Joseph Math Tutor
Відкрити в Telegram
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
Показати більше1 854
Підписники
-124 години
+67 днів
+1330 день
Архів дописів
1 854
#ዉጤት ከመገለፁ በፊት ትምህርት ሚኒስቴር በይፋ መግለጫ ይሰጣል:: ትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ከሰጠ በኃላ ነው ዉጤት ማየት ምትጀምሩት:: ስለዚህ በትዕግስት ጠብቁ 🙏🙏
#ዉጤት ሲገለፅ በቀላሉ የምታዩባቸው መንገዶች !!!
1. eaes.et
2. eaes.gov.et
3. eaes.edu.et
4. result.neaea.gov.et
5. SMS 6284
6.https://t.me/EAESbot
1 854
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የሁሉም መደበኛ ተማሪዎች (ቅድመ፣ ድህረ እንዲሁም የዶክትሬት ተማሪዎች) ምዝገባ መስከረም 7 እና 8 /2018 ዓ/ም መሆኑ ተገልጿል።
መስከረም 9 እና 10 ደግሞ በ2017 የሬሜዲያል ትምህርት ተከታትለው የማለፊያ ውጤት ያመጡ እንዲሁም አዲስ የመጀመሪያ አመት ፍሬሽ ማን እና የሬሜዲያል ተማሪዎች ምዝገባ ቀን እንደሆነ ተገልጿል።
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር
@Joseph_maths_tutorial
1 854
ለኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ
የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡ ትምህርት የሚጀምረዉ መስከረም 12፣ 2018 ዓ.ም ይሆናል፡፡
በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ ማለፍያ ነጥብ ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች፤ የ2018 ዓ.ም አዲስ ገቢ (ፍሬሽማን) ተማሪዎች ምደባ በትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ሲደረግ ወደፊት በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ የሚደረግላችሁ ይሆናል፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 854
+1
#DebreBerhanUniversity
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ነባር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና የኤክስቴንሽን ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም የምዝገባ ጊዜ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 854
#BulehoraUniversity
#ጥሪማስታወቂያ
ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ
ዩኒቨርሲቲያችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን እየገለጸ፡ ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደዉ መስከረም 5-6/2018 ዓ.ም ስለሆነ ማንኛዉም ተማሪ በአካል ቀርቦ በተጠቀሰዉ ቀነ ገደብ ዉስጥ እንዲመዘገብ እየገለጽን ከተባለዉ ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆናችንን በጥብቅ እናሳዉቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• በ2017 የትምህርት ዘመን 1ኛ ዓመት ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች የትምህርት ክፍል ምርጫ የሚካሄደዉ መስከረም 06/2018 ዓ.ም እና ዉጤታችሁ ደግሞ የሚገለጸዉ መስከረም 08/2018 ዓ.ም ይሆናል፡፡
• የቅድመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ትምህርት ከመጀመሩ በፊት በ(e-SHE) የተዘጋጀዉን (student Success Suit (SSS)) ሥልጠና የሚትወስዱ መሆኑን ከወዲሁ እናሳዉቃለን፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 854
#WachamoUniversity
#የጥሪማስታውቂያ
ለዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ!!
