uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 333 підписників, посідаючи 2 647 місце в категорії Блоги та 2 350 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 333 підписників.

За останніми даними від 25 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -108, а за останні 24 години на -4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 38.62%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.61% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 538 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 808 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 26 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 333
Підписники
-424 години
-317 днів
-10830 день
Архів дописів
Share አድርገው!! በወለጋ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን መንግሥት እስከፈቀደላቸው ቀን ድረስ ኖረው ተጨፈጨፉ፡፡ በሰዓታት ጥቃትም ከሰባት መቶ በላይ ንጹሐን ተቀጠፉ፡፡ ይሄው አካል በሰጠን ነጻነት ል
Share አድርገው!! በወለጋ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን መንግሥት እስከፈቀደላቸው ቀን ድረስ ኖረው ተጨፈጨፉ፡፡ በሰዓታት ጥቃትም ከሰባት መቶ በላይ ንጹሐን ተቀጠፉ፡፡ ይሄው አካል በሰጠን ነጻነት ልክ የምንንቀሳቀሰው ብሎም በተፈቀደልን መጠን ልክ ኀዘናችንን የምንገልጸው እኔ እና አንተ ደግሞ ወገኖቼን አስጨፍጭፈኻል ተብሎ ሊወገዝ የሚገባው አካል ጥቃቱን እንዲያወግዝልን እና የኀዘን ቀን እንዲያውጅልን በመለማመጥ ላይ እንገኛለን! የለም የለም ወንድማለም! በቁጥር ሲሰላ ከአንድ ቀበሌ ነዋሪ የሚበልጥ ሕዝብ የተጨፈጨፈበትና የዓለም ሚዲያዎች ‹‹የሰው ልጅ እንደ ዶሮ መቀላቱን ገልጸው ያወገዙት ጥቃት የደረሰበት አካል ወደ አደባባይ ወጥቶ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ኀዘኑንም ሆነ ተቃውሞውን መግለጽ መብቱ ብቻ ሳይሆን ግዴታውም ጭምር ነው፡፡ ስለዚህ የሱፍ ኢብራሒም እንዳለው የታወጀብንን የዘር ማጥፋት ለማስቆም ጠንካራ ትግል የሚጠይቅ ቢሆንም ይሄን ትግል ግን ሰላማዊ በተቃውሞ ሰልፍ መጀመር ይኖርብናል፡፡ እንዲህ አይነት ሐሳብ ሲመጣ የተቃውሞ ሰልፍ ትርጉም አልባ መሆኑን የሚነግሩን ኃይሎች ዋነኛ ዓላማ የታወጀብን ማለቂያ የለሽ እልቂት በፌስቡክ ፖስት ተወስኖ እንዲቀር ማድረግ ነውና እነሱን ሳትሰማ ለሟች ወገኖቻችን ኀዘናችንን፣ ለገዳዮቹ ደግሞ ቁጣችንን የምንገልጽበት የአደባባይ መድረክ መፍጠር ግድ ይለናል፡፡ ሼር እና ፖስት በማድረግ ለሌሎች አጋሩት፡፡

photo content

ባለፈው "አውራ ጎዳና ቀበሌ ላይ ወራሪዎች ተገደሉ" በሚል ዘገባ ነጠላውን ዘቅዝቆ በCGTN ሲያለቅስ የነበረው ይሄ ዘረኛ ጋዜጠኛ 700 ንጹሐን ሲያልቁ ምነው ድምጹን አጠፋ? ከትልቅ ቦታ የተቀመጠ ት
ባለፈው "አውራ ጎዳና ቀበሌ ላይ ወራሪዎች ተገደሉ" በሚል ዘገባ ነጠላውን ዘቅዝቆ በCGTN ሲያለቅስ የነበረው ይሄ ዘረኛ ጋዜጠኛ 700 ንጹሐን ሲያልቁ ምነው ድምጹን አጠፋ? ከትልቅ ቦታ የተቀመጠ ትንሽ ሰው‼️

