uk
Feedback
በጎጎታ ኬር የህጋ ሞዴል አዳሪ ት/ቤት

በጎጎታ ኬር የህጋ ሞዴል አዳሪ ት/ቤት

Відкрити в Telegram
264
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
грудень '24
грудень '24
+3
в 0 каналах
листопад '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+47
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+182
в 1 каналах
Get PRO
серпень '240
в 0 каналах
Get PRO
липень '240
в 0 каналах
Get PRO
червень '240
в 0 каналах
Get PRO
травень '240
в 0 каналах
Get PRO
квітень '240
в 0 каналах
Get PRO
березень '240
в 0 каналах
Get PRO
лютий '240
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+268
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
10 грудня+2
09 грудня0
08 грудня0
07 грудня0
06 грудня+1
05 грудня0
04 грудня0
03 грудня0
02 грудня0
01 грудня0
Дописи каналу
ማስታወቂያ የRemedial ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ምርጫን በተመለከተ በ 2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ህዳር 12/2016 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፡ - ከታች የተዘረዘሩ ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም የማያስተናግዱ መሆኑን እንገልጻለን። 1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 4. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 5. አርሲ ዩኒቨርሲቲ 6. ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲ

2
Немає тексту...
336
3
አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ዝውውር መመሪያ 👇👇 በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና በላይ ያገኘ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛዋወራል፡፡ ✔ ከ1ኛ - 3ኛ ክፍል ላሉ ተከታታይ ምዘና ከ70% ወስደው የማጠቃለያ ምዘና (ፈተና) ከ30 % እንዲወስዱ ያዛል። ያላለፉ ተማሪዎች በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ድጋፍ አግኝተው የሚዘጋጀውን ፈተና ተፈትነው እንዲገቡ ይደረጋል። ✔ ከ4ኛ - 5ኛ ላሉ ደግሞ ተከታታይ ምዘና ከ60% ወስደው የማጠቃለያ ምዘና (ፈተና) ከ40 % እንዲወስዱ ያስቀምጣል። በእነዚህ ክፍሎች ተማሪዎች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማግኘት አለባቸው። ✔ ከ7ኛ ወደ 8ኛ እንዲሁም ከ8ኛ ወደ 9ኛ ለሚሸጋገሩ ደግሞ 40% ተከታታይ ምዘና 60% ደግሞ የማጠቃለያ ምዘና እንደሚወስዱ ያስቀምጣል። ለማለፍም 50 ከመቶ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው። ✔ ከ9-11ኛ ክፍል ሂሳብ (Maths) እና እንግሊዘኛ (English) ትምህርት ከ50% በታች ያመጣ ተማሪ እንዲሁም 1-7ኛ ክፍል 6ኛን ሳይጨምር Maths እና የማስተማሪያ ቋንቋውን ከ50% በታች ካመጣ ወደቀጣይ ክፍል መዛወር የማይችል እንደሆነ ተጠቅሷል። ✔ በመመሪያው አንኳር የትምህርት ዓይነት ተብለው የተለዩ የትምህርት አይነቶች ሲቀመጡ ለአንደኛ እና ለመካከለኛ ደረጃ የትምህርት እርከኖች ትምህርቱ የሚሰጥበት ቋንቋ እና የሒሳብ ትምህርት ዓይነቶች እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና የሒሳብ ትምህርት አንኳር ዓይነቶች ሆነው ተለይተዋል። ✔ በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍሎች ላይ በሚሰጡ ፈተናዎች የማለፊያ ነጥብ ካላገኘ ለአንድ ጊዜ በትምህርት ቤቱ በመደበኛነት ትምህርት እንዲከታተል ይደረጋል። ነገር ግን ከ9ኛ_11ኛ ክፍል ተማሪ በአንድ ክፍል ከ2 ጊዜ በላይ ከደገመ ወይም በተከታታይ ክፍሎች ከደገመ ከትምህርት ዓለም ይሰናበታል። ✔ በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና በላይ ያገኘ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛዋወራል፡፡ ✔ የአንደኛ ደረጃ ከ1-5 እና 6ኛ የክፍል ክፍል ዝውውር የራሱ የዝውውር አፈፃፀም እንደሚኖረው ሲጠቀስ በተመሳሳይ ፥ የመካከለኛ ደረጃ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል የተማሪዎች ምዘና እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር አተገባበር የየራሳቸው ዝርዝር መመሪያ ወጥቶላቸዋል። ✔ አስራ አራት አመት የሚወስደውን አጠቃላይ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች በአንድ የሥራና የተግባር ትምህርት መስክ ጥናት ማጠናቀቃቸውንና በዚያም መስክ መመረቃቸውን ለማረጋገጥ የሚካሄድ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ይኖራል። ✔ መመሪያው ተግባራዊ የሚደረገው ከቅድመ አንደኛ ደረጃ አስከ 12ኛ ክፍል በመደበኛ እንዲሁም በማታውና በርቀት መርሃ ግብሮች ትምህርት በሚሰጡ ተቋማት ሲሆን ከዓለም አቀፍና ከውጭ ማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች በስተቀር በመንግስትና በሌሎች በሁሉም አይነት ትምህርት ቤቶች/ተቋማት/ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
303
4
Немає тексту...
