cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹

إِنَّمَا يَخْ؎َى اللَّهَ مِنْ عَِؚادِهِ الْعُلَمَاءُ ۗ إِنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ غَفُورٌ አላህን ኚባሮቹ ውስጥ ዚሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ና቞ው፡፡ አላህ አሾናፊ መሓሪ ነው፡፡ (📗Al Qura'an 35:28) https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0

Більше
РеклаЌМі ЎПпОсО
198
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
НеЌає ЎаМОх7 ЎМів
НеЌає ЎаМОх30 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ЀПтП МеЎПступМе
ዚመካ ሙሜ -ሪኮቜ ዹአላህን ፈጣሪነት አልካዱም! ~ ነቢዩ ï·º ዚተላኩባ቞ው እነዚያ ሙሜ -ሪኮቜ #አብዛኞቹ ዚሰማይ፣ ዚምድር ፈጣሪ አላህ እንደሆነ፣ ዹሁሉ ነገር ስልጣኑ በእጁ እንደሆነ፣ ዝናብ ዹሚሰጠው አላህ እንደሆነ ያምኑ ነበር። እነዚህ ባዶ ሙግቶቜ ሳይሆኑ ዚተሚጋገጡ ሐቆቜ ና቞ው። ቁርኣን ውስጥ ኹሚገኙ በርካታ መሚጃዎቜ ውስጥ #ጥቂቱን ብቻ ልጥቀስ። 1.  قُل لِّمَنِ ٱلۡأَرۡضُ وَمَن فِيهَآ إِن كُنتُمۡ تَعۡلَمُونَ ÙšÙ€ سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ أَفَلَا تَذَكَّرُونَ ÙšÙ¥ قُلۡ مَن رَُؚّّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ ٱلسَؚّۡعِ وَرَُؚّ ٱلۡعَرۡ؎ِ ٱلۡعَ؞ِيمِ ÙšÙŠ سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ أَفَلَا تَتَّقُونَ ÙšÙ§ قُلۡ مَنۢ ؚِيَدِهِۊ مَلَكُوتُ كُلِّ ؎َيۡءٖ وَهُوَ يُجِيرُ وَلَا يُجَارُ عَلَيۡهِ إِن كُنتُمۡ تَعۡلَمُونَ ÙšÙš سَيَقُولُونَ لِلَّهِۚ قُلۡ فَأَنَّىٰ تُسۡحَرُونَ ÙšÙ© {“ምድርና በውስጧ ያለው ሁሉ ዹማን ነው ዚምታውቁ ኚሆናቜሁ?” በላ቞ው። “በርግጥ ዹአላህ” ይላሉ። “ታዲያ አትገሰፁምን?” በላ቞ው። “ዚሰባቱ ሰማያት ጌታና ዚታላቁ ዐርሜ ጌታ ማን ነው?” በላ቞ው። “በርግጥ አላህ ነው” ይላሉ። “እንግዲያው አትፈሩትምን?” በላ቞ው። “ዹሁሉ ነገር ስልጣኑ በእጁ ዹሆነው እሱ ዚሚጠብቅ በሱ ላይ ዹማይጠበቅ (ዹሆነው) ማን ነው? ዚምታውቁስ ኚሆናቜሁ?” በላ቞ው። “(ሁሉም) ለአላህ ነው” ይላሉ። “ታዲያ እንዎት ትታለላላቜሁ?” በላ቞ው።} [ሙእሚኑን፡ 84-89] 2.  وَلَ؊ِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَسَخَّرَ ٱل؎َّمۡسَ وَٱلۡقَمَرَ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۖ} ... {وَلَ؊ِن سَأَلۡتَهُم مَّن نَّزَّلَ مِنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ فَأَحۡيَا ؚِهِ ٱلۡأَرۡضَ مِنۢ َؚعۡدِ مَوۡتِهَا لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۚ} {ሰማያትንና ምድርን ዹፈጠሹ ፀሐይንና ጹሹቃንም ዚገራ ማን እንደሆነ ብትጠይቃ቞ው በእርግጥ “አላህ ነው” ይላሉ።