cookie

МО вОкПрОстПвуєЌП файлО cookie Ўля пПкращеММя вашПгП ЎПсвіЎу перегляЎу. НатОсМувшО «ПрОйМятО все», вО пПгПЎжуєтеся Ма вОкПрОстаММя файлів cookie.

avatar

Exit Exam - Civil (🇪🇹)

We try to help any civil engineering students to succeed in exit exam

Більше
ЕфіПпія5 873МПва Ме вказаМаОсвіта45 438
РеклаЌМі ЎПпОсО
880
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
-27 ЎМів
-230 ЎМів

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ПрОріст піЎпОсМОків

ТрОває заваМтажеММя ЎаМОх...

ሰላም ዹዚህ ግሩፕ አባሎቻቜን ፀ መልካም ዚዕሚፍት ጊዜ እያሳለፋቜሁ እንዳላቜሁ ተስፋ እናደርጋለን።እንደሚታወቀዉ መጀመሪያዉ ዙር ፈተና ያልተሳኣላ቞ዉ ተማሪዎቜ ለቀጣይ ዙር በቂ ዝግጅት ማድሚግ ያለባ቞ዉ በመሆኑ ኚወዲሁ እንቅስቃሎ ማድሚግ ማድሚግ አስፈላጊ ነዉ። በመሆኑም ዚመጀመሪያዉ ዙር ፈተና ጥያቄ ያገኛቜሁ ካላቜሁ እንድትልኩልን እንዲሁም ተጚማሪ አስፈላጊ ናቾዉ ተጠቅመንበታል ዚምትሏ቞ዉን መሚጃዎቜ እንድትልኩ በአክብሮት እንጠይቃለን። **በቀጣይ ለሙያዊ እድገት(Career development) ዚሚያግዙ መሚጃዎቜንም ዚምንለዋወጥ ይሆናል። ኚምስጋና ጋር።
ППказатО все...
👍 6👏 1
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ምርቃት ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ኹነገ ሚቡዕ ጀምሮ ተማሪዎቻ቞ውን ያስመርቃሉ። ተቋማት ለዓመታት ያስተማሯ቞ውን ተማሪዎቜ ቀተሰቊቻ቞ው ፣ ዚክብር እንግዶቜ በተገኙበት ነው ዚሚያስመርቋ቞ው። ዘንድሮ ኹተሰጠው ዚመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ በምርቃት መርሃግብር ላይ ኚመሳተፍ ጋር በተገናኘ በተመራቂዎቜ ዘንድ ጥያቄዎቜ ዚነበሩ ቢሆንም ትምህርት ሚኒስ቎ር ይህ ጉዳይ ዚተቋማቱ #ዚሎኔት ውሳኔ ጉዳይ መሆኑን ገልጟ ነበር። በዚህም መሰሚት በተቋማት ሎኔት ውሳኔ ለምርቃት ብቁ ዹሆኑ / ዹምሹቃ ፎርማሊቲ ዚሚያሟሉ ተማሪዎቜ ዚምርቃት ስነሥርዓት ላይ ይሳተፋሉ ፀ ነገር ግን ጊዜያዊ ዚትምህርት ማስሚጃ቞ውን ዚሚወስዱት ዚመውጫ ፈተና ያለፉት ብቻ ና቞ው። ዚተቋማት ዹምሹቃ ቀን መቌ ነው ? ነገ ሚቡዕ ተማሪዎቻ቞ውን ኚሚያስመርቁ ተቋማት መካኚል ድሬዳዋ ዩኒቚርሲቲ ይገኝበታል። ዚፊታቜን ሐሙስ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ፊ - ወለጋ ዩኒቚርሲቲ (ነቀምቮ ካምፓስ) ፀ ጊምቡ እና ሻምቡ በነጋታው። - ደብሚ ማርቆስ ዩኒቚርሲቲ (በዋናው ግቢ) ፀ በ15/2015 (ቡሬ ካምፓስ) - ደብሚብርሃን ዩኒቚርስቲ - አርባምንጭ ዩኒቚርሲቲ ዋናው ግቢ) ፀ በነጋታው በሳውላ ካምፓስ - ሚዛን-ቮፒ ዩኒቚርሲቲ - ጂንካ ዩኒቚርሲቲ - ሀዋሳ ዩኒቚርሲቲ - ወላይታ ሶዶ ዩኒቚርሲቲ - ጅግጅጋ ዩኒቚርሲቲ - ሰመራ ዩኒቚርሲቲ - ዲላ ዩኒቚርሲቲ - እንጅባራ ዩኒቚርሲቲ - ዋቾሞ ዩኒቚርሲቲ (በዋናው ግቢ)  በነጋታው (ዱራሜ ካምፓስ) - መደ ወላቡ ዩኒቚርሲቲ - ቀብሪ ድሃር ዩኒቚርሲቲ - ወራቀ ዩኒቚርሲቲ - መቱ ዩኒቚርሲቲ - አምቩ ዩኒቚርሲቲ - ወልድያ ዩኒቚርሲቲ - አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቮክኖሎጂ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቻ቞ውን ያስመርቃሉ። ተቋማት ተማሪዎቻ቞ውን ካስመሚቁ በኃላ ዹ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞቜን ኹሐምሌ 16 ጀምሮ ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል። #tikvahethiopia @tikvahethiopia
ППказатО все...
👍 6
Repost from Tikvah-University
ЀПтП МеЎПступМеДОвОтОсь в Telegram