የ2018 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሄደው መስከረም 8 እና 9 2018 ዓ.ም መሆኑን እየገለጽን በተጠቀሰው ቀን በአካል ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡- በ2018 ዓ.ም ወደ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለሚመደቡ እና በ2017 ዓ.ም የሪሜድያል ፕሮግራም ተከታትለው ማለፍያ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ወደ ፊት በሌላ ማስታወቂያ የምናሳዉቅ ይሆናል።
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 854
#AASTU
#የጥሪማስታወቂያ
ለአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ
እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ምግባ ከዚህ በታች በተገለጸው መሰረት የሚከናወን መሆኑን እናሳውቃለን፡
1. ሁሉም የመጀመሪያ ድግሪ እና የድኅረ-ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች - መስከረም 08-09/2018 ዓ.ም (ሃሙስ እና አርብ)
2. ሁሉም የተከታታይ መጀመሪያ ድግሪ እና የድኅረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች - መሰከረም 10-11/2018 ዓ.ም (ቅዳሜ እና እሁድ)
ማሳሰቢያ፡
1. ከተጠቀሱት ቀናት ውጭ ምዝገባ የማይካሄድ መሆኑን እናሳውቃለን።
2. ምዝገባ የሚከናወነው በአካል ነው።
3. የመጀመሪያ ድግሪ መደበኛ ተማሪዎች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) እንድታወጡ እናሳሰባለን።
@Joseph_maths_tutorial
1 854
#MattuUniversity
የጥሪ ማስታወቂያ!!
ይህ መቱ ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መስከረም 08 እና 09 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን አስታውቋል።
የ2018 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 12/2018 ዓ.ም መሆኑን ተገልጿል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
የ2018 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ አመት (አዲስ) ተማሪዎች፣ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ያጠናቀቁና የትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች መግቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መረጃ እንደደረሰን ወድያውኑ የምናሳውቅ ይሆናል።
ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
@Joseph_maths_tutorial
1 854
እስካሁን ጥሪ ያቀረቡ ዩኒቨርሲቲዎች
▪️አሶሳ ዩኒቨርሲቲ:- ሁሉም ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ጎንደር ዩንቨርሲቲ:- ሁሉም ነባር ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም አዲስ ገቢ መደበኛ መስከረም 7 እና 8
▪️አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ:- ሁሉም ነባር ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ወልደያ ዩኒቨርሲቲ :- ለጤና ሳይንስ እና እንስሳት ህክምና ክፍል ነባር ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6
▪️አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ:- ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም ለሁሉም መደበኛና ተከታታይ ተማሪዎች መስከረም 8( በቅጣት 12)
▪️ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ:- ለሁሉም ቅድመ ምረቃ( አዲስ ገቢ ጨምሮ) እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ :- ከremedial ውጪ ያሉ መግቢያ ቀን መስከረም 10
▪️ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ :- ለአዲስ ገቢ(remedial ጨምሮ) መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም ነባር ተማሪዎች 8 እና 9
▪️ቀብሪዳር ዩንቨርስቲ :-
ሁሉም ተማሪዎች አዲስ የሚመደቡትንም ጨምሮ መስከረም 8 እና 9
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
1 854
#UniversityOfKabridahar
ቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡
በዚህም፦
➫ ነባር የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች እና በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ ማለፍያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የምትመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
➫ በተለያየ ምክንያት ዊዝድሮ ሞልታችሁ የወጣችሁ ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡
@Joseph_maths_tutorial
1 854
+1
#WolloUniversity
ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም የመግቢያ ጊዜ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት በየምትማሩበት ግቢ (ደሴ ግቢ፣ ኮምቦልቻ ግቢ እና ልዕለ ህክምና ግቢ) ሪፖርት ማድረግ እንዳለባችሁ ተገልጿል።
በ2018 ዓ.ም አዲስ ለምትመደቡ የአንደኛ ዓመት እና የሪሚዲያል ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ተምራችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ጥሪ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል።
@Joseph_maths_tutorial
1 854
+1
#SamaraUniversity
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የሁሉም ነባር መደበኛ የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን የመግቢያ ቀን መስከረም 07/2018 ዓ.ም ሲሆን፤ ምዝገባ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
ትምህርት መስከረም 12/2018 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።