} {ኹሰማይም ውሃን ያወሚደና በሱም ምድርን ኚሞተቜ በኋላ ህያው ያደሚጋት ማን እንደሆነ ብትጠይቃ቞ው በርግጥም “አላህ ነው” ይላሉ።} [ዐንኚቡት፡ 61፣ 63] 3.   {وَلَ؊ِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ لَيَقُولُنَّ خَلَقَهُنَّ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡعَلِيمُ} {ሰማያትንና ምድርን ማን እንደፈጠሚ ብትጠይቃ቞ውም በእርግጥ “አሾናፊውና አዋቂው (አላህ) ነው ዚፈጠራ቞ው” ይላሉ።} [ዙኜሩፍ፡ 9] 4.   {وَلَ؊ِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَهُمۡ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۖ } {ማን እንደፈጠራ቞ው ብትጠይቃ቞ውም “በእርግጥ አላህ ነው” ይላሉ።} [ዙኜሩፍ፡ 87] እንዲያውም ዚመካ ጣኊታውያን ለአላህ አምልኮትም ይፈፅሙ ነበር። እርድና ሐጅን በምሳሌነት መውሰድ ይቻላል። ኹዚህም አልፎ ጣኊታውያኑ ጣኊቶቻ቞ው ኹአላህ በታቜ እንደሆኑ ያውቁ ነበር። በማስሚጃ ነው ዚማወራው። 1.  {وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۊٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعُؚۡدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرُِؚّونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ} {እነዚያም ኚርሱ ሌላ ሚዳቶቜን ዚያዙት “ወደ አላህ ማቃሚብን እንዲያቀርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቾውም” (ይላሉ።)} [ዙመር፡ 3] 2.  {وَيَعُؚۡدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمۡ وَلَا يَنفَعُهُمۡ وَيَقُولُونَ هَٰٓ؀ُلَآءِ ؎ُفَعَٰٓ؀ُنَا عِندَ ٱللَّهِۚ} {ኹአላህም ሌላ ዚማይጎዳ቞ውን እና ዹማይጠቅማቾውን ያመልካሉ። “እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻቜን ናቾው” ይላሉም።} [ዩኑስ፡ 18] ልብ በሉ! ወደ አላህ ለመቃሚብ ነው ጣኊቶቜን ዚሚያመልኩት እያለን ነው። ኢብኑ ዐባስ ሚዲዚላሁ ዐንሁማ እንዲህ ይላሉ፡- كَانَ الْمُ؎ْرِكُونَ يَقُولُونَ: لََؚّيْكَ لَا ؎َرِيكَ لَكَ، قَالَ: فَيَقُولُ رَسُولُ اللهِ ï·º: «وَيْلَكُمْ، قَدْ قَدْ» فَيَقُولُونَ: إِلَّا ؎َرِيكًا هُوَ لَكَ، تَمْلِكُهُ وَمَا مَلَكَ، يَقُولُونَ هَذَا وَهُمْ يَطُوفُونَ ؚِالَؚْيْتِ “አጋሪዎቹ 'ለበይኹ ለአንተ ተጋሪ ዹለህም' ይሉ ነበር። ይህን ሲሉ ዹአላህ መልእክተኛ ï·º {ወዮላቜሁ በቃ በቃ!