ሕዝብ ጋር ብሽሽቅ የገጠመ ብሽቅ መሪ
+1
ሕዝብ ጋር ብሽሽቅ የገጠመ ብሽቅ መሪ

photo content

photo content

"በከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት የሆኑ 14 ሰዎች በኦነግ ሸኔ ተገደሉ" ተብሎ በመንግሥት ሚዲያዎችና አመራሮች የተገለጸው ውሸት ነው። ሰዎቹ የተገደሉት በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ነው" የኢሰመኮ ሪፖርት
"በከረዩ የሚችሌ ገዳ አባላት የሆኑ 14 ሰዎች በኦነግ ሸኔ ተገደሉ" ተብሎ በመንግሥት ሚዲያዎችና አመራሮች የተገለጸው ውሸት ነው። ሰዎቹ የተገደሉት በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ነው" የኢሰመኮ ሪፖርት‼️

"ኦነግ ሸኔ የሚባለው ነፍሰ ገዳይ ቡድን በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ያለ ነው። መንግሥት ነገሮችን ለማወሳሰብ ሲል እራሱ የፈጠረው ኃይል ነው። ለዚያም ነው በጠራራ ጸሐይ በከባድ መሳሪያ ንጹሐንን ገድሎ
"ኦነግ ሸኔ የሚባለው ነፍሰ ገዳይ ቡድን በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ያለ ነው። መንግሥት ነገሮችን ለማወሳሰብ ሲል እራሱ የፈጠረው ኃይል ነው። ለዚያም ነው በጠራራ ጸሐይ በከባድ መሳሪያ ንጹሐንን ገድሎ ሲሄድ ማንም የማይዘው!" ኦቦ ቀጀላ ባንድ ወቅት ለአሐዱ ኤፍ ኤም ከተናገረው‼️

photo content

ለበለጠ ሞላ‼️ ▬▬▬▬ እንደወረደ የፃፍከውን የወረደ ጽሑፍ አንብቤ የሚከተለውን እላለሁ። ወለጋ ምድር ላይ "አማራ" በሚባል ማንነት እንጂ "ወሎዬ" በሚል መስፈርት የተጨፈጨፈ ሕዝብ የለም። ሲቀጥል ደግሞ በጠቀስካቸው ቦታዎች የወሎ አማራ ሲጨፈጨፉ የሸዋ፣ የጎጃምና የጎንደር አማራ ሊተርፉ የቻሉት ቦታው ላይ ባለመስፈራቸው ነው። አንተ እና እኔም ሳንጨፈጨፍ የቀረነው ጊምቢ ላይ ስላልተገኘን ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘም በአማራ ክልል ውስጥ ያሉ አብዛኞቹ ዞኖች ሲወረሩ የጎጃም አማራ የተረፈው ከአሸባሪው ቀጠና ጋር ባለመጎራበቱና የጎንደር ወንድሙ "በእኔ ምድር ላይ ተሻግረህ ወደ ባሕር ዳር አትሄድም" በሚል አቋም ወራሪውን ደብረ ታቦር ላይ በመመከቱ ነው። እናም እልኻለሁ... "አማራዎች" ተብለው የተገደሉ ወገኖችን ወደ "ወሎዬዎች" ምድብ አውርዶ የጋራ ኀዘንን በዞን መሸንሸን ከኦነግ እንጂ ከአብን አመራር አይጠበቅም። በዚያ ላይ ደግሞ ሐሳብህ መላውን አማራ ለአደጋ ከመዳረግ አልፎ ለወሎ ሕዝብ የሚያመጣለት ጸጋ የለም። የድሮ አክባሪህ‼️