ዚመውጫ ፈተና ውጀት መታዚት ጀመሚ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዚመውጫ ፈተና ዚወሰዱ ተማሪዎቜ ውጀታ቞ውን በ " ኩላን ላይን " ማዚት መጀመራ቞ውን ማሚጋገጥ ቜሏል። ምንም እንኳን ትምህርት ሚኒስ቎ር ውጀት መታዚት ዹሚጀምሹው ኚማታ ጀምሮ መሆኑን ቢገልጜም ኹዚህ ሰዓት አንስቶ ተማሪዎቜን ዹፈተናውን ውጀት እያዩ መሆኑን አሚጋግጠናል። ዚመውጫ ፈተና ውጀት ዚሚታዚው በ result.ethernet.edu.et ላይ Username እና Password በማስገባት ነው። ድሚገፁ ተመራቂዎቜ ፈተናውን ማለፍ አለማለፋቾውን ካገኙት ውጀት ጋር Pass / fail እያለ ያሳውቃ቞ዋል። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia
ППказатО все...
❀ 1
Repost from N/a
" ዹ2015 ዚመውጫ ፈተና ዚወሰዱ ተማሪዎቜ ውጀታ቞ውን ኚእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው ዚተሰጣ቞ውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይቜላሉ " - ትምህርት ሚኒስ቎ር
ППказатО все...
👍 3❀ 2
ፈተናዉን እንዎት አገኛቜሁ?
ППказатО все...
👍 11
መልካም ፈተና እመኝላቿለሁ።
ППказатО все...
❀ 26
Repost from Tikvah-University
#Update ሁሉም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎቜ በተቋማቾው ዚምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንደሚሳተፉ ተገለጞ። መንግሥት ኹዚህ ቀደም ወስዶት በነበሹው ውሳኔ ላይ ማሻሻያ በማድሚግፀ “ዚመውጫ ፈተናን #ያላለፉ ተማሪዎቜም በተቋማቾው ዚምርቃት ፕሮግራም ላይ እንደሚሳተፉ” ዚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቜ ህብሚት አሳውቋል። ኹዚህ ቀደም ኚግማሜ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጀት (CGPA 2.00>) ያላ቞ው ተማሪዎቜ ዚምርቃት መርሃ ግብር ላይ ይሳተፉ ዹነበሹ መሆኑን ዚኢትዮጵያ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቜ ህብሚት አስታውሷል። አሁንም በተመሳሳይ ዚመውጫ ፈተናውን ዚማያልፉ ተማሪዎቜ ዚምርቃት መርሃ ግብር ላይ ዚሚሳተፉ ሲሆን ዲግሪ ለመውሰድ መሟላት ዚሚገባ቞ውን እንዲያሟሉ ይጠበቃል ብሏል። ዚመውጫ ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎቜ ለምዘና ብቁ ሲሆኑ በዚሊስት ወሩ መፈተን እንደሚቜሉም ህብሚቱ ገልጿል። ያለገደብ ድጋሚ ዹመፈተን ፍላጎት ዹሌላቾው ዕጩ ምሩቃን በደሹጃ ዝቅ ያለ ዚትምህርት ማስሚጃ መውሰድ እንደሚቜሉ በመመሪያ መቀመጡን ህብሚቱ ዹላኹልን መግለጫ ያሳያል። ዚመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎቜ በትምህርት ማስሚጃ቞ው ላይ ኹ100 ያመጡት ውጀት ዹሚገለፀው በጊዜያዊው ማስሚጃ቞ው ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ላይ እንደሆነም ህብሚቱ ጠቁሟል። @tikvahuniversity
ППказатО все...
❀ 8👍 3
Repost from Engineering Solution
Exit EXAM 6.pdf1.40 KB
Explanation 6.pdf3.26 KB
👍 4
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ይነበብ ትምህርት ሚኒስ቎ር በሀገሪቱ ዚትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድሚግ ኚጀመራ቞ው ስራዎቜ አንዱ ዹሆነ ዚተመራቂ ተማሪዎቜ ዚመውጫ ፈተና ኹነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል። በዚህ ፈተና ወቅት ኚተማሪዎቜ እና ኚፈታኞቜ ምን እጠበቃል ? [ ኚተፈታኞቜ ዹሚጠበቅ ] - ተፈታኞቜ ወደ መፈተኛ ክፍላቾው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኀክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም ዹተኹለኹለ ነው።  (ይዞ ዹተገኘ ፈተናው /ውጀቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል) - ፈተና ኚመጀመሩ ኹ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባ቞ው ይህም ማለት ኚጥዋቱ 2፡00 በፊት ፀ ኚሰዓት ደግሞ ኹ8፡00 በፊት ተፈታኞቜ መገኘት አለባ቞ው። - ተፈታኞቜ ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባ቞ው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባ቞ው። - ተፈታኞቜ ፈተና ኹተጀመሹ በኃላ ኹ30 ደቂቃ በፊት ኹፈተናው ክፍል መውጣት ዚለባ቞ውም። - ተፈታኞቜ ፀ ፈተናውን ዚሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቊታ ብቻ መቀመጥ አለባ቞ው። - ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ ዚተመደበበት ዚራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጩ መክፈትና መጠቀም አለበት። - በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ኚቊታ ቊታ መዘዋወር በፍፁም ዹተኹለኹለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ኹጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማዚት ዚለበትም። - ምንም ዓይነት ወሚቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም። - ተፈታኞቜ በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባ቞ዋል። - ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎቜ ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎቜ áˆ˜á‰³á‹˜á‹ ያለባ቞ው ሲሆን ዹፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባ቞ዋል። NB. ሁሉም ተፈታኞቜ ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሞው እንዲገቡ ዹሚደሹግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ኚፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደሹግ እንቅስቃሎ እንቅፋት ሆኖ ኹተገኘ ኹመፈተኛ አኚባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ ዚመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል። [ ኚፈታኝ መምህራን ዹሚጠበቅ ] - ዚተፈታኝ ተማሪዎቜን ID በአግባቡ በማሚጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደሹግ ይጠበቅባ቞ዋል። - ተፈታኝ ተማሪዎቜን በሥም ዝርዝራ቞ው መሠሚት ማስቀመጥ ይኖርባ቞ዋል። - ፈታኝ መምራህን ዚተፈታኝ ተማሪዎቜን አ቎ንዳንሰ ይወስዳሉ ፀ ተማሪዎቜን ፊርማ ያስፈርማሉ። - በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጜ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎቜ ኚቊታ ቊታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድሚግ አለባ቞ው። - ዹፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩሚት መኚታተል አለባ቞ው። - በህመም ምክንያት ተማሪዎቜ ኹመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ኚሱፐርቚዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። - ተማሪዎቜ በጎናቾው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለኚቱ መቆጣጠር አለባ቞ው። - ተማሪዎቜ ፈተናው ኹተጀመሹ ኹ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባ቞ዋል። - ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ ዹተገኘ ማንኛውም ተማሪ ኹመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድሚግ ይጠበቅባ቞ዋል። - ፈተናው ኹጀመሹ ኹ15 ደቂቃ በኃላ ዚሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድሚግ ዚላባ቞ውም። - ዹፈተና አፈጻጞም ሪፖርት ለሱፐርቚዘር ማቅሚብ ይጠብቅባ቞ዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መሹጃውን ኹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው ዚሰበሰበው። @tikvahethiopia
ППказатО все...
👍 4
Оберіть іМшОй тарОф

На вашПЌу тарОфі ЎПступМа аМалітОка тількО Ўля 5 каМалів. ЩПб ПтрОЌатО більше — Пберіть іМшОй тарОф.