} ይሏቾው ነበር። እነሱ ግን 'ዚምትቆጣጠሚው ዚማይቆጣጠርህ ላንተ ዹሆነ ተጋሪ ቢሆን እንጂ' ይላሉ። ይህን ዚሚሉት ኚዕባን እዚዞሩ (ጠዋፍ ሲያደርጉ) ነው።” [ሙስሊም፡ 1185] እንደምታዩት ሰዎቹ በአላህ ፈጣሪነት ያምኑ ነበር። ዒባዳም ለሱ ይፈፅሙ ነበር። እንዲያውም ጣኊቶቻ቞ው አላህ ዚሚቆጣጠራ቞ው ኚሱ በታቜ ዹሆኑ እንደሆኑ በግልፅ እዚተናገሩ ነው። ይሄ ሁሉ መሹጃ እያለም “ዹለም! ዚመካ አጋሪዎቜ ኹነ ጭራሹ በአላህ አያምኑም ነበር” ዹሚል አለ። ቢገባቜሁ ቜግራቜሁ ኚቁርኣን ጋር ነው። “እና ዹአላህን ፈጣሪነት ዚሚያምኑ ኚነበሩ እንደ ኚሃዲ፣ አጋሪ ያስቆጠራ቞ው ምን ነበር?” ኚተባለ ኚምክንያቶቹ ውስጥ #አንዱ ሺርክ ነው። #ሙሜሪኮቜ ነበሩ። አላህን እንደሚያመልኩት ጣኊቶቻ቞ውን ያመልካሉ። ለአላህ ሐጅ እንደሚያደርጉት በሐጁ ላይ ጣኊቶቻ቞ውን ይጠራሉ። “ዹአላህ ባሪያ” ብለው ስም እንደሚያወጡት “ዹዑዛ ባሪያ” ብለው ስም ያወጣሉ። በአላህ እንደሚምሉት በጣኊቶቻ቞ው ይምላሉ። ለአላህ እንደሚያርዱት ለጣኊቶቻ቞ው ያርዳሉ። አላህን እንደሚወዱት ጣኊቶቻ቞ውን ይወዳሉ። ... ይሄ ተግባራ቞ው ነው ኚነብዩ ï·º ጋር ያፋጠጣ቞ው። ይሄ ተግባራ቞ው ነው ለአላህ ባላንጣ ማድሚግ ተብሎ ዚተወገዘው። {ኚሰዎቜም ኹአላህ ሌላ ባላንጣዎቜን ዹሚይዝ አለ። ልክ አላህን እንደሚወዱት ይወዷ቞ዋል} ዹሚለው ዚጌታቜን ቃል ይህን ሀሳብ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። በተመሳሳይ ዛሬም ዒባዳዎቜን ለአላህ እንደሚሰጠው ለፍጡሮቜ ዚሚሰጥና ዹሚማፀን ኹሆነ ዚነዚያን ሙሜሪኮቜ ተግባር ነው ዚፈፀመው። ዚዒባዳ ተውሒድ ኹሌለ በአላህ ፈጣሪነትና ጌትነት ማመን ብቻውን ሙስሊም አያሰኝም፣ ኚእሳትም አያድንም። በመቅሪዚይ (845 ሂ.) ንግግር ፅሁፌን ልቋጭ፡- “ተውሒደ ሩቡቢያ እነዚያ አጋሪዎቜ ያልካዱበት ለመሆኑ ጥርጥር ዚለም። ይልቁንም ጥራት ይገባውና እሱ (አላህ) ብቻ ዚነሱም ዚሰማያትና ዚምድርም ፈጣሪ፣ ለአለማቱ ጥቅም ባጠቃላይ ዹቆመ እንደሆነ ያምኑ ነበር። ይልቅ ዚተቃወሙት ዚአምልኮትና ዚውዎታን ተውሒድ ነው።” [ተጅሪዱ ተውሒዲል ሙፊድ፡ 8] ይሄ እንግዲህ ዚብዙሃኑ ሙሜሪኮቜ እምነት ነው። በጊዜው ኚነበሩ ኚሃዲዎቜ ውስጥ ዹተወሰኑ ደህሪዮቜ ነበሩ፣ በፈጣሪ ዚማያምኑ። እነዚያን ዚሚመለኚቱ መሚጃዎቜን ብቻ እዚመዘዙ ሌሎቜን አንቀፆቜን መግፋት እራስን መሞወድ ነው። = ዚ቎ሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
ППказатО все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كنا؎ة اؚن منور

አሕ ^ባሜ እና ዐብዱል ቃዲር አልጀይላኒይ (561 ሂ.) ~ ተስፈንጣሪው ዹአሕ ^ ባሜ አንጃ "አላህ ኚፍጡራን ሁሉ በላይ ነው" ዹሚሉ ሙስሊሞቜን ኚኢስላም በማስወጣት (በማ^ ክ^ ፈ^ር) ዚታወቀ ነው። ዚቡድኑ ቁንጮዎቜ በዚህ ፅንፈኛ አቋማቾው ዚተነሳ እነ ኢማሙ ዳሪሚይን፣ እነ ኢብኑ ኹዘይማን፣ እነ ኢብኑ መንደህን እስኚማብጠልጠል ደርሰዋል። ይሄ አጉል ዹሆነ አካሄዳ቞ው ግን ሳያስቡት ቅርቃር ውስጥ ሲኚታ቞ው ይታያል። "እናኚብራ቞ዋለን" ኹሚሏቾው ዑለማዎቜ ውስጥ ዹአላህን ኚፍጡራን በላይ መሆን ዚሚያፀድቁ ያጋጥሟ቞ዋልና። ጀይላኒይ ሹሒመሁላህ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ መሆን ይቜላሉ። ዹአላህን ኚዐርሹ በላይ መሆን አንዮ ሳይሆን ደግመው ደጋግመው አስሚግጠው ገልፀዋል። ይህንን እውነት ዚማይቀበሉትን ኮንነዋል። ኹዚህም አልፈው አሻዒራን በስም ጠቅሰው አብጠልጥለዋል። ይሄ ለአ^ ሕ^ባሟቜ ኚባድ ራስ ምታት ነው። አይቀበሏቾው እነሱ ዘንድ ዹማይሆን ነገር ነው። ሌሎቜን እንደ - ሚያ* ኹ^ ፍሩ እንዳያኚ * ፍ- ሯ ^ቾው በሱፊያው ዓለም ያላ቞ው ቊታ እጅግ ዹገዘፈ ነው። ሌሎቜን በሚያ* ኹ^ ፍሩበት ጉዳይ እሳ቞ውን ሲያልፉ ደግሞ አጭ በርባሪነታ቞ው ገሃድ ይወጣል። ምን ይሻላል? ሜምጥጥ አድርገው መዋሞትን እንደ ዘዮ መርጠው ነበር። ቜግሩ ግን ውሞቱም ዚነሱን ዝቅጠት ኚማጋለጥ ባለፈ ዚሚፈይድ አለመሆኑ ነው። ቀጥሎ ጀይላኒይ ዹአላህን ኹ0ርሹ በላይ መሆን ያፀደቁባ቞ውን ንግግሮቜ እጠቅሳለሁፊ [1ኛ]:- وأن الله تعالى خلق سموات ؚعضها فوق ؚعض، وسؚع أرضين ؚعضها أسفل من ؚعض، ومن الأرض العليا إلى السماء الدنيا مسيرة خمسما؊ة عام، وؚين كل سماء وسماء مسيرة خمسما؊ة عم، والماء فوق السماء الساؚعة، وعر؎ الرحمن فوق الماء، والله تعالى على العر؎ “ዹላቀው አላህ ሰማያትን ኚፊሎቹን ኚኚፊሎቹ በላይ፣ ሰባት ምድሮቜን ደግሞ ኚፊሎቹን ኚኚፊሎቹ በታቜ አድርጎ ፈጥሯል። ኹላይኛዋ ምድር እስኚ ታቜኛዋ ሰማይ ድሚስ አምስት መቶ አመት ዚሚያስኬድ ርቀት አለ። ኚእያንዳንዱ ሰማይ እስኚ ቀጣዩ ሰማይ ድሚስ እንዲሁ ዚአምስት መቶ አመት ጉዞ ርቀት አለ። ውሃው ኚሰባተኛው ሰማይ በላይ ሲሆን ዹአሹሕማን ዐርሜ ኹውሃው በላይ ነው። ኹፍ ያለው አላህ በዐርሹ ላይ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/123] [2ኛ]:- وَهُوَ ؚِجِهَةِ العُلُوِّ، مُسْتَو عَلَى العَرْ؎ِ، ... واللهُ تَعَالَى عَلَى العَرْ؎ِ وَلاَ يَخْلُو منْ عِلْمِهِ مكانٌ، وَلاَ يجوزُ وصفهُ ؚأنَّهُ فِي كلِّ مكانٍ، ؚلْ يقالُ: إنَّهُ فِي السَّمَاءِ عَلَى العَرْ؎ِ “እርሱ በላይ አቅጣጫ ኚዐርሹ በላይ ኹፍ ብሎ ነው። 
 ዹላቀው አላህ በዐርሹ ላይ ነው። ኚእውቀቱ ዚሚራቆት ቊታ ዚለም። ‘እርሱ ሁሉም ቊታ ነው’ ብሎ መግለፅ አይፈቀድም። ይልቁንም እርሱ በሰማይ በዐርሹ ላይ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/121] [3ኛ]:- وهو ؚاين من خلقه، لا يخلو من علمه مكان، ولا يجوز وصفه ؚأنه في كل مكان، ØšÙ„ يقال: إنه في السماء على العر؎ “እርሱ ኚፍጡሩ ተለይቶ ነው ያለው። ኚእውቀቱ ዚቱም ቊታ አይራቆትም። ‘በሁሉም ቊታ ነው’ ብሎ እሱን መግለፅ አይፈቀድም። ይልቁንም በሰማይ በዐርሹ ላይ ነው ይባላል።” ይህን ካሉ በኋላ ዚቁርኣንና ዚሐዲሥ ማስሚጃዎቜን ዘርዝሚዋል። አለፍ ብለውም “ዚኢስቲዋእን መገለጫ ያለ ‘ተእዊል’ (ቁልመማ) በዐርሹ ላይ ኹፍ ማለት ነው ብሎ ያለ ገደብ መሚዳት ይገባል” ካሉ በኋላ ኚርራሚያ፣ #አሜዐሪያና ሙዕተዚላን ኹነ ተሳሳተው ትርጓሜያ቞ው ጋር በስም ጠቅሰው አውግዘዋል። [አልጉንያ፡ 1/124] [4ኛ]:- كَوْنُهُ عزَّ وجلَّ عَلَى العَرْ؎ِ مذكورٌ فِي كلِّ كتاٍؚ أُنزلَ عَلَى كلِّ نؚيٍّ أُرسلَ ؚلا كَيْفٍ “አሾናፊውና ዹላቀው - ያለ አኳኋን - በዐርሹ ላይ መሆኑ በሁሉም ዹተላኹ ነብይ ላይ በተወሹደ መፅሐፍ ውስጥ ሁሉ ተጠቅሷል።” [አልጉንያ፡ 1/125] [5ኛ]:- وأنه تعالى ينزل في كل ليلة إلى سماء الدنيا، كيف ؎اء وكما ؎اء، فيغفر لمن أذنؚ وأخطأ وأجرم وعصى لمن يختار من عؚاده وي؎اء، ... لا ؚمعنى نزول رحمته وثواؚه على ما ادعته المعتزلة والأ؎عرية “ዹላቀው (አላህ) በዚሌሊቱ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ በሚሻው ሁኔታ፣ እንደ መሻቱ ይወርዳል። ሃጢአት ለፈፀመ፣ ለተሳሳተ፣ ለወነጀለ፣ ላመፀ ይምራልፀ ኚባሮቹ ለመሹጠውና ለፈለገው። እንጂ ሙዕተዚላና #አሜዐሪያ እንደሞገቱት ዚእዝነቱና ዚምንዳው መውሚድ አይደለም።” [አልጉንያ፡ 1/125] በጀይላኒይ ላይ ወሰን በማለፍ ለሚታወቁት በርካታ ሱፊዮቜ ይሄ እጅግ አስደንጋጭ ነገር ነው። በቁርኣንና በሐዲሥ ላይ እንደለመዱት አይቆለምሙት፣ አይመቜም። ጭራሜ “አሜዐሪያ” እያሉ በስም ጠርተው ነው ደጋግመው ያብጠለጠሏ቞ው። ምን ይሻላል? ቢጚንቃ቞ው ሁለት ዓይነት ማምለጫዎቜን ዘይደዋል። [ማምለጫ አንድ]ፊ አንዳንዶቹ: “ሌሎቜ ሰዎቜ በኪታባ቞ው ውስጥ አስገብተውባ቞ው እንጂ እሳ቞ው ይህን አላሉም” በማለት አይናቾውን በጹው አጥበው ዚተኚራኚሩ አሉ። ለምሳሌ ሀይተሚይ (974 ሂ.)። [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 145] ግና ኹሀይተሚይ በፊት ያለፉ ታላላቅ ዑለማዎቜ - ሱፊዮቜ ጭምር - ያሚጋገጡት ሐቅ በእንዲህ አይነት ድንጋጀ በወለደው ባዶ ሙግት አይፈርስም። ሲጀመር ሀይተሚይ በመሰል ጉዳዮቜ ላይ ሚዛናዊነት ዚለውም። እንደ ኢብኑ ዐሚቢይ ላሉ አፈንጋጮቜ እዚተሟገተ እነ ኢብኑ ተይሚያን በሃሰት ዹሚወነጅል ነው። [ማምለጫ ሁለት]ፊ "ኋላ ቶብተዋል" ዹሚል ነጭ ውሞት ነው። ይህንን ካሉት ውስጥ ያፊዒይ (768 ሂ.) ተጠቃሜ ነው። ያፊዒይ ኹላይ ዚተዘሚዘሩትን ንግግሮቜ ዹጀይላኒይ መሆናቾውን ይመሰክራል። ይሄ ለሀይተሚይ ምላሜ ይሁንልን። ነገር ግን በህይወታ቞ው መጚሚሻ ላይ “ዐቂዳ቞ውን ቀይሹዋል ይላል። “ማስሚጃው” አስቂኝ ነው። ዹጀይላኒይ “አላህ ኚዐርሜ በላይ ነው” ብሎ ማመን ለኢብኑ ደቂቀል ዒድ ሲደርስ በጀይላኒይ “አፈንጋጭነት” ይገሚማሉ። ጀይላኒይም ይሄ ነገር ሲደርሳ቞ው በህይታ቞ው ፍፃሜ ላይ ዐቂዳ቞ውን ቀዚሩ ይላል። ያፊዒይ ይቀጥልና ታሪኩን ዹነገሹኝን ነጅሙዲን አልአስፈሃኒይን አልጠሚጥሚውም። ምክንያቱም እሱ ዚኚሜፍ (መገለጥ) ባለቀት ነውና ይላል። [ሚርኣቱል ጂናን፡ 3/272] ሱፊያ ሰፈር እንዲህ አይነት በሬ ወለደ ወሬ ብርቅ አይደለም። ያፊዒይም በዚህ ዚታወቀ ነው። ለማንኛውም ጀይላኒይና ኢብኑ ደቂቀል ዒድ ዘመናቾው አይገናኝም። ኢብኑ ደቂቅ ዚተወለዱት ጀይላኒይ ኚሞቱ ኹ64 በኋላ ነው። ምኑን ኹምኑ እንደሚያገናኝ ተመልኚቱ። ባለ ኚሜፉ እንዲህ አይነት መክሹፍ (ዹተጋለጠ) ውሞት ነው ዚዋሞው። ታሪኩ ቅጥፈት እንደሆነ ሌሎቜ ነጥቊቜን መጹመር ቢቻልም በዚህ ደሹጃ ላለ ቅጥፈት ደክሜ ማድኚም አልፈለግኩም።
ППказатО все...
ЀПтП МеЎПступМе
ልብ በሉ! እንዲህ ዚሚንደፋደፉት ለጀይላኒይ ያላ቞ው ዹተጋነነ ቊታ እና ዹጀይላኒይ ብርቱ ፀሹ አሜዐሪያ አቋም አልጣጣም ብሎ ስላስ቞ገራ቞ው ነው። ኚቅርቃሩ መውጫ መንገድ እውነቱን መቀበል ብቻ ነበር። ግን በራሱ ላይ ቆልፎ ስለ ተቀመጠ አካል ምን ማለት ይቻላል?! = (ኢብኑ ሙነወር፣ ሾዋል 16/1444 (ሚያዚያ 28/2015)) ዚ቎ሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
ППказатО все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كنا؎ة اؚن منور

ሙሓደራ 183 ክፍል አንድ (001) ★ ሚድ በ አሕባሹ አቡበኚር ላይ ★ 👉በ ሞይኹል ኢስላም ላይ ለቀጠፈው ቅጥፈት ዹተሰጠ ምላሜ እናም ሌሎቜ 🎙በ ኡስታዝ ኞድር አሕመድ አል ኹሚሮ(አቡ ሓቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed https://t.me/UstazKedirAhmed https://t.me/UstazKedirAhmed
ППказатО все...