መርማሪ ኮሚሽን ይቋቋም‼️ አሳዬ ደርቤ እባላለሁ፡፡ የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ማስከበር የአንድ መንግሥት ትንሹ ግዴታ ቢሆንም ሥልጣን ላይ ያለው አካል ግን ላለፉት ሦስት ዓመታት ዜጎችን ከጥቃት ሊከላከል ቀርቶ የጅምላ እልቂትን በማቃለል ሞትን እና ግድያን የተለማመደ ሕዝብ በማፍራት ላይ ይገኛል፡፡ ከሁለት ቀን በፊትም በተፈጸመው ጭፍጨፋ የተገደሉ ንጹሐን ቁጥር ከሰባት መቶ በላይ መድረሱ ቢነገርም መንግሥት ተብየው አካል ግን የአገር ውስጥ ሚዲያዎችን አፍ አፍኖ የሟቾቹን ማንነትና ብዛት ከማድበስበሱም በላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ‹‹አሸባሪ›› ተብሎ የተፈረጀውንና ከዓመት እስከ ዓመት ዜጎችን የሚጨፈጭፈውን ነፍሰ ገዳይ ቡድን ‹‹ኢ-መደበኛ ኃይል›› በሚል መጠሪያ ጋርዶ ከደሙ ለማንጻት በመጣር ላይ ይገኛል፡፡ ይህ በመንግሥት መዋቅር የታገዘ ዘር ተኮር ጥቃትና አገራዊ ውድቀት ግን ከዚህ በላይ መቀጠል ስለሌለበት ገለልተኛ የሆኑ አገራዊና ዓለም አቀፍ ተቋማትን ያካተተ መርማሪ ኮሚሽን ተቋቁሞ የሚከተሉት ነገሮችን እንዲያጣራ እጠይቃለሁ፡፡ 1ኛ. ‹‹ኦነግ ሸኔ›› በሚል ባለቤት አልባ ሥም ሲጠራ ኖሮ ‹‹ኢመደበኛ ኃይል›› መባል የጀመረው ነፍሰ ገዳይ ቡድን ግልጽ በሆነ መልኩ ማንነቱ፣ ባለቤቱና ፍላጎቱ እንዲጣራ፣ 2ኛ. በወለጋ እና በመተከል እንዲሁም በሁሉም ክልሎች እንደ አገር የተፈጸሙ ጥቃቶችን እና የወንጀሉ ተሳታፊዎችን የሚለይ ጥልቅ ምርመራ ተደርጎ ተሰውረው የቀሩና በድብቅ የተቀበሩ ዜጎች ብዛት በአኃዝ እንዲገለጽ፤ እንዲሁም በጥቃቱ ላይ የተሳተፉ አሸባሪዎች፣ ፖለቲከኞች እና የመንግሥት አመራሮች ተጠያቂ እንዲሆኑ፤ 3ኛ. በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ተፈትሾ የወደቀውና የሆነን አካል ከማውደም ውጭ ማንንም በማይጠቅም ዘረኝነት ውስጥ ተሸጉጦ ያለ አንዳች የኃላፊነት መንፈስ አገራዊ እልቂት የሚፈጥሩ ንግግሮችን እና ተግባሮችን በማዛመት ላይ የሚገኘው የብልጽግና መንግሥት እንደ ሮዋንዳ ሳያጫርሰን እና እንደ ሶሪያ ሳያፈራርሰን በፊት በአገር ደረጃ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም እየጠየቅኩ ‹‹ጥያቄህ ጥያቄዬ ነው››› የምትሉ ወገኖች ሥሜ የተጠቀሰበት ስፍራ ላይ ሥማችሁን ተክታችሁ እንዲታጋሩት አሳስባለሁ፡፡

