uk
Feedback
የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

Відкрити в Telegram

*ጥቃቅን ለውጦች- አስደናቂ ውጤት!!! ** የእለት ከእለት ልማዶችን በመጠቀም የላቀ ሕይወት መምራት *** ራስን የመቆጣጠር ምስጥር **** የአቶሚክ ልማድ አስደናቂ ኃይል ***** ዘላቂ ውጤቶችን የማምጣት ምስጢር

Показати більше
945
Підписники
+124 години
+47 днів
+430 днів
Архів дописів
ጅማሬህን አንዳትርሳ! ፨፨፨፨//////////፨፨፨፨ አዲስ ስራ የጀመርክበትን፣ እራስህን ችለህ ከቤት የወጣህበትን፣ አላማህን ለማሳከት ለትምህርት ከቤተሰብህ ተለይተህ አዲስ ህይወት የጀመርክበትን፣ ሀ ብለህ የፍቅር ህይወት ውስጥ የገባህበትን፣ በሒደትም ትልቁን ትዳር የመሰረትክበትን፣ በልጆችም የተባረክበትን ቀን በፍፁም እንዳትረሳ። ማንም ትደርሳለህ ብሎ ያልጠበቀህ ቦታ ደርሰሃል፣ ማንም ባላሰበህ መንገድ እራስህን ገልጠሃል፣ ማንም በማይረዳህ ልክ ልቀህ ተገኝተሃል፣ ከፍ ብለሃል፣ አድገሃል። መሆን ያለበት እስኪሆን ድረስ በፍፁም ተስፋ እንዳትቆርጥ። እያንዳንዳችን የየራሳችን ሃላፊነት አለብን፣ እርሱንም በተወጣን ልክ ተዓምራዊ የተባለውን ህይወት በየደረጃው እናጣጥመዋልን። የሚገባህን እስክታገኝ በፍፁም እንዳትተኛ፤ ያሰብክበት ሳትደርስ እንዴትም ጉዞህን እንዳትገታ፤ የተመኘሀው ከእጅህ ሳይገባ በጭራሽ ጥረትህን እንዳታቆም። አዎ! ጀግናዬ..! ጅማሬህን እንዳትረሳ! የምንም መነሻህ ጅማሬህ ነው፤ መሰረትህ ጅማሬህ ነው። ትናንት ባትጀምር ዛሬን ባላየሀው ነበር። ምንናልባት ጉዞህ አልጋ በአልጋ ላይሆን ይችላል ነገር ግን ጨክነህ ተጉዘህበታል፣ እየመረረህ ዋጥ አድርገህ ወደፊት ተጉዘሃል፣ እንቅልፍ እያማረህ ቁጭ ብለህ አድረሃል፣ መዝናናትን እየፈለክ እራስህን ገድበህ ዋጋ ከፍለሀዋል። ሁሉም ነገር ሲያልፍ ቀላል ይመስላል ነገር ግን ምንም ነገር በቀላሉ አይመጣም። ሌላው ቢቀር በስሜትህ መጫወትህ አይቀርም፤ ከምትጠብቀውና ከሚሆነው ጋር መፋለምህ አይቀርም። ጀማሬና ፍፃሜህን እንዳትረሳ ጉዞህን ግን በሚገባ እወቀው፣ ተረዳው። ብዙዎች ከምንም ጉዞህ ከሚማሩት እንደሚማሩ፣ በጅማሬና በፍፃሜህም እንደሚበረታቱ እወቅ። አዎ! ምንም ነገር ሲጀመር በትንሹ ነው። መቼ አድጎ አስደማሚውን ለውጥ እንደሚያመጣ አይታወቅም። የጊዜ ጉዳይ እንጂ ከልብህ የምታደርገው ጥረት ይከፍልሃል፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ልፋትህ ፍሬ ያፈራል። እያንዳንዱ ትርጉም ሰጪ ድካም የእራሱ ዋጋ አለው፤ የትኛውም ስሜት ሰጪ ጥረት በስተመጨረሻ የእራሱ ክፍያ አለው።  ትምህርትህን ከታች ትጀምራለህ በሂደትም አንተም እያደክ የትምህርት ደረጃህም እያደገ ይሔዳል፤ በእውቀት ትታነፃለህ፣ በጥበብ ትጎለምሳለህ፣ ስራህን በብድር ትጀምራለህ በሒደትም ድፍረትና ጥረትህ በአንድላይ ህይወትህን ሲቀይሩ ትመለከታለህ። ተስፋ ሁሌም አለና ተስፋ አትቁረጥ፤ አንዳች ከባድ ፈተና ቢገጥም በፈተና ለመሸነፍ እንዳልጀመርክ አስታውስ፤ አንዳች የሚያንገራገር ስሜት ቢሰማህ የጀመርክበትን ምክንያት እያስታወስክ ተሻገረው። 😊 💪