አንድ እውነት በአሕ ^ባሜ ስብኚት ለተሞወዳቜሁ ሁሉ ~ ቀደምት ዚአሜዐሪያ መሪዎቜ ዹአላህን ኚፍጡራን በላይ መሆን ያምኑ ነበር። "አላህ ኚዐርሹ በላይ ነው" ዹሚሉ ሰዎቜን ኚኢስላም በማስወጣት ለሚታወቁት አሕ - ባሟቜ ይህንን መቀበል ኚባድ ነው። መሹጃው ይሄውና፡- 1. ኢብኑ ኩላብ (240 ሂ.)፡- አሜዐሪዮቜ ዘንድ ዹተኹበሹ “ዹኛ” ዚሚሉት ሞይኜ ነው። ዚዛሬ አሜዐሪዮቜ ኹዚህ ሰውዹ ዚቀዱት መሰሚታዊ ዐቂዳ ስላላ቞ው እውነተኛው ዚአሜዐሪያ መዝሀብ መስራቜ ኢብኑ ኩላብ ነው እስኚሚባል ተደርሷል። አሜዐርዮቹ አቡ መንሱር አልበግዳዲይና ሞህሚስታኒም ሞይኻ቞ው እንደሆነ መስክሚዋል። [ኡሱሉዲን፣ በግዳዲይ፡ 104] [ኒሃዚቱል ኢቅዳም፡ 303] ኹመሆኑም ጋር በያዝነው ጉዳይ ላይ ያለው ዐቂዳ ግን ኚነሱ ዹተለዹ ነው። ይሄውና ቃሉ፡- ولو لم ي؎هد لصحة مذهؚ الجماعة في هذا الفن خاصة إلا ماذكرنا من هذه الأمور لكان فيه ما يكفي، كيف وقد غرس في ؚنيه الفطرة ومعارف الآدميين من ذلك مالا ؎يء أؚين منه ولا أوكد؟ لأنك لا تسأل أحدا من الناس عنه، عرؚيا ولا عجميا، ولا م؀منا ولا كافرا فتقول: أين رؚك؟ إلا قال: في السماء إن أفصح، أو أومأ ؚيده أو أ؎ار ؚطرفه إن كان لا يفصح “ለ(አህሉ ሱና) ወልጀማዐ መዝሀብ ትክክለኝነት በዚህ ዘርፍ ላይ ዚጠቀስና቞ው ነገሮቜ እንጂ ሌላ ምስክር ባይኖር እንኳ በዚህ ውስጥ ዹሚበቃ ነገር አለ። በንፁህ ተፈጥሮና በሰው ዘር እዝነ ልቩና ላይ ዹተተኹለ ነገር እንዎትስ ብሩህና ዹፀና አይሆን? ምክንያቱም ዐሚብም ይሁን ሌላው አማኝም ይሁን ኚሃዲ ማንንም ሰው ‘ጌታህ ዚት ነው?’ ብለህ ስለሱ አትጠይቅም መግለፅ ኚቻለ ‘በሰማይ’ ዚሚልህ፣ መግለፅ ካልቻለ በእጁ ወይም በአይኑ ዚሚያመላክትህ ቢሆን እንጂ።” [ደርእ፡ 6/194] [አልጁዩሜ፡ 1/435] "ዚተጠቀምካ቞ው ምንጮቜ ዚኢብኑ ተይሚያ ኪታቊቜ ናቾው" ዹሚል ተቃውሞ ዚሚያነሳ ካለ ኢብኑ ኩላብ ዹአላህን ኚዐርሹ በላይ መሆን በሚገባ ያፀድቅ እንደነበር አቡል ሐሰን አልአሜዐሪይና አቡ መንሱር አልበግዳዲይም አሚጋግጠዋል። [መቃላቱል ኢስላሚዪን፡ 299] [ኡሱሉዲን፡ 113] ኢብኑ ኩላብ ዛሬ አሕባሟቜ ዚሚያራምዱትን አቋም እንዲህ ሲል ኮንኖታል፡- “ኚአእምሯዊ ምልኚታም ኚቁርኣንና ሐዲሥም ዚመጚሚሻ ያፈነገጠው ደግሞ ‘አለም ውስጥም አይደለም፣ ኚሱ ውጭም አይደለም’ በማለት እኩል ያራቆተው ነው። ምክንያቱም ‘እስኪ ባለመኖር ግለፀው’ ቢባል ኹዚህ በበዛ ስለሱ ምንም ሊል አይቜልምና። ቀጥተኛ ዹሆኑ ዹአላህን ዘገባዎቜ ነው ዚመለሰው። ኚማስሚጃም ኚአመክንዮም አንፃር ዹማይሆን ነገር ነው በዚህ ላይ ዚተናገሚው። ዚጠራው ተውሒድ ይሄ እደሆነ ሞግቷል። ጥርት ያለው ማራቆት እነሱ ዘንድ ጥርት ያለው ማፅደቅ ሆኗል።” [ደርእ፡ 6/119] [በያኑ ተልቢሲል ጀህሚያ፡ 1/44] 2. ሓሪሥ አልሙሓሲቢይ (243 ሂ.)