆኑ፥ ቁጣን ማረሳሳት፥ ተቃውሞን መጥለፍ እኩሉ አረመኔ፥ ከለቅሶኛው መሀል፥ በላይን ሰወረ እኩሉ
ሰበር ዜና ጠብቅ‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ባለፈው ወለጋ፥ በአረመኔ አፈሙዝ፥ ሺህ ነፍስ ሲረግፍ ልማድ በመሆኑ፥ ቁጣን ማረሳሳት፥ ተቃውሞን መጥለፍ እኩሉ አረመኔ፥ ከለቅሶኛው መሀል፥ በላይን ሰወረ እኩሉ ሤረኛ፥ ጭፍጨፋ ሊያስረሳ፥ሱዳን ገብቶ አደረ በፈጠራ ዜናም፥ የጎንደር ገበሬን፥ መጨፍጨፍ ጀመረ። ዛሬ ከዚያው ጫካ፥ እልፍ አእላፍ አማራ፥ ሲረሸን በጅምላ በካድሬዎች ዜና፥ የሰው ደም ጠጥቶ፥ የዓባይ ግድብ ሞላ። በዘር ፍጅት አዋጅ ፥ በሺህ የሚቆጠር ፥ አማራ እንዳለቀ ተሜ በዋስ ወጣ ፥ በላይ ተለቀቀ። እናም እልኻለሁ… በዚች የደም መሬት እንደ ወገኖችህ ፥ በየተራ እስክታልቅ ፍትሕን ተውና ፥ ሞት የሚያለማምድ ፥ ሰበር ዜና ጠብቅ።

photo content

ከዚህ በኋላ ኢዜማን እንደ ተፎካካሪ ፓርቲ ቆጥረህ አብረህ ከቀጠልክ በቀጣይ የሚኖርህ የትግል ሕይወት "የአራት ኪሎ ዘበኛ" እንጂ "ፖለቲከኛ" ተብሎ የሚፃፍ አይሆንም። እናም ከዚህ ተለጣፊ ፓርቲ ወጥ
ከዚህ በኋላ ኢዜማን እንደ ተፎካካሪ ፓርቲ ቆጥረህ አብረህ ከቀጠልክ በቀጣይ የሚኖርህ የትግል ሕይወት "የአራት ኪሎ ዘበኛ" እንጂ "ፖለቲከኛ" ተብሎ የሚፃፍ አይሆንም። እናም ከዚህ ተለጣፊ ፓርቲ ወጥተህ ምክንያታዊ ትግል የምታካሂድበትን ጠንካራ ድርጅት መሥርት!!

ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔በአማራዎች ላይ የሚፈጸሙትን የዘር ፍጅት ወንጀሎች በሥማቸው በመጥራት ፈንታ ‹‹በንጹሐን ወይም ደግሞ በኢትዮጵያውያን ላይ የተሰነዘሩ
ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔በአማራዎች ላይ የሚፈጸሙትን የዘር ፍጅት ወንጀሎች በሥማቸው በመጥራት ፈንታ ‹‹በንጹሐን ወይም ደግሞ በኢትዮጵያውያን ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች›› በሚል ሥያሜ ማድበስበስ ጥቃቱን እንደመጋረድና እንደ መካድ አይቆጠርም ወይ? ➔በወለጋ የተፈጸመውና በሺህ የሚቆጠሩ አማራዎችን የፈጀው ጥቃት የኀዘን ቀን ሳይታወጅለት፣ ዜጎችና ሚዲያዎች ሳያወግዙት፣ ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ አመራሮች ተጠያቂ ሳይሆኑበት እንዲሁም ዘላቂ መፍትሄ ሳይበጅለት እንደ ሌሎች ጥቃቶች ሁሉ ተደብስብሶ ማለፉ በቀጣይ ጊዜያት በስፋት የሚጨፈጨፉ አማራዎች መኖራቸውን አይነግርዎትም? ➔ከተባበሩት መንግሥታት በኩል የቀረበው የወለጋውን ጥቃት የማጣራት ጥያቄ በመንግስት በኩል ተቀባይነት አለማግኘቱ የአማራዎች የጅምላ መቃብር በመንግሥት መዋቅር የሚቆፈር መሆኑን አያመለክትም? ➔ኦነግ ሸኔ ስለሚባለው አሸባሪ ማንነትና ባለቤት የእርስዎ ተቋም ቢጠየቅ በቂ መልስ አለው ብለው ያምናሉ? ➔በእርስዎ የሚመራው ተቋም በተለያዩ ስፍራዎችና ጊዜዎች የደረሱትን ጥቃቶች አጣርቶ ባቀረበው ሪፖርት መሠረት ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸውና ጥቃቱን በማስፈጸማቸው ሕጋዊ እርምጃ የተወሰደባቸው የመንግሥት አመራሮችም ሆኑ የሽብር ድርጅት መሪዎችን ያውቃሉ? ➔የኢሰመኮ ሪፖርቶች ካለፈው የዘር ማጥፋት ወንጀል ተነስተው የመጪውን ጊዜ ስጋት ይፋ በማውጣት ፈንታ ግልጹን- መደባበቃቸውና ሐቁን-መሸፋፈናቸው ተቋሙን የዘር ማጥፋት ወንጀሉ ተባባሪ አያደርገውም ብለው ያስባሉ? ➔በመጨረሻም ኢሰመኮ የተባለው ተቋም ባይኖር እስካሁን ከተፈጸመው በላይ የሚፈጸም ጭፍጨፋ ይኖር ነበር? በንጹሐን ላይ ካንዣበበው ስጋት አንጻር ሲመዘንስ በእርስዎ የሚመራው ተቋም ኃላፊነቱን ባግባቡ እየተወጣ ነው ብለው ያምናሉ?