photo content

አሻጋሪው መሪ ▬▬▬▬▬ ➔መተከል ላይ 168 አማራዎች የተጨፈጨፉ ቀን ▬ ጨበራ ጩርጩራ ፓርክ ሄዶ ዝሆን ይመለከት ነበር። ➔አጣዬ የወደመች ቀን▬ካቢኔውን አስከትሎ አዲስ አበባ ውስጥ ቀለም የተቀባ ቢ
አሻጋሪው መሪ ▬▬▬▬▬ ➔መተከል ላይ 168 አማራዎች የተጨፈጨፉ ቀን ▬ ጨበራ ጩርጩራ ፓርክ ሄዶ ዝሆን ይመለከት ነበር። ➔አጣዬ የወደመች ቀን▬ካቢኔውን አስከትሎ አዲስ አበባ ውስጥ ቀለም የተቀባ ቢሮ እየመረቀ ነበር። ➔አማራ ክልል ተወርሮ የጅምላ ጭፍጨፋ ሲያስተናግድ በነበረበት ወቅት ▬ በኦሮሚያ ክልል ከሚገኝ ማሳ ውስጥ ቁሞ "በዚህ ዘመን ትራክተር እንጂ ሚኒሽር አያስፈልግም" እያለ የአማራን ማሳ በሞርታር ያሳርስ ነበር። ➔ትናንት ወለጋ ላይ ከ300 በላይ አማራዎች ሲጨፈጨፉ▬ ሰላጣና ጎመን ፍለጋ ኮሲ ለኮሲ ይዞር ነበር። (በዚህ መልኩ እንኳን ያንተ ሥልጣን አገሪቷም አትቀጥልም‼️)

በታሪክ ውስጥ ብዙ አረመኔ ሥርዓቶች ተከስተው አልፈዋል። እንደ ብልጽግና ግን ንጹሐንን ካስጨፈጨፈ በኋላ የጅምላ መቃብር ላይ ሰላጣ እና ቆስጣ ተክሎ የሚኩራራ አረማዊ ሥርዓት ተከስቶ የሚያውቅ አይመስ
በታሪክ ውስጥ ብዙ አረመኔ ሥርዓቶች ተከስተው አልፈዋል። እንደ ብልጽግና ግን ንጹሐንን ካስጨፈጨፈ በኋላ የጅምላ መቃብር ላይ ሰላጣ እና ቆስጣ ተክሎ የሚኩራራ አረማዊ ሥርዓት ተከስቶ የሚያውቅ አይመስለኝም። ይህ አይነት እርኩሰት እና እብሪት የት እንደሚያደርሳችሁ መገመት አይከብድም።