፡- አሜዐሪዮቜ እንደ ሞይኻ቞ው ዚሚወስዱት ነው። [ኡሱሉዲን፡ 208-209] ዹአላህን ኚፍጡራን በላይ መሆን በሚገባ ያፀድቃል። ለምሳሌ ይህን ዚሚያመላክቱ ማስሚጃዎቜን ኹዘሹዘሹ በኋላ እንዲህ ብሏል፡- فهذا مَقْطَعٌ يوجُؚ أنَّهُ فوقَ العر؎ِ، فوقَ الأ؎ياءِ، منزَّهٌ عَنِ الدُّخولِ في خلقهِ، لا يخفى عليهِ منهم خافية، لأنَّهُ أؚانَ في هذهِ الآياتِ أنَّ ذاتَهُ ؚنفسهِ فوقَ عؚادهِ “ይሄ እርሱ ኚዐርሹ በላይ፣ ኚነገሮቜ በላይ እንደሆነ በፍጡሮቹ ውስጥ ኚመግባት ዚጠራ እንደሆነና ኚነሱ ዚትኛዋም ስውር ነገር እንደማትሰወሚው ዚሚያስሚግጥ ክፍል ነው። ምክንያቱም በነዚህ አንቀፆቜ ውስጥ እሱ ዛቱ በራሱ ኚባሮቹ በላይ እንደሆነ ግልፅ አድርጓልና። 
” ቀጥሎም ማስሚጃዎቜንና ዘለግ ያሉ ትንታኔዎቜን ይሰጣል። [ፈህሙል ቁርኣን፡ 349 - 352] በሌላ ቊታም ስለ ቁርኣን ሲያወራ እንዲህ ብሏል፡- وَقد تكلم ؚِهِ ؚِنَفسِهِ من فَوق عَرْ؎ه وأنزله مَعَ الْأمين من ملايكته إِلَى أَمِين أهل الأَرْض “በርግጥም በሱ (በቁርኣኑ) ኚዐርሹ በላይ ሲሆን በራሱ ተናግሯል። ኚመላእክት ውስጥ ኚታማኙ (ጂብሪል) ጋር ኚምድራውያን ውስጥ ታማኝ ወደሆነው (ሙሐመድ) አውርዶታል።” [ፈህሙል ቁርኣን፡ 309] 3. አቡል ዐባስ አልቀላንሲይ፡- ኚአቡል ሐሰን አልአሜዐሪይ ጋር አንድ ዘመን ኹመሆኑ በስተቀር ዚውልደቱም ዚህልፈቱም አመት በውል አይታወቅም። ኚአሜዐሪያ ኢማሞቜ እንደሆነ ግን እራሳ቞ው መስክሚዋል። [ኡሱሉዲን፡ 310] አቡ መንሱር አልበግዳዲይ በኢስቲዋእ ዙሪያ አሜዐሪዮቜ ያንፀባሚቋ቞ውን ዚተለያዩ ሀሳቊቜ ሲዘሚዝር እንዲህ ብሏል፡- ومنهم من قال: إن استواءه على العر؎ كونه فوق العر؎ ؚلا مماسة، وهذا قول القلانسي وعؚد الله ØšÙ† سعيد “ኚነሱም ውስጥ ‘ኢስቲዋኡ ያለ መነካካት ኚዐርሹ በላይ መሆኑ ነው’ ያለ አለ። ይህ #ዚቀላንሲይ እና ዚዐብደላህ ብኑ ሰዒድ (ኢብኑ ኩላብ) አቋም ነው።” [ኡሱሉዲን፡ 113] ኚኢብኑ ዐሳኪርም እንዲህ ዹሚል ማሚጋገጫ እናገኛለን፡- وَهُوَ من جملَة الْعلمَاء الْكَِؚار الْأَثَؚْات واعتقاده مُوَافق لاعْتِقَاده فِي الْإِثَؚْات “እርሱ (ቀላንሲይ) ኚታላላቅና ታማኝ ዑለማዎቜ ውስጥ ሲሆን እምነቱም ኚሱ (ኚአቡል ሐሰን) ዹማፅደቅ እምነት ጋር ተመሳሳይ ነው።“ [ተብዪን፡ 398] ኢብኑ በዚዛም (662 ሂ.) እንዲህ ብሏል፡- “ኚአሜዐሪያ መሻይኜ ውስጥ ዹሆነው አልቀላንሲይ በሞሪዐ ዚተዘገቡ ጉልህ ማስሚጃዎቜን በመንተራስ ‘ዹላቀው አላህ በሁሉም ቊታ ሳይሆን በአንድ ቊታ ነውፀ እርሱ በሰማይ ነው’ ወደሚል አቋም ተጉዟል።” [አልኢስዓድ ፊ ሾርሒል ኢርሻድ፣ ኢብኑ በዚዛ፡ 225] 4. አቡል ሐሰን አልአሜዐሪይ (324 ሂ.)