ተስፋ ይኑርህ ! ሁሌም የምናገኘው ውጤት የለፋንበትን እና አብዝተን የጠየቅነውን እንዲሳካልን የፀለይነውን ነው በዚህ ሁኔታ ታድያ ተስፋ መቁረጥ የሚባል ነገር በፍፁም አያስፈልግም ፤ ምላሹ ሊዘገይ ቶሎ ላይሰጥ እናም የማይሳካ መስሎ ሊሰማ ይችላል ግን ህልማችን ተስፋ ሳንቆርጥ ከልባችን ከታገልንለት ይዘግይ እንጂ እውን ይሆናል ከቆምንም ቆሞ ይቀራል ስለዚህ ወደኋላ ማለት አይፈቀድም ሁሉም ነገር ወደፊት ይሆናል! ደስ የሚል ምሽት ተመኘው🙏

ደስ ይበልህ! እውነተኛ ለውጥ በፈተናና በችግር የተሞላ ነው፤ ከንብ ማር መውሰድ የሚፈልግ ሰው ንድፊያዋን መታገስ አለበት። ወዳጄ ነገሮች ከባድ ሲሆኑ ብታዝን፣ ብታማርር ወይ ራስህን ብትጎዳ ምንም አትፈጥርም! በፈተና ደስ ይበልህ ምክንያቱም ጠንካሮች ናቸው የሚፈተኑት!  ልዩ ምሽት ተመኘው።

ሰባኪው አዲስ ተጋቢ ሙሽሮችን ወደመድረክ ጠርቶ የጋብቻ ስስነርዓታቸውን እያስፈፀመ እያለ "ይህንን ጋብቻ የሚቃወም ካለ ወደ መድረክ ይምጣ አለ!" በዚህ ጊዜ አንድ የ3 ዓመት ህፃን ልጅ ያቀፈች እርጉ
ሰባኪው አዲስ ተጋቢ ሙሽሮችን ወደመድረክ ጠርቶ የጋብቻ ስስነርዓታቸውን እያስፈፀመ እያለ "ይህንን ጋብቻ የሚቃወም ካለ ወደ መድረክ ይምጣ አለ!" በዚህ ጊዜ አንድ የ3 ዓመት ህፃን ልጅ ያቀፈች እርጉዝ ሴት ከአዳራሹ መጨረሻ ወንበር ተነስታ ወደፊት ማዝገም ጀመረች። ሙሽሪትም ያች ህፃን የያዘች እርጉዝ ሴት ወደፊት ስትመጣ ስታይ ሙሽራውን ወራዳ ልክስክስ በሚስትህ ላይ ነው ልታገባኝ የነበረው አለችና በጥፊ ሙታው በጎን ባለው በር ወጥታ ሮጠች። ታዳሚውም አብዛኛው እያጉረመረመ በሚቀርበው በር እየወጣ ሄደ። ያች ህፃን የያዘች ሴት ፊት ወንበር ላይ ስትደርስ ከአንዱ ወንበር ላይ ቁጭ አለች። ሰባኪውም ግራ ተጋብቶ "ምነው ችግር አለ እህቴ?" አላት። ያች ሴትዮም "ምንም ችግር የለም ጌታዬ! ጆሮዬ የመስማት ችግር ስላለበት በደንብ እንዲሰማኝ ከፊት ልቀመጥ ብዬ ነው!" አለችው። ♥የመልዕክቱ አንኳር ጭብጥ፡- የነገሮችን ፍፃሜ ሳናይ/ሳንሰማ/ ቸኩለን በግምት አንደምድም(አንወስን) የሚል ነው! መልካም ሰንበት !!!