428
5
+1
Немає тексту...
530
6
የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል! #Ethiopia | የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ነገር ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዚህም መሰረት በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣ 180 ከ 600 እና 150 ከ500) የተቆረጠ መሆኑ ተመላክቷል። ከላይ በተራ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉት የሚከተሉትን መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ ብቻ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 255 ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ700 -234 ያመጡ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች ከ600- 218 ያመጡ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 200 ያመጡ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 224 ያመጡ ታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 - 192 ያመጡ ታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ700- 210 ያመጡ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ አርብቶ አደር አካባቢ የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ600 - 180 ያመጡ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ500 -150 ያመጡ ዓይነ ስውራን ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከ500 -150 ያመጡ መሆን አለባቸው ተብሏል።
512
7
#የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል። 2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ 3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፡፡ መረጃው የተሰበሰበው https://portal.etherenet.edu.et ላይ ነው፡፡ 4. በተማሪዎች የተመረጡ ተቋማት ያላቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 5. ጾታ ፡- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ ተደርጓል፣ 6. የትምህርት ቤት ተዋጽኦ ፡- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን ያግዛል፡፡ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል፡፡ 7. የውጤት ተዋጽኦ ፡-የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር ያግዛል፡፡ 8. ወሊድን በተመለከተ፡- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው፡፡ በመሆኑም በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡ መረጃዎቹ የተሰበሰቡት https//student.ethernet.edu.et ላይ ነው፡፡ •አስፈላጊ ማስረጃዎች: - ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የህጻናት የክትባት ካርድ 9. ትክክለኛ የሕክምና ቦርድ ማስረጃዎች፡- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል፡፡ • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና ከህዝብ ጤና ተቋማት የህክምና ምስክር ወረቀት በሶስት ዶክተሮች እና በህክምና ዳይሬክተሩ የጸደቀ። • የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው። 10. ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች (identical twins) ፡- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል። የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et ላይ ነው። • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡- ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የልደት የምስክር ወረቀት፣ 11. የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች:- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምትውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል። የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው። • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የአካል ችግር ያለበትን የሰውነት ክፍል የሚያሳይ ፎቶግራፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣ ማሳሰቢያ፣ ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን እንገልጻለን፡፡ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር!
415
8
ማስታወቂያ -የቅሬታ ምላሽን ይመለከታል። በ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ለይ በአካል በመምጣት ቅሬታ ላቀረባችሁ በስልክ ወይም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ምላሽ ተሰጥቷል። እየተሰጠም ይገኛል። በበይነ መረብ(Online) ቅሬታ ያቀረባችሁ ምላሹም በበይነ መረብ የተሰጠ በመሆኑ ከዚህ በፊት ውጤት ባያችሁበት መልኩ በድረ ገጽ eaes.et ላይ ምላሹን ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። በቁጥር የተወሰኑ ቅሬታዎች በምላሽ ሂደት ላይ ያሉ በመሆኑ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን። የት/ት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
633
9
+1
Немає тексту...
636
10
4_5852697998059901929(1).docx
533
11
Немає тексту...
969
12
Немає тексту...
536
13
የሂጋ ሞዴል አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነው በሱፈቃድ መለሰ አብዶ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና #621 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል ። ተማሪ በሱፈቃድ በዚህ ዉጤቱ በመላዉ ሀገሪቱ ከ600 በላይ ካመጡ 200 ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ በመሆን ታሪክ ሰርቷል።
486
14
Немає тексту...