ግድያን በመቃወማቸው የተገደሉ!
ግድያን በመቃወማቸው የተገደሉ!

ትናንት "ዲያስፖራ" እያልክ ስታልበውና ስትበዘብዘው የኖርከው ማሕበረሰብ "አማራ" መሆኑን የምታረጋግጥበት ቀን ደርሷል። የብአዴን ሰንሰለት ተብትቦ ስለያዘው እንጂ ለአገር ሲል ተሸክሞህ የከረመው ሕዝ
+3
ትናንት "ዲያስፖራ" እያልክ ስታልበውና ስትበዘብዘው የኖርከው ማሕበረሰብ "አማራ" መሆኑን የምታረጋግጥበት ቀን ደርሷል። የብአዴን ሰንሰለት ተብትቦ ስለያዘው እንጂ ለአገር ሲል ተሸክሞህ የከረመው ሕዝብ ከልቡ ውስጥ አውጥቶ ወርውሮኻል።

ወንድማችንን ያፈኑት የአንድ ሳምንት የፌስቡክ አጀንዳ ሰጥተው የወለጋውን እልቂት ማረሳሳት ስለፈለጉ ነው። እናም ዓላማቸውን ካሳኩ በኋላ ዐይኑን በጨርቅ ሸፍነው ካፈኑበት ቦታ ላይ ጥለውት ይመለሳሉ።
ወንድማችንን ያፈኑት የአንድ ሳምንት የፌስቡክ አጀንዳ ሰጥተው የወለጋውን እልቂት ማረሳሳት ስለፈለጉ ነው። እናም ዓላማቸውን ካሳኩ በኋላ ዐይኑን በጨርቅ ሸፍነው ካፈኑበት ቦታ ላይ ጥለውት ይመለሳሉ። ባለህበት ሰላም ሁን ወንድማለም‼️

photo content

በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ ተፈትቶ የነበረው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከመንገድ ላይ ተይዞ ወደ ሌላ እስር ቤት መዛወሩን ስትሰማ ሥልጣን ላይ ያለውን አካል "መንግሥት" ብሎ መጥራት ይዘገንንኻል። ጽናቱን ይስጥ
በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ ተፈትቶ የነበረው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከመንገድ ላይ ተይዞ ወደ ሌላ እስር ቤት መዛወሩን ስትሰማ ሥልጣን ላይ ያለውን አካል "መንግሥት" ብሎ መጥራት ይዘገንንኻል። ጽናቱን ይስጥህ ወንድማለም‼️

ወንድሞቻችን በ30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። የበለጠ ብርቱ ሆነው እንደሚወጡ አልጠራጠርም‼️
+1
ወንድሞቻችን በ30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። የበለጠ ብርቱ ሆነው እንደሚወጡ አልጠራጠርም‼️