ሁሉም ሰው የራሱ ነገር አለው ! እኛ በአንድ መንገድ ተሳካልን ደስተኛ ሆንን ማለት ሌሎች ሰዎችም ሁሉ በዛ መንገድ ነው የሚያልፍላቸው የሚያሳኩት የሚደሰቱት ማለት አይደለም ፤ እኛ የፈለግነውን መውደድ እንችላለን ነገር ግን ሌሎችን እኛ የወደድነውን እንዲወዱ የመረጥነውን እንዲመርጡ ማስገደድ አለብን ማለት አይደለም ሁሌም ቢሆን መሆን እና ማየት ያለብን የእኛ የሆነውን ለእኛ የተሰጠውን ብቻ ነው እንደ እከሌ ለምን አልሆነልኝም ወይም አልሆንኩም ብለን ልንከፋ አይገባም ፤ የተሰራነው እንደሌላው እንድንሆን ሳይሆን እንደራሳችን ሆነን እንድንኖር  ነው! ስለዚህ ደስታን ከራሳችን እንፈልገው ! የደስታ ቀን ተመኘው🙏

የስኬት መጀመሪያው የምትወደውን ነገር ማወቅ ነው። በመቀጠል የምትወደውን መስራት ነው። የምትወደውን ስራ እስካልሰራህ ድረስ ስኬታማ ነኝ ማለት አትችልም። ዓለም ቢያደንቅህ እንኳን በውስጥህ እርካታ አ
የስኬት መጀመሪያው የምትወደውን ነገር ማወቅ ነው። በመቀጠል የምትወደውን መስራት ነው። የምትወደውን ስራ እስካልሰራህ ድረስ ስኬታማ ነኝ ማለት አትችልም። ዓለም ቢያደንቅህ እንኳን በውስጥህ እርካታ አይኖርም። ስራህን የምትወደው ከሆነ በጥልቅ ጉጉት ታከናዉነዋለህ። 📓አእምሮዎን የመጠቀም ጥበብ ✍ አቤል ፀጋዬ

ትኩረትህን ቀይር! ግራንት ካርደን የተባለ ሚሊየነር "በጣም የሚያበሳጭ ነገር በገጠመኝ ቁጥር ወረቀት አውጥቼ ትልቁ ህልሜን እፅፈዋለው፤ ከዛ እንደገና አዲስ ጉልበት እና ሀይል እሞላለሁ" ይለናል። አይንህን ከትናንሾቹ ችግሮችህ ንቀልና ትልቁ መድረሻህ ላይ አድርግ! ትኩረትህ ወዳለበት ጉልበትህ ይፈሳል፤ ከጥቃቅን ድክመቶችህ እና ሰው ምን ይለኛል ከሚለው ጭንቀትህ ይልቅ ስለ ትልቁ ፍላጎትህ ማሰቡ ብርታት ይሰጥሀል። በህይወት ወሳኙ የገጠመህ ችግር አይደለም...ወሳኙ ያንተ ምላሽና ቆራጥነት ነው! የደስታ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

በጠዋት ተነስ! "ሺ አመት አይኖር ለምን ረፈድ አርጌ እንቅልፌን አልተኛም" ብሎ ውስጥህ ሊነግርህ ይችላል። እንዲህ በለው ሰበበኛውን ድምፅ "ልክ ነህ ህይወት ስታበቃ ማንም አይከለክልህም ሺ አመት ትተኛለህ፤ አሁን የምትኖረው እድሜ ግን የተገደበ ነው ስለዚህ በጠዋት ተነስ!!" ልዩ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

ራስ ላይ ማተኮር! የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል፤ ራስህን ከሰዎች ጋር የምታወዳድር ከሆነ መቼም አትደሰትም፤ ደስ ቢልህ እንኳን ደስታህ ብዙ አይቆይም! ከራሱ ጋር የሚወዳደር ሰውን ግን ማንም አያቆመውም። በራስህ ለውጥ ደስ ይበልህ፤ ዛፎች ሁሉ እኩል አያድጉም ግን ማደግ እስከሚችሉት ከፍ ይላሉ። ወዳጄ አይንህን ከሌሎች ላይ ነቅለህ ወደ ራስህ ባየህ ቁጥር እድገትህ ፈጣን ነው፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ የአይምሮ ሰላም አለህ!