፡- አህሉ ሱና “ዹላቀው አላህ በምድሩ ሳይሆን ኚሰማያቱ በላይ በዐርሹ ላይ እንደሆነም ኢጅማዕ አድርገዋል። ... ዚኢስቲዋኡ ፍቺ ቀደሪያዎቜ (ሙዕተዚላዎቜ) እንደሚሉት መቆጣጠር ማለት አይደለም” ብሏል። [ሪሳላ ኢላ አህሊ ሠግር፡ 130-131] ስለ አቡል ሐሰን ዐቂዳ ዝርዝር ዹፈለገ ኹዚህ በፊት ዚፃፍኩትን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይቜላልፊ https://tinyurl.com/5y8k639h 5. ዐሊይ ብኑ መህዲ አጊበሪይ (380 ሂ.)፡- ዚአቡል ሐሰን አልአሜዐሪ ተማሪ ነው። እንዲህ ብሏል፡- اعلمْ - عصمنا الله وإيَّاكَ مِنَ الزيغِ ؚرحمته - أنَّ الله سؚحانه في السَّمَاء فوقَ كلِّ ؎يءٍ، مستوٍ على عر؎هِ، ؚمعنى أنَّه عَالٍ عليه “እኛንም አንተንም አላህ በእዝነቱ ኚጥመት ይጠብቀንና - ዚጠራው አላህ - ኹሁሉም ነገር በላይ በሰማይ እንደሆነ፣ በዐርሹ ላይ ኹፍ ያለ ነው በሚል ፍቺ ኢስቲዋእ ያደሚገ እንደሆነ እወቅ።”
ППказатО все...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

ኚዚያም ቁርኣናዊ ማስሚጃዎቜን ዹዘሹዘሹ ሲሆን ቀጥሎም ኢስቲዋእን በኢስተውላ (ተቆጣጠሚ) በመተርጎም በሚታወቁት ሙዕተዚላ ላይ ዹሰላ ትቜት ሰንዝሯል። [ተእዊሉል አሓዲሢል ሙሜኪላ፣ ኢብኑ መህዲ፡ 24ኛ ወሚቀት] [አልአስማእ፣ በይሀቂ፡ 2/307] “ኢስቲዋእ በዐሚብ ቋንቋ መቆጣጠር ማለት አይደለም” በማለትም ለአክባሪዎቹ አሜዐሪያዎቜ ም቟ት ዚማይሰጥ ምስክርነት ሰጥቷል። [ተእዊል፡ 25ኛ ወሚቀት] ልብ በሉ! ዐሊይ ብኑ መህዲ አላህ ኹሁሉ ነገር በላይ በዐርሹ በላይ መሆኑን ያፀድቅ እንደነበር በይሀቂይም መስክሚዋል። [አልአስማእ፡ ቁ. 870] አሜዐሪዮቜ “ኢስተዋ” ዹሚለውን “ኢስተውላ” እያሉ ለመቆልመም (ተእዊል ለማድሚግ) ዚሚጠቀሙትን ስንኝ አስመልክቶም እንዲህ ብሏል፡- “በዐርሹ ላይ ኢስቲዋእ ዚማድሚጉ ትርጓሜም ገጣሚው 
 እንዳለው እሱን መቆጣጠር ሊሆን አይቜልም። ምክንያቱም መቆጣጠር ማለት ቜሎታና ሃይል ነው። ዹላቀው አላህ ደግሞ ቻይ፣ ሃያልና አሾናፊ ኹመሆን ተወግዶ አያውቅም። {ኚዚያም በዐርሹ ላይ ኹፍ አለ} ሲል ግን ይህ መገለጫ ካልነበሚ በኋላ መምጣቱን ስለሚያሳይ እነሱ ዚሚሉት ውድቅ ይሆናል።” [አተምሂድ፡ 262] በአሕ - ባሜ ዚጥመት ስብኚት ዚተሞወዳቜሁ ወገኖቻቜን ሆይ! አላህን ፈርታቜሁ፣ አኺራቜሁን አስባቜሁ፣ ህሊናቜሁን ኹነዚህ አካላት ጫና ነፃ አድርጋቜሁ እውነቱን መርምሩ። አላህ ልባቜሁን ለሐቅ ክፍት ያድርግላቜሁ። = (ኢብኑ ሙነወር፣ ሾዋል 10/1444 (ሚያዚያ 22/2015)) ዚ቎ሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
ППказатО все...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كنا؎ة اؚن منور

ЀПтП МеЎПступМе
00:32
ВіЎеП МеЎПступМе