የእራሳችሁ መከፋፈል አንሶ ‹‹አማራዎች›› ተብለው የተገደሉ ወገኖቼን አትከፋፍሏቸው…! አሳዬ ደርቤ ➔የክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ የሚለው አሸባሪ ትናንት ክልላችንን ሲወርር ‹‹አማራዎች›› ብሎ በጅምላ አወደመን እንጂ ሙስሊሙን ሲያጠቃ ለክርስቲያኑ ምሕረት አላደረገለትም፡፡ ➔እስልምና ውስጥ ለመደበቅ የሚሞክረው ይሄኛው አሸባሪም በወለጋና በተለያዩ ስፍራዎች ላይ አማራዎችን ሲጨፈጭፍ ክርስቲያን እና ሙስሊም ለይቶ አያውቅም፡፡ እኒህም ሁለት አሸባሪዎች በእምነትም ሆነ በማንነት የተለያዩ ቢሆኑም ‹‹አማራ›› የሚባል የጋራ ጠላት ስላላቸው ከእጃቸው መሃከል ሲያገኙህ ‹‹ነፍጠኛ›› ብለው በጅምላ ያርዱኻል፡፡ ‹‹አማራ›› ብለው ወደ መቃብር ያወርዱኻል፡፡ ባጠመዱልህ የሤራ መረብ ውስጥ ወድቀህ እርስ በእርስ ስትነካከስ ደግሞ በሃይማኖት ታርጋ አውጋዥ እና አጋዥ ሆነው ይከሰታሉ፡፡ በጥቃቱ የተቆጡ መስለው የአዞ እንባቸውን እያንጠባጠቡ እና ምራቃቸውን እያዝረበረቡ እርስ በእርስ የምንጫረስበትን አፍታ ይጠብቃሉ፡፡ የእነሱ መሰሪነት እያደገ ሲመጣ የኔ እና ያንተ ቡልኻነት እየተባባሰ መምጣቱን ጠንቅቀው የተረዱ በመሆናቸው በሤራቸው ውስጥ ወድቀን እርስ በእርስ ስንጠፋፋ በሃይማኖት መነጽር ኀዘናቸውን እና ቁጣቸውን የሚገልጹ ይሆናሉ፡፡ በእነሱ ምድር ውስጥ ስንኖር እና በእነሱ ወገን ታርደን ስንቀበር ግን ማንነት እንጂ ኃይማኖት የለንም፡፡ ክርስቲያንም ሁን ሙስሊም በቋንቋ ከሚዛመዷቸው ነፍሰ ገዳዮቻቸው አትበልጥባቸውም፡፡ ከእርካታ ስሜት ባለፈ ኀዘንም ሆነ ቁጣ አይሰማቸውም፡፡ ሐቁ ይሄ ቢሆንም ታዲያ እነ አሕመድን ጀበልን መፈታተን የሚፈልጉ አንዳንድ ከንቱዎች ያለምንም የእምነት ልዩነት ‹‹አማራዎች›› ተብለው የተገደሉ 246 ወገኖቻችንን በእምነት ሸንሽነው ‹‹ከመቶ በላይ ሙስሊሞች መገደላቸውን አልሰማችሁም እንዴ?›› እያሉ ነው፡፡ እኔ ግን እላችኋለሁ… ➔በሃይማኖት ውስጥ የተደበቁ ዘረኞችን ተንኮል ለማስረዳት ብላችሁ ‹‹አማራዎች›› ተብለው የተገደሉ ወገኖቻችንን በጎጥ ማንነትም ሆነ በሃይማኖት ልታለቅሱላቸው አትሞክሩ፡፡ ➔ሌሎችን ከመጥላት ይልቅ የምትገደሉበትን ማንነታችሁን በማጥበቅ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ➔አላህን እና እግዜራችሁን በተናጠል ይዛችሁ ለሞት የሚዳርጋችሁንና ከሞት የሚታደጋችሁን ‹‹አማራ›› የሚባል የጋራ ማንነታችሁን አስከብሩ፡፡ የወገኖቻችንን ነፍስ ፈጣሪ ይማር፡፡