መጀመሪያ እኛን እንይ ! አብዛኛውን ግዜ ላሳኩ ሰዎች አስተያየት መስጠት ይቀናናል ፣ እንዲህ ቢያደርጉ ኖሮ እንደዚያ ቢፈጥሩ እኮ የተሻለ ያገኙ ነበር የተሻለ ይሆንላቸው ነበር ፣ እንደዚህም ቢጨምሩበት እንላለን እነሱ ያንን ነገር ሲያሳኩ እኮ ብዙ ነገሮችን ሞክረው አይተው ተረድተው ነው! ምን አልባት ግን እኛ እነሱ የደረሱበት ሩቧን እንኳን አልሞከርናትም አንዳንዴ አስተያየት ለመስጠት የምናባክነውን ግዜ ከነሱ ለመማር ብንጠቀመው ከእኛም አልፈን ለብዙዎች እንተርፋለን! ደስ የሚል ምሽት ተመኘው 🙏

ስኬት እና ደስታ በእጃችን ነው! ስኬታማ እና ደስተኛ ሰዎች ፍቅር የተሞሉ ናቸው ፤ ሁሌም ቢሆን ከመስጠት አይቆጠቡም ከማድረግ ወደኋላ አይሉም ለመጣው ሰው ሁሉ ሰላም ፍቅር መረጋጋትን ይሰጣሉ ሁሉም ሰው እነሱ ባሉበት መገኘትን ይወዳል ፤ ስለዚህ ስኬትን እና ደስታህን እሩቅ አትፈልገው ከውስጥህ ፍጠረው ከልብህ ሁን ከልብህ ውደድ ከልብህ ስጥ ያኔ ከልብህ ትደሰታለህ! ደስ የሚል ምሽት ይሁንላችሁ🙏

#የማንዴላ_ምርጥ_አባባሎች 🔴 “መቼም አልሸነፍም። ወይ አሸንፋለሁ ወይም እማራለሁ።” 🔴 "ድፍረት ማለት የፍርሀት አለመኖር ሳይሆን በፍርሀት ላይ ድል መቀዳጀት እንደሆነ ተረድቻለሁ፡ ጎበዝ ሰው ማ
#የማንዴላ_ምርጥ_አባባሎች 🔴  “መቼም አልሸነፍም። ወይ አሸንፋለሁ ወይም እማራለሁ።” 🔴 "ድፍረት ማለት የፍርሀት አለመኖር ሳይሆን በፍርሀት ላይ ድል መቀዳጀት እንደሆነ ተረድቻለሁ፡ ጎበዝ ሰው ማለት ፍርሃት የማይሰማው ሳይሆን ያንን ፍርሃት የሚያሸንፍ ነው።" 🔴” አሸናፊ...ተስፋ የማይቆርጥ ህልምኛ ነው።” 🔴 "በሕይወት ውስጥ የሚቆጠርልን እኛ መኖራችን ብቻ ሳይሆን፣ በሌሎች ህይወት ላይ ያደረግነው ለውጥ ነው” 🔴"ትምህርት ዓለምን ለመለወጥ ሊጠቀሙበት የሚችሉት በጣም ኃይለኛ መሣሪያ ነው።”    🔴”አንድ ትልቅ ኮረብታ ከወጣ በኋላ አንድ ስዉ ሊያውቅ የሚችለው ብዙ ተጨማሪ ኮረብታዎች መኖራቸውን ብቻ ነው።"            🔴 "በስኬቴ አትዳኙኝ፣ ወድቄ  በተነሳሁት ልክ ዳኙኝ ።" 🔴 "ሁሉም ሰው ራሱን ከሰጠና ለሚያደርገው ነገር ከፍተኛ ፍቅር ካለው፣ ከሁኔታዋች በላይ በመነሳት ስኬትን ሊቀዳጅ ይችላል።" 🔴"እስኪደረግ ድረስ ሁልጊዜ የማይቻል ይመስላል።"                🔴 "የተሻለችን ዓለም ለሚኖሩባት ሁሉ መፍጠር በእጅህ ላይ ነው ያለው።" 📗📒📕

ስኬት የኪራይ ቤት ነው! ስኬት ዋጋ መክፈልን ይጠይቃል ልናገኘው ለምንፈልገው ነገር ሁሌም ልንተጋለት በየቀኑ ሊሰጠው የሚገባውን ነገር ልንሰጠው ይገባናል ! አንዴ አሳክቻለው ብለን ቆመን የምናየው ነገር አይደለም ዛሬም ነገም ከነገ ወድያው ከስር ከስሩ እየኮተኮትን ልናሳድገው ይገባናል ካለበዚያ ግን የቤቱን ኪራይ እንዳልከፈለ ሰው ዋጋ ባለመክፈላችን እንባረራለን! የስኬት ጊዜ ተመኘው🙏