600
15
ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 14 የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል። የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አ+1
ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 14 የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል። የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር ይፋ ሆኗል። በዚህም መሰረት ፤ ከመስረም 7 እስከ 11 ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል። የአንደኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ከጥር 27 እስከ የካቲት 1 እንደሚሰጥ የሚያሳየው የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር ከየካቲት 4 እስከ 8 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው የተማሪዎች ፈተና የሚታረምበት ውጤት የሚጠናቀርበትና የሚገለፅበት ወቅት እንደሆነ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር እንደሚያሳየው የካቲት 18 የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከግንቦት 12 እስከ ግንቦት 23 የአጠቃላይ የትምህርት ማጠቃለያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና ይሰጣል። ከግንቦት 26 እስከ 30 የ6ኛ ክፍል አንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 3 እስከ 7 የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ የማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና ጊዜ እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል። የሁለተኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ወቅትም ከሰኔ 17 እስከ 21 ሲሆን ከሰኔ 24 - 28 ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ዝግ ሆነው ፈተና የማረም፣ ውጤር የሚጠናቀርበት ፣ እና የሚገለፅበት እንደሚሆን ካሌንደሩ ያሳያል። ሰኔ 30 ወላጆች እና የትምህርት ማህበረሰቡ በተገኙበት የአመቱ ትምህርት ማጠናቀቂያ ይሆናል። ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ እንደሚደረግ ማሳስቢያ ሰጥቷል። @Moe_Ethiopia @Moe_Ethiopia
633
16
Немає тексту...
450
17
Немає тексту...
481
18
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መቼ ይገለፃል ? የቀጣይ አመቱ ፈተናስ በየትኛው ካሪኩለም ይሰጣል ? የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት እስከ  መስከረም 2016 ዓ/ም አጋማሽ ድረስ ይፋ ለማድረግ እቅድ መያዙ ታውቋል። ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን መስከረም አጋማሽ ድረስ ይፋ በማድረግ በጥቅምት ወር የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንዲጀመር የማድረግ ዕቅድ መያዙን ከሰሞኑን መግለጫ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ መገራቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። ከዚህ በተጨማሪ በ2015 ዓ.ም. በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን ሲወስዱ የነበሩት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች፣ የመጨረሻዎቹን ሦስት ፈተናዎች ባለመፈተናቸው ዘንድሮ መጨረሻ ድረስ ተፈትነው እንዲያሚያጠናቅቁ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ በጎንደር በነበረው ግጭት ወቅት ፈታናዎቹን ያልወሰዱት በአጠቃላይ ከ16 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንደነበሩ የሚዘነጋ አይደለም። በሌላ መረጃ ደግሞ ፤ በቀጣይ ዓመት 2016 ዓ/ም የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አዲሱ እና የቀድሞው ካሪኩለም ድብልቅ ፈተና እንደሆነ ታውቋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ ቀጣይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሆኑ እስከ 11ኛ ክፍል የተማሩት በድሮው ካሪኩለም መሆኑን ገልጸው በቀጣይ አመት የሚማሩት ግን በአዲሱ ካሪኩለም መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ የሽሽግር ስራ በሚሰራበት ወቅት ብሔራዊ ፈተናው ተደባልቆ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። ከታች ያሉትን በድሮው ካሪኩለም አሁን ገብተው የሚማሩትን በአዲሱ ካሪኩለም ተደርጎ ነው ፈተናው የሚዘጋጀው በዚህ ላይ ችግር አይፈጠርም ብለዋል። በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የኢንተርኔት አገልግሎት ባለባቸው አካባቢዎች በኦንላይን እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል። @tikvahethiopia
470
19
በ2016 ዓ.ም አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይተገበራል:: የሁለተኛ ደረጃ የተማሪ መጻህፍትና የመምህራን መምሪያዎችን ለመምህራንና ባለድርሻዎች ለማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠም ይገኛል:: ---------------------//--------------------------- ነሐሴ 19/2015 (የትምህርት ሚኒስቴር) በ2016 ዓ.ም አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሁሉም የመንግስትና የግል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚተገበር የትሞህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪ መጻህፍትና የመምህራን መምሪያዎችን ለመምህራንና ባለድርሻዎች ለማስተዋወቅ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠም ይገኛል። የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) ስርዓተ ትምህርቱ የሚተገበረው ከዓለም አቀፍና ከውጭ የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች በስተቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በሚያስተምሩ ሁሉም የመግስትና የግል ትምህርት ቤቶች መሆኑን ገልፀዋል። ስርዓተ ትምህርቱም በሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ፣ በትግራይ ክልል ደግሞ በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል እንደሚተገበርም ተናግረዋል። ሰራ አስፈፃሚው ስርዓተ ትምህርቱ ከሥራና የተግባር የትምህርት አይነቶች በስተቀር በሁሉም የቀለም ትምህርት ዓይነቶች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ እንደሚተገበርም ገልፀው የሥራና የተግባር ትምህርቶችም ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚተገበሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ስርዓተ ትምህርት እየተሻሻለና እየዳበረ እንደሚሄድ የጠቆሙት ዶ/ር ቴዎድሮስ ለስርዓተ ትምህርቱ ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ2015 ዓ. ም ጀምሮ መተግበር መጀመሩ ይታወቃል።
400
20
Немає тексту...
345