photo content

የአማራ ብሔርተኛን የመውቀስ ሞራል ያለህ ማን ነህ? አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔ባለፉት ሰላሳ ዓመታት እንደ አማራ ሕዝብ ለጥቃት የተዳረገ ሕዝብ ባይኖርም አብዛኛው የአማራ ኤሊት ግን "ወገኔን የሚያስጨፈጭፈው ሥርዓት አገር ማትረፍ ከተቻለው…" በሚል ምኞት ኦህዴድ መራሹን ብልጽግና ከህውሓት ኢሕአዴግ የተሻለ ለማድረግ አራት ዓመት ሙሉ የተቻለውን ያህል ሲጥር ነበር፡፡ ሆኖም ግን አማራን ለማጥቃት የተደራጁት ኃይሎች ተኩስ ሲጠናከርና ክልሉ ሲወረር የመንግሥት ግደለሽነትና ዳተኝነትም እየጨመረ በመምጣቱ አብዛኛው የአማራ ኤሊትም ‹‹በክልል ልዩ ኃይሎች ፈንታ መከላከያ ሠራዊታችን ይጠናከር›› የሚል ጥያቄውን አቁሞ ሐቁን በመቀበል ፋኖን ማደራጀት ጀመረ፡፡ ➔ሲቀጥል ደግሞ አሁን ‹‹ብሔርተኛ›› የምትለው አካል የአማራ ሕዝብ እልቂት በየሳምንቱ በተከሰተ ቁጥር አጸፋ ከመመለስና መንግሥት ላይ ሤራ ከመጠንሰስ ይልቅ የችግሩ ምንጭ ላይ አተኩሮ ‹‹አገር አፍራሹና ደም አፋሳሹ ከፋፋይ ሕገ-መንግሥት ሊሻሻል ይገባል›› እያለ ሲጠይቅ የነበረ ቢሆንም የመንግሥት መልስ ግን ‹‹ለአንድ ሕዝብ ብለን ሕገ-መንግሥት አናሻሽልም›› የሚል ነበረ፡፡ ከብዙ ጉትጎታ በኋላም ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ለሌላው ብሔር ጸጋ ከሆነ ለአማራው ብቻ አደጋ የሚሆንበት ምክንያት የለም›› በሚል አቋም ከዜግነት ወደ ማንነት ፖለቲካ ወርዶ ብሔርተኝነትን ማቀንቀን ጀመረ፡፡ ➔ከዚህ ባለፈም ‹‹ጃፓን አገር ለተሠራ መኪና የብሔር ታርጋ መሥጠት፣ በአገልግሎታቸው ደንበኛ ማፍራት የሚገባቸውን ባንኮች በብሔር ማዕቀፍ ውስጥ ማስገባት፣ መማር ለሚሹ ዜጎች እውቀትን በሚሰጡ ፈንታ በብሔር እሳቤ ሰርቲፊኬት የሚሸጡ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርስቲዎችን መክፈት… ልክ ስላልሆነ መታረም አለበት›› የሚሉ ሐሳቦችም በብዛት የሚሰሙት ከአማራው ኤሊት ነበረ፡፡ ይሄውም ለአገር የሚበጅ ጥያቄው ችላ ተብሎ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች ወደ ሌሎች ባንኮች ሲዘዋወሩ ባዬ ጊዜ እርሱም የአማራ ባንክን መሠረተ፡፡ ምን ልልህ ፈልጌ መሰለህ…. በአገር ማእቀፍ ውስጥ ሳቁም ሆነ ለቅሶው፣ ጸጋውም ሆነ አደጋው፣ በረከቱም ሆነ መቅሰፍቱ የጋራ ቢሆንም ሥልጣን ላይ ያሉት የፖለቲካ ነጋዴዎች ግን በጋራ እንድንስቅም ሆነ በጋራ እንድናዝን ባለመፍቀዳቸው ሁላችንም ብሔርተኞች ሆነናል፡፡ በብሔር በረት ውስጥ ደግሞ አንድኛው ተኳሽ፣ ሌለኛው አልቃሽ እንደሆኑ አይቀጥሉም፡፡ አንዱ ብሔር ተጠቃሚ ሲሆን ሌለኛው ብሔር ደግሞ ተጠቂ እና ወዳሚ እንደሆነ አይኖርም፡፡ ስለሆነም ትናንት ጥቃት ካደረስክበት በኋላ እንባውን እያየህ ‹‹አልቃሻ›› ያልከው አካል በማግስቱ እንባውን ግቶህ ሳቅህን ከቀማህ በኋላ ‹‹ተልካሻ›› እያለ ያሾፍብኻል፡፡ ትናንት ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ይሻሻል›› በማለት የዜግነት ጥያቄውን ሲያቀርብ ‹‹ለአንድ ሕዝብ ብዬ አላስተካክልም›› በሚል መልስ የገፈተርከው አካል እንዳንተ ጽንፈኛ ሆኖ ያደረክበትን እና የምታደርገውን ማድረግ ከጀመረ በኋላ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ የጋራ ችግር መሆን ስለጀመረ በጋራ እናስተካክለው›› ስትለው ‹‹አልሰማህም›› ይልኻል፡፡ አሁንም እየሆነ ያለው ይሄው ነው!