🌗አንድ በምሽት አቅጣጫ የጠፋበት መርከብ ከሩቅ ያየ ሰው ወደ እቤቱ ገብቶ ሻማ ይለኩሳል ሻማውም ለምን ለኮስከኝ ቢለው ሰውዬው ‹‹አቅጣጫ የጠፋው መርከብ ከሩቅ ያታየኛል ለሱ በእሳት ልጠቁመው ነው
🌗አንድ በምሽት አቅጣጫ የጠፋበት መርከብ ከሩቅ ያየ ሰው ወደ እቤቱ ገብቶ ሻማ ይለኩሳል ሻማውም ለምን ለኮስከኝ ቢለው ሰውዬው ‹‹አቅጣጫ የጠፋው መርከብ ከሩቅ ያታየኛል ለሱ በእሳት ልጠቁመው ነው ይለዋል ሻማውም ‹‹ታዲያ እኔ ሻማ ነኝ እንዴት ከሩቅ እታያለሁ›› ቢል ሰውዬውም መለሰ ‹‹ሻማዬ ሆይ አንተ ብቻ የቻልከውን ብራ›› አለውና ይዞት ይወጣና ብዙ ደረቅ እንጨቶችን እንደ ዳመራ ከቆለለ ቦሃላ በሻማው እሳት እንጨቶቹን ለኮሰ ብርሃኑም ብዙ ሆነ ያኔ መርከቡም ተመልክቶ መጣ ሰውዬውም ለሻማው እንዲህ አለው ‹‹ሻማዬ ሆይ አየህ አንተ በቻልካት መጠን ስለበራህ ያንተን ብርሀን ተቀብለው የሚያደማምቁ ብዙዎች አሉ›› አለው፡፡ እንግዲህ እንዲህ ነው የኔ ጥረት ትንሽ ናት አትበል፡፡ የቻልከውን ካደረክ ሌሎች ያንተን ብርሃን የሚቀበሉ እልፎች አሉ ‹‹የትም ሁን ማንም ሁን ያቅምህን በጎ ለማድረግ ግን አትስነፍ ደግነት እንደ ጥሩ ሽቶ ነው ከአንዱ ተነስቶ ወደ አንዱ ይጋባል›› **እንግዲህ አንዲህ ነው ለመስጠት የግድ ሃብታም መሆን አይጠበቅብህም፡፡ ደግሞ ማንም ሰው ልስጥ ካለ የሚሰጠው አያጣም፡፡

እመን! "አንድ እምነት ያለው ሰው ፍላጎት ብቻ ካላቸው 99 ሰዎች እኩል አቅም አለው" ይለናል ጆን ስቱአርት ሚል። የእምነትን ፍሬ ሳትዘራኸው ማጨድ የለም፤ ምንም ነገር እንደማያቅትህ በሂደት ሁሉም ነገሮች እንደሚሳኩልህ ማመን አለብህ! ግሩም ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