መዝግቡት‼️ አሳዬ ደርቤ ከዚህ በፊት "አማራ የሚባል ሕዝብ የለም" የሚሉ ፖለቲከኞች አጋጥመውን ነበር። ዛሬ ደግሞ የአማራን ሕልውና የሚክድ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ለማየት በቃን። 😆 አጃኢብ እኮ
መዝግቡት‼️ አሳዬ ደርቤ ከዚህ በፊት "አማራ የሚባል ሕዝብ የለም" የሚሉ ፖለቲከኞች አጋጥመውን ነበር። ዛሬ ደግሞ የአማራን ሕልውና የሚክድ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ለማየት በቃን። 😆 አጃኢብ እኮ ነው‼️ የሆነው ሆኖ... ይህ ሰውዬ በአማራ ሕዝብ እጣ ፈንታ ላይ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ፍርድ በማስተላለፍ ላይ ይገኛል። ለማስረጃም ያህል፦ ➔እነ በረከት ስምዖንን በሚያስናፍቅ መልኩ 12 ሺህ ፋኖዎችን ከእስር ቤት አጉሮ ያለምንም ሕጋዊ እርምጃ እያሰቃያቸው ነው። ➔እልፍ አእላፍ የአማራ አክቲቪስቶችን እና ጋዜጠኞችን አፍኖ የአማራን ሕዝብ ለዘላለማዊ ባርነት እየሸጠው ነው። ➔የክልሉን ዩኒቨርሲቲዎች በጥይት ተኩስ የሚናጡ የጦር ሜዳ እያደረጋቸው ነው። ➔የተጨፈጨፉትን አማራዎች ማንነት ነጥቆ የጌቶቹን ማንነት ሊያወርሳቸው እየተፍገመገመ ነው። ➔እነ ዘመነ ካሴን ጨምሮ በርካታ ጀግኖችን ገድሎ ለአራት ኪሎ መንግሥት አስከሬናቸውን በስጦታ መልክ ሊያበረክት የተወለደበትን የጎጃም ምድር በጦር መሳሪያ እያመሠው ነው። እናም.... ይህ ሕሊናውን የሸጠ ተላላኪ ሰውዬ "የአማራን ሕዝብ ከዚህ በላይ ማሰቃየት አትችልም" ሊባል ይገባዋል።

በግፍ ለተጨፈጨፉ ወገኖቻችን ድምፅ እንሁን‼️ =================== 1. ብሔራዊ የሀዘን ቀን ይታወጅ። 2. ሰንደቅ ዓላማው ዝቅ ብሎ ይውለብለብ። 3. መንግሥት ለድርጊቱ ኃላፊነት በመውሰድ
በግፍ ለተጨፈጨፉ ወገኖቻችን ድምፅ እንሁን‼️ =================== 1. ብሔራዊ የሀዘን ቀን ይታወጅ። 2. ሰንደቅ ዓላማው ዝቅ ብሎ ይውለብለብ። 3. መንግሥት ለድርጊቱ ኃላፊነት በመውሰድ ይቅርታ ይጠይቅ። 4. ጨፍጫፊዎች በአስቸኳይ ለህግ ይቅረቡ። 5. ለጥቃቱ ሰለባዎች ካሳ ይሰጥ። 6. ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ ባለሥልጣናት በህግ ይጠየቁ። ⛔️ መንግሥት ሆይ ! ጥያቄዎቻችንን በአስቸኳይ መልስ። ሀገርና ህዝብ የጣለብህ ፣ ከየትኛውም መንግሥት የሚጠበቅ ትንሹ ግዴታህ ነው።

ጥያቄ? አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ እኔ እምለው... በጀት እና ሥልጣን-የጨበጠ ልጁ- በዲናር ሲሸጠው እኔን አሳጥቶ- ‹‹ወገኔ›› የሚባል ሕዝብ፥ ያስታቀፈኝ ማነው? እኔ እምለው... ይሄን አፈር ገፊ- እንደ
ጥያቄ? አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ እኔ እምለው... በጀት እና ሥልጣን-የጨበጠ ልጁ- በዲናር ሲሸጠው እኔን አሳጥቶ- ‹‹ወገኔ›› የሚባል ሕዝብ፥ ያስታቀፈኝ ማነው? እኔ እምለው... ይሄን አፈር ገፊ- እንደ አብራኬ ክፋይ ስለምን ወደድኩት ፥ ከወለድኩት በላይ? እኔ እምለው… እንደ ገነት በለስ፣ እንደ ቴምር ፍሬ፣ ሞት የጣፈጠው ሕዝብ ገዳዩን ታቅፎ- በሳንጃ በአፈሙዝ- ደሙ ሲንጠባጠብ ለምን ይሆን እኔ የሚያቅለሸልሸኝ- የምበላው ምግብ፡፡ እኔ እምለው… የሚጠለልበት- ጎጆ ቤቱ ሲጨስ- ሰቀላው ሲቃጠል ባገሩ አገር ጠፍቶት፥ ሰርክ ሲፈናቀል ማን ስለሆንኩ ነው- ልቤን እየቆፈርኩ፥ድንኳን የምተክል? እኔ እምለው... እግዜርና መንግሥት፤ በጥቅሻ ተግባብተው- ሞቱን ሲደግሱ ሹማምንት ልጆቹ፥ ከመቃብሩ ላይ- ቪላ ሲቀልሱ ያኔ ሕጻን ሳለን- በእንጨት መሳይ ጣቱ- በለሴ ቆራርሶ- ለልጆቹ ሲያድል፤ ከሁሉም ከፍ አርጎ- የቸረኝ ይመስል ለምንድን ነው እኔ ሞቱ የሚረብሸኝ- የገደልኩት ያህል? (በጣም ነው የምወድህ አማራዬ!)