photo content

በጦርነቱ ወቅት ‹‹አንድም ወራሪ አምልጦ እንዳይወጣ፣ ውጠህ አስቀረው›› በሚል ቅስቀሳው የሚታወቀውና የሰሜኑን ሕዝብ በሰበር ዜናው ጨርሶ ከጎረቤት አገራት እያስመጣ ሲገድል የነበረው ናትናኤል መኮነን
በጦርነቱ ወቅት ‹‹አንድም ወራሪ አምልጦ እንዳይወጣ፣ ውጠህ አስቀረው›› በሚል ቅስቀሳው የሚታወቀውና የሰሜኑን ሕዝብ በሰበር ዜናው ጨርሶ ከጎረቤት አገራት እያስመጣ ሲገድል የነበረው ናትናኤል መኮነን የተባለ ፍናፍንት ስለ እኔ የጻፈውን አነበብኩት፡፡ የሚገርመው ነገር ሰሜን እዝ በተጠቃ ማግስት ‹‹የኢትዮጵያ ሠራዊት ምርኮኞችን እረሽኖ ከገደል ከተተ›› ከሚል ዜና ጋር ቪዲዮ ሲለቀቅ ‹‹በመከላከያ ልብስ ግድያውን የፈጸሙት አሸባሪዎች ናቸው›› የሚል ማስተባበያ ሲሰጥ የነበረውና ‹‹ይሄን ያህል ወራሪ ተደመሰሰ›› የሚል ዜናን እንጀራው ያደረገው ይሄ እንኩቶ ፍጡር እኔ ላይ ጣቱን ሲቀስር አለማፈሩ ግርም ይላል፡፡ የሆነው ሆኖ… ➔በቅርብ ቀን የተማረኩ የኤርትራ ወታደሮች ሲረሸኑ የሚያሳይ ቪዲዮ አላየኸም እንዴ? ➔በዚያ ጦርነት ላይ በጭና፣ በጋሼና፣ በኮምቦልቻ፣ በአጋምሳ፣ በጋሊኮማ፣ በቆቦ፣ በአንጾኪያ ሰባት ሺህ ነፍሶች የተረሸኑት በዚያ መልኩ መሆኑን አታውቅም እንዴ? ➔‹‹ደብረ ጽዮን 300 ሺህ ወጣት የገባበት አይታወቅም›› ማለቱን አልሰማህም እንዴ? በኢትዮጵያስ ወገን በርካታ ዜጋ አላለቀም እንዴ? ጦርነቱ እኮ ከዚያ ቪዲዮ የከፉ እልፍ አእላፍ አረመኔያዊ ድርጊቶች የተስተናገዱበት ነው፡፡ እናስ ትናንት ‹‹ጁንታ›› የሚል ሥም በተሰጣቸው ወጣቶች ላይ የተፈጸመውን ዘግናኝ ቪዲዮ ለቅቀህ ሥም ካጠፋህ በኋላ ‹‹ፋኖ›› ላይ ተመሳሳዩን አረመኔያዊ ድርጊት ልታስፈጽም ስትዘገጃጅ ዝም ብየ የምመለከትህ ይመስልኻል?

ስለ ቪዲዮው ▬▬▬▬▬ ➔ያኔ በወረራው ወቅት የተቀረጸ ነው። ➔ወጣቶቹ ብዙ መስዋዕትነት ካስከፈለ ምሽግ ውስጥ የተማረኩ ነበሩ። ➔ከሰሜን ጫፍ ተነስተው ሰሜን ሸዋ ድረስ የመጡት "ሒሳብ የሚያወራርድ" ክላሽና ላውንቸር ተሸክመው እንጂ ቅቤና ማር ጭነው አልነበረም። ➔በአሳዛኝ ገጽታ የተሞላውንና ከሦስት መቶ ሺህ በላይ ነፍስ የበላውን ዘግናኝ ጦርነት እንደ "ባሕላዊ ጨዋታ" መመልከት ሊበቃ ይገባል።