የቴሌግራም ቻናላችን 👇👇👇👇👇👇👇👇😍 https://t.me/atomichabity

ዛሬም ሰላም መሆን ይቻላል! ፨፨፨፨፨፨/////////፨፨፨፨፨፨ ዛሬም ሰላምን ማውረድ፣ በሰላም መቆየት፣ በሰላም መነጋገር ይቻላል። ያለፉት መልካም የአብሮነት ጊዜያት ቢያበቁም ዛሬ በሰላማዊና ጥሩ ሁኔታ ግንኙነትን ማስኬድ ይቻላል። በተበደልኩ ስሜት ለበዛ ጥላቻ መሰናዳት አያስፈልግም፣ የማይረባ እልህ መገባት አያዋጣም። መለያየቱ የተሻለ ምርጫ እስከሆነ ድረስ ያለፉትን አስደሳች ጊዜያት በመዘንጋት ክፋትን ብቻ መቁጠር፣ በአሉታዊ መንገድ ብቻ መፈረጅ ጤነኛ አመለካከት አይደለም። መሆን ስላለበት ሆኖልና ያለፈ ግንኙነትን እንከን ብቻ መፈለግ ዋጋ የለውም። አዎ! ጀግኒት..! ምንም ቢሆን የሆነ ጊዜ የደስታሽ ምክንያት እርሱ ነበር፤ ሲንከባከብሽ፣ ሲያዝንልሽ የነበረው ሰው እርሱ ነው። ሁኔታዎች የግንኙነቱን ቀጣይነት ባለመፍቀዳቸው ማብቃቱ እንዳለ ሆኖ፣ ልዩነቱም በስምምነትና በፍቅር መሆን ይችላል። ከዛም ቦሃላ ሰላማዊ ግንኙነት መፍጠር፣ ከተበዳይነት ስሜት መውጣትና የተረጋጋ ሰላማዊ ግንኙነት መፍጠሩ ለሁለቱም አካል እጅግ ተመራጭ አካሔድ ነው። አዎ! በውስጥህ ቂምን አዝለህ፣ ለበቀል እየተንደረደርክ መቼም የተረጋጋ ህይወት ሊኖርህ አይችልም። በዳይ ሆንክ ተበዳይ፣ ጎጂም ሆንክ ተጎጂ ከፀፀት የምትድነው፣ ወደፊት የምታስበው፣ የተሻለ የምታደርገው፣ ጥሩ ተማሪ የምትሆነው በይቀርባይነት ስትታነፅ፣ በደልን ስትተውና ቂምን ስትረሳ ብቻ ነው። አብራቹ በነበራቹ ሰዓት የሚደረግልህን ነገር ካልጠበክ ስላም የማትሆንበትና ነፃ የማትሆንበት ምክንያት የለም። ሰው ተጎዳድቶ በይቅርታ ይታረቃል፤ ምንም ታሪክ አብሮ ያላሳለፈ ሰው በሰዓታት ግጪት ቢጣላ አንድ የሚያደርገውን፣ የሚያስማማውን ነገር ላያገኝ ይችላል። ለረጅም ጊዜ አብሮ የቆየ፣ ብዙ ነገር አብሮ ያሳለፈ ሰው ግን ቢያንስ አንድ የሚያስማማውና የሚያስታርቀው ነገር አያጣም። ዳግም መስማማት በምትችለው ቁርሾ ሰላምህን አትጣ። ዛሬም ሰላም መሆን ይቻላልና ልዩነትን በፀጋ፣ ጉዳትንም በይቅርታ ማለፉን ለእራስህ ብለህ እወቅበት። ማንም ሁን ብሎ ቢበድለህ ከበዳይነት ነፃ እስከሆንክ ድረስ እራስህን አረጋጋ፣ ህሊናህን ነፃ አውጣ፣ ተጠያቂነትን ከእራስህ ላይ አውርድ። ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨ 😊💪

የቆሙ ሰዎች እንዳያቆሙህ! አንዳንድ ሰዎች የሚተቹ ቃላትን መሰንዘር ልማድ ይሆንባቸዋል ፤ ምንም ሳይሰሩ በሚሰራው ሰው ቦታ ላይ ሳይቀመጡ በእርሱ ሚዛን የመመዘን ብቃቱም ሳይኖራቸው አንተ እኮ አትረባም ይሉታል! ኳስ ሜዳ ላይ ያሉ ደጋፊዎች እንዲህ አድርግ እንዲያ አታድርግ እያሉ አስተያየት የሚወረውሩ ሰዎች ለአንድ ደቂቃ እንኳን እሱን መሆን እና ሜዳው ላይ ገብተው ለመጫወት ብቁ ያልሆኑ ሰዎች ናቸው ! ምናልባት እድሉን ቢያገኙት የተጫዋቹን ሩብ ታህል ብቃት አያሳዩም ! " ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ" አደል የሚባለው ! ለማይሰራ ሰው አስተያየት መስጠት ይቀለዋል ስለዚህ እከሌ ተቸኝ እከሌ በስራዬ አሾፈብኝ ስሜት የሚጎዳ መጥፎ አስተያየት ሰጠኝ እያልክ መንገድህን እንዳታቆም ያመንክበትን ነገር  በደንብ ከልብህ ጠንክረህ ስራበት በፍፁም እንዳትቆም !  የቆመ ሰው ሌላውን ማስቆም ነው እና አላማው ነቅተህ ራስህን አድነው! ደስ የሚል ምሽት ተመኘው🙏

ወድቆ የማይቀር ማንነት! ታላቅ ለመሆን ተፈጥረሀል! ደስተኛ ሆነህ ለመኖር ተፈጥረሀል! አሁን ያለህበትን አይተህ ራስህን ዝቅ አታርገው፤ ብርሀን ከጨለማ ጋር ምንም ህብረት የለውም፤ ያንተም ድክመት ወይ መሳሳት ጊዜያዊ ነው፤ ለምን ካልከኝ ጥሎ የማይጥል ፈጣሪና ወድቆ የማይቀር ማንነት ስላለህ! ተዓምረኛ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