🔔 በ2017 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በፍሬሽማን ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር ወደ ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የምትመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ እንደሚደረግላችሁ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
@Joseph_maths_tutorial
1 854
+1
#BahirDarUniversity
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና የማታ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት አሳውቋል፡፡
በዚህም፦
➫ በ2017 ዓ.ም Freshman እና በ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ ትምህርት ተማሪዎች የነበራቸሁ ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት መስከረም 05 እና 06/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡ (ሪፖርት ምታደርጉበትን ካምፓስ ለማወቅ ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ፡፡)
➫ ሌሎች ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም፤ ፕሮግራሞቹ በሚገኙበት ካምፓሶች ይካሔዳል፡፡
➫ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ የማታ (Extension) ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 15 እና 16/2018 ዓ.ም፤ ፕሮግራሞቹ በሚገኙበት ካምፓሶች ይከናወናል፡፡
➫ በሁሉም ፕሮግራሞች የግብርና ኮሌጅ፣ የእንስሳት ሀክምና፣ የስነ-ምድር እና የአደጋ መከላከል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሪፖርት የምታደርጉት በዘንዘልማ ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል፡፡
🔔 በ2017 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ በቀጣይ ይገለጻል ተብሏል፡፡
@Joseph_maths_tutorial
1 854
+1
#JigjigaUniversity
ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ነባር ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡
አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች፣ በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የነበራችሁና ያለፋችሁ እንዲሁም 1ኛ ዓመት 2ኛ አጋማሽ ነባር ተማሪዎች መግቢያ መስከረም 05 እና 06/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
➫ የትምህርት ሰነዶች (ከ8ኛ-12ኛ ክፍል) ዋናውና ኮፒው፣
➫ የቅርብ ጊዜ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ (8)፣
➫ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።
@Joseph_maths_tutorial
1 854
#UniversityOfGondar
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለነባር እና አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
በዚህም የሁሉም ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 05 እና 06/2018 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የሚመደቡ አዲስ ገቢ መደበኛ ተማሪዎች እና በ2017 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በጎንደር የኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት መስከረም 07 እና 08/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል፡፡)
@Joseph_maths_tutorial
1 854
ዉጤት ሲገለፅ በቀላሉ የምታዩባቸው መንገዶች !!!
1. eaes.et
2. eaes.gov.et
3. eaes.edu.et
4. result.neaea.gov.et
5. SMS 6284
6.https://t.me/EAESbot
Share our channel 👇🏿👇🏿👇🏿
@Joseph_maths_tutorial
1 854
የ12ኛ ክፍል ውጤት ሊለቀቅ 4 ቀናት ብቻ ቀርቶታል‼️
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጳጉሜ ወር ላይ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል ።
ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ደግሞ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ/ም ተማሪዎችን መቀበል ይጀመራሉ
ውጤት ይፋ ሊደረግ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርቶታል።
1 854
#ArbaminchUniversity
የጥሪ ማስታወቂያ!!
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ኢ-መደበኛ መርሃ-ግብር ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ እሁድ መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሰኞ እና ማክሰኞ መስከረም 5 እና 6 ቀን 2018 ዓ.ም፣ እና ትምህርት መጀመሪያ ረቡዕ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
የ2018 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ አመት (አዲስ) ተማሪዎች፣ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ያጠናቀቁና የትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች መግቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መረጃ እንደደረሰን ወድያውኑ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በ2017 ትምህርት ዘመን 1ኛ ዓመት ትምህርት አጠናቀው ትምህርት ክፍል ምደባ ያላገኙ ተማሪዎች ትምህርት ክፍል ምርጫ ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ ምደባ የሚፈጸመው ማክሰኞ መስከረም 06 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ ውጤት የሚገለጸው ረቡዕ መስከረም 07 ቀን 2017 ዓ.ም. ይሆናል፡፡
ሁሉም የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች ከምዝገባ በፊት በኤሌክትሮኒክ ትምህርት አስተዳደር ክፍል አስተባባሪነት የሚሰጠውን የ e-SHE SSS ሥልጠና በማጠናቀቅ ቢያንስ አንድ (1) ሰርተፊኬት ማግኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
JOIN: @Joseph_math_tutorial
--------------------------------------------
